08/08/2026
የመላ ካናዳ አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት "ለኅብረት ተጠርተናል" በሚል በቶሮንቶ ከተማ ባዘጋጁት በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ ታላቅ ኮንፈረንስ ላይ እንድናገለግል በተጠራንበት፣ በኮንፈረንሱ ምጨረሻ ላይ "የአገልግሎትህን 50ኛ ዓመት" በሚል በድንገት ሰርፕራይዝ አደረጉን።
"ብርሃነ ወንጌል" በተሰኘች ቤተክርስቲያን በመዘምራን ቡድን የተሰለፍኩበት ዓመት ተጨምሮ ሲሰላ በእርግጥም 50 ዓመት መሙላቱን ያስተዋልኩት በኋላ ነው። እነዚህ 50 ዓመታት የሙላት፣ የሙቀትና የምቾት ዓመታት ብቻ አልነበሩም። የምንኖርባት ምድር ጠፍጣፋ (Flat) ብቻ ሣትሆን ወጣገባ እንደሆነች ሁሉ፣ ሕይወትም እንዲሁ ውጣ ውረድ የበዛበት ቢሆንም ቅሉ፣ ጌታን ለመከተል የመጀመሪያዋን እርምጃ እግሬን ካንሣሁበት ዕለት ጀምሮ እስከዚህች ሰዓት ድረስ በማንከስም፣ በዳዴም ሆነ በሩጫ ዘመን እጄን ይዞ የመራኝን እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ፣ ይህን የሰማ ሁሉ ያመስግንልኝ።
ወንድሜ ሸዋዬ ዳምጤ እንዳዜመው፣ "ቀሪ ዘመኔን" እንዲባርክልኝ እለምነዋለሁ፣ እናንተም ለምኑልኝ።
"ተነሥተንም ወደ ቤቴል እንውጣ፤ በዚያም በመከራዬ ጊዜ ለሰማኝ፥ በሄድሁበትም መንገድ ከእኔ ጋር ለነበረው ለእግዚአብሔር መሠውያን አደርጋለሁ" (ዘፍ. 35:3) "አቤቱ አንተ ተስፋዬ ነህና፥ እግዚአብሔር ሆይ፥ ከታናሽነቴ ጀምረህ መታመኛዬ ነህና።
አምላኬ፥ ከታናሽነቴ ጀምረህ አስተማርኸኝ፤ እስከ ዛሬም ተአምራትህን እነግራለሁ" (መዝ. 71:5 ፣ 17)
የካናዳ አብያተ ክርስቲያናት እና በክርስቶስ ቤተሰቦቻችን በመላ፣ እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይባርካችሁ እላለሁ።
የDNA of the Kingdom ministries 8ኛ ዙር ዓለም እቀፍ ጉዟችን የሚጀምረው ከፊታችን መስከረም 1/2019 (September 8/2026) በመሆኑ እንደተለመደው በጸሎታችሁ አብራችሁን እንድትጓዙ ግብዣዬ ነው።
ወንጌል ያሸንፍ! የሰው ዋጆች ሁሉ በአዳኙ ኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ይታረቁ! አብያተ ክርስቲያናት በሠላም ይኑሩ፣ ይታነጹም!ለምድራችንና ለሕዝባችን ሠላም ይሁን!!! ታምራትና ቤተሰቡ፣ ከአገልግሎት አጋሮች ሁሉ ጋር።
ሙሉ የሶሻል ሚዲያ ሊንኮቻችን
https://linktr.ee/TamiratHaile
የዝማሬ ቻናል: 👇👇
youtube.com/
የትምህርትና የሌሎች መልዕክቶች ቻናል👇👇
https://youtube.com/
የፌስቡክ ገፅ: http://facebook.com/OfficialPastorTamiratHaile
ዌብሳይት:- http://dnakingdomministries.org