Mella Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Mella, Eastern Orthodox church, Reston, VA.

I have reached 100 followers! Thank you for your continued support. I could not have done it without each of you. 🙏🤗🎉
03/19/2023

I have reached 100 followers! Thank you for your continued support. I could not have done it without each of you. 🙏🤗🎉

12/23/2022
አሜን
07/01/2021

አሜን

በዓታ ለማርያምባዕታ ለማርያም በእለተ ቀኗ ከክፉ ነገር ሁሉ ትሰውራችሁ።እናታችን ቅድት ድንግል ማርያም ከአባቷ ከእያቀብና ከእናቷ ከሐና ሐምሌ 30 ራእይ አይተው ነሐሴ 7 በብስራተ መልአክ በ...
06/10/2021

በዓታ ለማርያም
ባዕታ ለማርያም በእለተ ቀኗ ከክፉ ነገር ሁሉ ትሰውራችሁ።
እናታችን ቅድት ድንግል ማርያም ከአባቷ ከእያቀብና ከእናቷ ከሐና ሐምሌ 30 ራእይ አይተው ነሐሴ 7 በብስራተ መልአክ በፈቃደ እግዚአብሔር እሑድ ተፀነሰች።
በእናቷ ማህፀን ሳለች ብዙ ታምራትን አድርጋለች የሞተውን ሳሚናስ ከሙት አስነስታዋለች።ይህም ሳሚናስ የጦሊቅ ልጅ ከኤዶቅ ካአጎቱ ቤት ሄዶ የሞተው ለቀብር ስወስዱት ከመንገድ ባሳረፉት ጊዜ ሐናም የአጎትዋ ልጅ ነበርና ለማልቀስ ብትደርስ ዘመዶቿ ሁሉ ተሰብስበው ሲላቀሱ እርሷም እየዞረች ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ብድግ ብሎ ተነሳቶ ስብሐት ለኪ እሙ ለፀሐይ ጽድቅ ማርያም ሆይ ለአብ ሙሽራው ለወልድ ወላድቱ ለመንፈስ ቅዱስ ጽርሐ ቤቱ ተፈስሒ ደስ ይበልሽ ብሎ ሰገደላት።
መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በእናቱ በኤልሳበጥ ማህፀን ሳለ ለእናታችን ማርያም እንደ ሰገደላት ሰላም ለኪ እንዳላት
{ ሉቃ.1፥41 } ይህም የሞተው ሳምናስ ከሞተበት ተነስቶ ሰገደላት።
☞ ይህንን ታምራት ስትሰራ በሐና ማህፀን 9 ወር ተቀመጠች። ግንቦት መባቻ ዕለት{ ግንቦት 1} ልባኖስ በምትባል አከባብ ተወለደች። በስምንተኛውም ቀን ስሟን "ማርያም" ብለው አወጡላት።
☞ እናታችን ማርያም በእናት አባቷ ቤት 3 ዓመት ተቀመጠች። መዝሙረኛው ዳዊት አባቷ በ{ መዝ 44፥10-11 }ላይ ልጄ ሆይ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ ንጉስ ውበትሽን ወድዶአልና እርሱ ጌታሽ ነውና እንዳለ እናታችን ቅድት ድንግል ማርያም በ3 ዓመቷ የስለት ልጅ ናትና በተመቅደስ ወስደው ለካህኑ ለዘካርያስ ሰጧት።
☞ ቀኑም የታህሳስ ባታ ነበር።መልአኩ ፋኑኤል ከሰማይበመሰቦ ወርቅ ህብስተ ሰማያዊ በብርሃን ጽዋ ስቴ ሕይወት ይዞ ረቦ ታያቸው።እመቤታችንንም በአንዱ ክንፍ ጋርዶ በአንዱ ክንፉም አጎናፅፎ ህብስቱን አብልቷት ወይኑን አጠጥቷት እመቤቴ ሆይ! መንገድ ባስመታሁሽ ማርኝ ብሎ የብርሃን መሶብ የብርሃን ጽዋ ይዞ ወደ ሰማይ አረገ።
☞እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም ሕብስተ ሰማያዊ እየተመገ በች ስቴ ሕይወት እየጠጣች ከንጹሓን ይልቅ ንጽሕት የሆንሽ አንቺ ነሽ ከማይነቅዝ ዕንጨት እንደ ተሰራ በወርቅ እንደ ተጌጠና ዋጋው ብዙ በሆነ በሚያበራ ዕንቁ እንደተለበጠ ታቦት በቤተ መቅደስ ውስጥ የኖርሽ የተመረጥሽ ድንግል ነሽ እንዳለ እትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ በአንቀጸ ብርሃን ቁጥር 6እንዲህ ሆና መላእክት ምግቧን እያመጡላት እየጎበኟት ከመላእክት ጋራ እየተጫወተች እየዘማረች 12 ዓመት በቤተ መቅደስ ተቀመጠች።
☞ የእናታችን የድንግል ማርያም ምልጃ ጸሎት በረከት እረድኤት ከእኛ ከቃልኪዳን ልጆቿ እንዲሁ የአስራት ሃገሯ ከሆነች ከእትዮጵያ ዘወትር አይለያት አይለየን አሜን።

እንኳን ለአምላክ ወሰብእ ለቅዱስ አማኑኤል  በዓልአደረሰን"እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው።"ዘጸአት 15፤3ግንቦት 28 ቀን በቅዱስ አማኑኤል ስም የታነጸው ቤተ መቅደስ የቅዳሴ...
06/05/2021

እንኳን ለአምላክ ወሰብእ ለቅዱስ አማኑኤል በዓል
አደረሰን
"እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው።"
ዘጸአት 15፤3
ግንቦት 28 ቀን በቅዱስ አማኑኤል ስም የታነጸው ቤተ መቅደስ የቅዳሴ ቤት በዓል ነው።
2ኛው ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ እንደዘመናችን ወልድ ፍጡር ቤተክርስቲያን ድንጋይ የሚሉ ሎቱ ስብሐት ክርስቲያን አንገት የሚቆርጡ ቤተክርስቲያን በእሳት የሚያጋዮ አረማውያን በአዳል በረሐ ተነስቶባቸው ህዝባቸው በጭንቅ ተይዞ ጋሻ ጉልበታቸውን ክብር ሞገሳቸው ወደሆነው ወደ ተአምረኛው በጎል ሰከበ ደብረ መንክራት ሚጣቅ ቅዱስ ኤማኑኤል ሄደው ፈጣሪ ቅዱስ አማኑኤል የተመዘዘው የአእዛብ ሰይፍ ወደ ሐፎቶ ከተመለሰ ህዝቤን ከአረማውያን ከታደክልኝ በአዋጅ አከብርሐለው ብለው ተስለው ድልን ስላቀዳጃቸው ቤተክርስቲያን ከጥፋት ስለዳነች አረማውያኑም ቀስታቸው ስለተሰበረ ስዕለታቸው ሰምሮ በአዋጅ እንዲከበር ድብ አንበሳ ነጋሪት ጎስመው መለከት አስነፍተው አውጀዋል እኛም የአባቶቻችን ልጆች ነንና እናከብራለን ክብሩም ለእኛው ነው ቅዱስ አማኑኤል ከነፍስና ከስጋ መከራ ይሰውረን ፍቅርን ይመግበን ለሕዝብ የሚያስቡ መሪዎች ይስጠን ከፍቅር ረሐብ ከዘረኝነት ደዌ ከዝሙት እሳት ከምንፍቅና አሽክላ ቅዱስ አማኑኤል ይሰውረን
አሜን አሜን አሜን🙏🙏🙏

የአቡነ ተክለሃይማኖትን ታሪክ“ወብዙኀን ይትፌሥሑ በልደቱ:: በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል” (ሉቃ.1፥14)በዘመነ ብሉይ የእግዚአብሔር ድምፅና የመልአክ ብሥራት ብርቅ በነበረበት ወቅት ካህ...
06/01/2021

የአቡነ ተክለሃይማኖትን ታሪክ
“ወብዙኀን ይትፌሥሑ በልደቱ:: በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል” (ሉቃ.1፥14)

በዘመነ ብሉይ የእግዚአብሔር ድምፅና የመልአክ ብሥራት ብርቅ በነበረበት ወቅት ካህኑ ዘካርያስና ቅድስት ኤልሳቤጥ ልጅ መውለድ አጥተው ባረጁበት ዘመን የእግዚአብሔር መልአክ ካህኑ ዘካርያስን እንዲህ አለው፡፡ መልአኩም እንዲህ አለው “ዘካርያስ ሆይ፥ አትፍራ፤ ጸሎትህ በእግዚአብሔር ፊት ተሰምቶአልና፤ ሚስትህ ኤልሣቤጥም ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልድልሃለች፤ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ፡፡ ደስታና ሐሤትም ይሆንልሃል፤ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል፡፡ እርሱ በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ ይሆናልና የወይን ጠጅና የሚያሰክርም መጠጥ ሁሉ አይጠጣም፤ ከእናቱ ማሕፀን ጀምሮም መንፈስ ቅዱስ ይመላበታል፡፡ ከእስራኤልም ልጆች ብዙዎችን ወደ አምላካቸው ወደ እግዚአብሔር ይመልሳቸዋል፡፡ እርሱም የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች፥ የከሓድያንንም ዐሳብ ወደ ጻድቃን ዕውቀት ይመልስ ዘንድ፥ ሕዝብንም ለእግዚአብሔር የተዘጋጀ ያደርግ ዘንድ በኤልያስ መንፈስና ኀይል በፊቱ ይሄዳል፡፡” (ሉቃ1፥13-18) ይህ ለመጥምቁ ዮሐንስ የተነገረ ቃል ቢሆንም ወላጆቹ (ካህኑ ዘካርያስና ቅድስት ኤልሳቤጥ) በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን እንደነበሩ በቅዱስ ወንጌል ተገልጿል /ሉቃ.1፥6-7/ እንደዚሁ ሁሉ ካህኑ ጸጋዘአብና ሚስቱ እግዚእ ሐረያ በእግዚአብሔር ሕግና ሥርዓት ይመሩ የነበሩ ደጋግ ክርስቲያኖች ነበሩ፡፡ ይህም ሊታወቅ በትሩፋት ሥራ፣ በጾም፣ በጸሎት፣ በምጽዋት የታወቁ ነበር፡፡ በተለይም የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል በዓልን ምክንያት በማድረግ ይመጸውቱ ነበር፡፡ የመልአኩም ጥበቃ ባለ ዘመናቸው ሁሉ አልተለያቸውም ነበር፡፡ ጌታችን በቅዱስ ወንጌል ላይ “መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬን ያፈራል፣” /ማቴ.7፥17/ እንዳለ፣ ለዓለም ሁሉ የወንጌልን ብርሃን የሚያበስር ሐዲስ ሐዋርያ በቅድስናና በክብሩ ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ሃያ አምስተኛ ሆኖ ያመሰገነውን ጻድቅ ወለዱ፡፡ በሰሜን ሸዋ ጽላልሽ ልዩ ስሙ ኢቲሳ በተባለ ቦታ የተወለዱት ጻድቁ ተክለ ሃይማኖት በ12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሡና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትምህርት ከየመን እስከ ኬንያ ከሶማሌ እስከ ሱዳን ድረስ የተስፋፋበትን ወርቃማ ዘመንን ያስገኙ ጻድቅ አባት ናቸው፡፡

“ነገርን ከሥሩ ውኃን ከጥሩ” እንዲሉ የጻድቁን አባት የአቡነ ተክለሃይማኖትን ታሪክ በአጭሩ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡

ቅዱሳኑ በትሩፋት ሥራ የተጠመዱ ነበሩ ልጅ አጥተው ሲያዝኑ ይኖሩ የነበሩት ካህኑ ፀጋ ዘአብና ቅድስት እግዚእ ሐረያ፣ በየወሩ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ያከብሩ ነበርና መጋቢት 12 ቀን የተራበን ሲያበሉ ሞቶሎሚ ንጉሠ ዳሞት ሀገራቸውን ወርሮ ከእነርሱ ደረሰ፡፡ ጸጋ ዘአብም እንደማይምራቸው አውቀው አንከርት ወደሚባለው ባሕር ሮጡ፡፡ ከሞተሎሚ ጭፍሮች አንዱ ተከተላቸው፣ የማይደርስባቸው ሲሆን ሰይፉን ሊወረውርባቸው ቃጣ፡፡ ሰይፉ ከእጁ ተጠቅልላ ቀረች፡፡ በሌላ እጁ ሁለተኛ ሊወረውር ቢቃጣ አሁንም ተጠቅልላ ቀረች፡፡ እሳቸውም እንዳልተዋቸው አይተው ዘለው ከባሕር ገቡ፡፡ ከባሕር ውስጥ ሆነው እንዲህ አያሉ ይጮሁ ጀመረ…” ኀይል የምትሆነኝ ቅዱስ ሚካኤል፣ አምባ መጠጊያ የምትሆነኝ ቅዱስ ሚካኤል፣ ኀይልህ ወዴት ነው? ከኃሊነትህ ወዴት ነው? ተአምራት ማድረግህ ወዴት ነው? እንሆ መሞቻዬ ደረሰ፡፡ ዛሬ የሽብር ቀን ነው፡፡ ዛሬ የመከራ ቀን ነው፡፡ ዛሬ ጥፋት ተፈርዶብኝ፡፡ በበዓልህ ደስ ሳታሰኘኝ ታሳዝነኛለህን? እያሉ ያለቅሱ ጀመረ፡፡ "እስመ ለመላእክቲሁ ይኤዝዞሙ በእንቲአከ ከመ ኢትትዐቀፍ በዕብን እግርከ፤ በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዛቸዋልና፣ እግርህ በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸውም ያነሡሃል፡፡" እንዲል /መዝ.90፥11/ ቅዱስ ሚካኤል በውስጥ ሆኖ ተቀብሏቸዋል፡፡ “ወባሕርኒ ኮነቶ ከመ ደብተራ ዘድለት ለማኅደር” ይላል ባሕርም እንደ ድንኳን ሆነላቸው “ኦ ፍቁርየ ጸጋ ዘአብ አስመ አነ አዐቅበከ በይነ ዘይወጽእ እምሐቁከ፤ ወዳጄ ጸጋ ዘአብ ሆይ፥ ከአብራክህ ስለሚከፈለው ቅዱስ እጠብቅሃለሁና አትፍራ” አላቸው፡፡ ከዚህ በኋላ በሦስተኛው ቀን አውጥቶ ቤተ ክርስቲያን አድርሷቸዋል፡፡

በሌላ በኩል በሞቶሎሚ ወታደሮች የተማረኩት እግዚእ ሐረያ ለንጉሡ ሚስት ሊያደርጓቸው፣ ከቤተ መንግሥቱ አገቧቸው፡፡ ቅድስት እግዚእ ሐረያ ግን “ጌታዬ ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስንፍናዬን ለምን ተመለከትክ፡፡ በንጹሕ ሆኖ የሚያገለግል ባሪያህ ጸጋ ዘአብን ለምን አላሰብከውም አንተን ለሚክዱ ኃጥአን ለሚሆኑ ጠላቶች አሳልፈህ ለምን ሰጠኸኝ ሕግህን ሥርዓትህን ከማያውቅ ከሚያጸይፍ ባሪያ ልጅ ትሰጠኝ ዘንድ ወደድክን? ከዚያም ከንጹሕ አገልጋይህም ቢሆን አንተን ደስ የማያሰኝ ልጅ ካለሆነ ማኅፀኔን ዝጋው እልሃለሁ፡፡ አቤቱ የትድግና ባለቤት ዛሬ በእኔ ላይ ትድግናህን ግለጽ” በማለት ያመለክቱ ነበር፡፡ ጠባቂ መልአካቸው፡- ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ከሠራዊት ሞቶሎሚ በመንጠቅ በክንፉ ታቅፎ ከዳሞት ዞረሬ በሦስት ሰዓት አደረሳቸው፡፡ በመጋቢት ሃያ ሁለት ቀን ጸጋ ዘአብ ከቤተ መቅደስ ገብተው ሲያጥኑና ስለ እግዚእ ሐረያ ሲለምኑ፣ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ከቤተ መቅደስ አግብቶ ከዚያ ትቷቸው ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ ገድለ ተክለሃይማኖት ምዕ.12

በዚህ ሁኔታ በእግዚአብሔር ቸርነት፣ በመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት ደግም የተገናኙት ሁለቱ ቅዱሳን /ጸጋ ዘአብና እግዚእ ሐረያ/ መጋቢት ሃያ አራት ቀን ከአብራካቸው የሚከፈለውን ጻድቁ ተክለሃይማኖትን ፀነሱ፡፡ እነሆም ታኅሣሥ 24 ቀን ቅዱስ አባታችን ተወለዱ፡፡

“ገድለ ተክለሃይማኖት” የተባለው መጽሐፍ አባታችን ተክለሃይማኖት በተፀነሱበት መጋቢት 24 ቀን ለእናትና አባታቸው እግዚአብሔር ራእይ እንዳሳያቸው ይገልፃል፡፡ ቅድስት እግዚእ ሐረያ ያዩት ራእይ “የብርሃን ምሰሶ ከቤታቸው ውስጥ ቁሞ የሞሶሶው ራስ ከሰማይ ደርሶ በዓለም ያሉ ሕዝብ ሁሉ ነገሥታቱም ጳጳሳቱም በዙሪያው ቁመው እኩሌቶቹም ይሰግዱለታል፤ እኩሌቱቹም እሱን ጥግ አድርገው ይቀመጣሉ፡፡ በሱም ላይ ብዙ አዕዋፍ ተቀምጠውበታል፡፡ እኩሌቶቹ ነጫጮች፣ እኩሌቶቹም ቀያዮች፣ እኩሌቶቹ አመድ አመድ ይመስላሉ፡፡ ዝጉርጉርም ናቸው፡፡ በሌላ በኩል ካህኑ ጸጋ ዘአብ ደግሞ በዚሁ ሌሊት ስላዩት ሕልም ለእግዚእ ሐረያ ሲነግሩ እንዲህ ብለዋል፡- “ከምንተኛበት አጎበር ሥር ፀሐይ ሲወጣ፥ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ብሩሃን ከዋክብት በክንፉ ላይ ተቀምጠው ለዓለሙ ሁሉ ሲያበሩ፣ ከብርሃኑም ብዛት የተነሣ ሀገሩ ሁሉ አበራ፡፡ ይህን ራእይ ዐይቼ ደንግጬ አለቀስኩ”

ከዚህ በኋላ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል የሁለቱንም ህልም ይተረጉሙላቸው ዘንድ ከእግዚአብሔር ተልኳል፡፡ በትርጓሜውም፡- “ከጸጋ ዘአብ ቤት ሲወጣ የታየው ፀሐይ ከአብራኩ የሚከፈለው ልጁ ተክለ ሃይማኖት ነው፡፡ በብርሃኑ ከምእመናን ላይ የኃጢአትን ጨለማ የሚያርቅ ይሆናል፤ በክንፉም ላይ ታዝለው፥የታዩት ከዋክብት በመንፈስ ቅዱስ በእርሱ ትምህርት ይወለዱ ዘንድ ያላቸው ልጆቹ ናቸው፡፡ የእግዚእ ሐረያ ሕልም ትርጉሙ እንዲህ ነው በቤታቸው የብርሃን ምሶሶ ቁሞ ራሱ ከሰማይ ደርሶ ያያቸው ልጅህ ነው፡፡ ነገሥታቱ ጳጳሳቱ ሲገዙለት ያየችውም በእውነት ነገሥታቱ ይሰግዱለታል፡፡ አሕዛብም ይገዙለታል፡፡ ለሁሉም መጠጊያ ይሆናል፡፡ ከነገሥታቱ በላይ ሆኖ ይኖራል፡፡ ተአምራቱ ከዛፍ ፍሬ ይበዛል ሥፍር ቁጥር የለውም፡፡ እንደሣዕረ ምድር ጸንቶ ይኖራል፡፡ ስሙም ለዘለዓለም ሲመሰገን ይኖራል፡፡ ሰማይ ከምድር በላይ እንደሆነ የሱም ስም አጠራሩ እንደሱ ካሉ ከቅዱሳን ምእመናን በላይ ሆኖ ይኖራል፡፡ የሕልማችሁ ትርጓሜ ይህ ነው፡፡” በማለት የሕልሙን ፍች አስታውቋቸዋል፡፡ በሚያስደንቅ ልዩ ልዩ ተአምራት በቅዱስ ሚካኤል ጥበቃና በእግዚአብሔር ቸርነት ከብዙ መከራ ተጠብቀው የኖሩት ሁለቱ ቅዱሳን ባልና ሚስት /ካህኑ ጸጋ ዘአብና ቅድስት እግዚእ ሐረያ/ ታኅሣሥ 24 ቀን ፃድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ወለዱ፡፡

ከሠተ አፉሁ
ታኅሣሥ 26 ቀን /በተወለዱ ሦስተኛው ቀን/ በዕለተ ሰንበት ከጧቱ ሦስት ሰዓት ላይ እጆቻቸውን አንሥተው ወደ ሰማይ እየተመለከቱ “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ፤ ማለትም፦ ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በባሕርይ በሕልውና አንድ የሚሆን አብ በአካል በስም ልዩ ነው፣ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በባሕርይ በህልውና አንድ የሚሆን ወልድ በአካል በስም ልዩ ነው፣ ከአብ ከወልድ ጋራ በህልውና አንድ የሚሆን መንፈስ ቅዱስ በአካል በስም ልዩ ነው” በማለት ሰማያዊያን መላእክት ምድራውያን ጻድቃን ፈጣሪን በሚያመሰግኑበት ሥርዓት ሆነው አመሰገኑ፡፡ እናትየው እግዚእ ሐረያ ግን ይህንን በልባቸው እያደነቁ “ልጄ ፍሥሐ ጽዮን ምን ትላለህ ይህ ቃል የአባትህ ሥራ ነው፡፡ ላንተ ግን የሚገባህ ጡት መጥባት ነው” በማለት ተናገሩ፡፡ ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ግን ክቡር ዳዊት “እም አፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስትዳሎከ ስብሐት፡፡ በእንተ ጸላዒ ከመ ትንሥቶ ለጸላኢ ወለገፋዒ፤ ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ ስለ ጠላትህ ጠላትንና ቂመኛን ለማጥፋት” በማለት የተናገረው ቃል ተፈጽሞላቸዋል፡፡ (መዝ.8፥2)

“በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል” ተብሎ በመጋቢ ሐዲስ በቅዱስ ገብርኤል የተነገረለት ዮሐንስ መጥምቅ /ሉቃ.1፥14/ ከእናት አባቱ አልፎ ብዙዎችን ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያገናኘ የደስታ ምንጭ የሆነ ነቢይም ሐዋርያም ነው፡፡ በጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት መወለድም፣ ለጊዜው ልጅ ባለማግኘት ለብዙ ዓመታት ሲያዝኑ ለነበሩ ወላጆቻቸው ታላቅ የምሥራችና ደስታ ሆኗል፡፡ በፍጻሜው ግን ፈጣሪያቸውን ባለማወቅ በአጋንንት አገዛዝ ሥር ወድቀው የነበሩ በብዙ መቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች በጸሎታቸው ኀይልና ግሩም በሆነው ትምህርታቸው ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስን ከባሕርይ አባቱ ከእግዚአብሔር አብና፣ ከባሕርይ ሕይወቱ መንፈስ ቅዱስ ጋር በአንድነት አውቀው ተረድተው ለስሙ እንዲገዙ አድርገዋል፡፡

ነቢዩ ኤርሚያስን ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔር ከእናቱ ሆድ ጀምሮ ለቅድስና ለክብር በነቢይነት እንደጠራው በመጻሕፋችን ተገልጦአል፡፡ /ኤር.1፥5/ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትም ለኢትዮጵያ ሰዎች ሐዋርያ ሆነው ያገለግሉ ዘንድ በባለቤቱ በመድኀኔዓለም በኢየሱስ ክርስቶስ አንደበት “እስመ ረሰይኩከ ሐዲስ ሐዋርያ፤ አዲስ ሐዋርያ አድርጌ ሾሜሃለሁ::” ተብሎ የተነገረላቸው ናቸው፡፡ በዚህም በጌታችን ቃል “በእኔ የሚያምን እኔ የምሠራውን ሥራ እርሱም ይሠራል ከዚያም የሚበልጥ ይሠራል” /ዮሐ.14፥12/ ተብሎ በተነገረው ቃል መሠረት፤ በሰው ሰውኛ ሊደረጉ የማይችሉ ታላላቅ ተአምራትን በመፈጸም ኢ-አማንያንን ወደ ሃይማኖት መልሰዋል፡፡ ተጋድሏቸውን የመዘገበው መጽሐፍ /ገድለ ተክለ ሃይማኖት/ እንደተመዘገበው በዛፍ ላይ አድሮ ሲያሰግዳቸውና ሲያስመልካቸው የነበረ ጋኔኑን አዋርደው እርሱን ከኢትዮጵያ ምድር አርቀው በአምልኮተ ባዕድ የነበሩ ሰዎችን ወደ ቤተ ክርስቲያን ኅብረት ቀላቅለዋል፡፡

ባለብዙ ገድል ጻድቁ ተክለ ሃይማኖት “ዳግማዊ ዮሐንስ” የሚል ስያሜ የተሰጣቸው ሐዋርያ ናቸው፡፡ ዮሐንስ መጥምቁ በተፀነሰ ጊዜ የአባቱን አንደበት የዘጋ፣ ሲወለድ ደግሞ የአባቱን አንደበት ዳግመኛ የከፈተ ነው፡፡ (ሉቃ.1፥62-66) "መምህር ወመገስጽ ዘኢያደሉ ለገድ" የተባለለት፥ ዮሐንስ መጥምቁ ንጉሥ ሔሮድስን ሳይፈራና ሳያፍር የገሰጸ እንደሆነ ሁሉ፤ አባታችን ተክለ ሃይማኖትም እንደ ሞቶሎሚ ያሉ ጣዖት አምላኪና አስመላኪ ነገሥታትና ኀያላንን ሳይፈራ የተጠራለትን አገልግሎት በጽኑ መታመን የፈጸመ ነው፡፡

ፈጣሪያችን ከጻድቁ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት በረከት ረድኤት ያሳትፈን፡፡ አሜን!!

 🙏🙏 👇👇👇🙏🙏💖💖በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ብርሃን የገለጸና የሰበከ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡የነቢያትን ትንቢት የፈጸመ፤የክርስቶስን ልደት ለድንግል ያበሰረ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ዳንኤ...
05/26/2021

🙏🙏
👇👇👇🙏🙏💖💖
በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ብርሃን የገለጸና የሰበከ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡
የነቢያትን ትንቢት የፈጸመ፤የክርስቶስን ልደት ለድንግል ያበሰረ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡
ዳንኤልን ከአናብስት ያዳነው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡
ሠለስቱ ደቂቅን ከእቶን እሳት ያዳነቸው ገብርኤል ነው፡፡
ወደ ዘካርያስ የተላከ የዮሐንስን ልደት ያበሰረ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡
ወደ ዮሴፍና ወደ ኒቆዲሞስ የተላከ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡
ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣን ከእቶን እሳት ያዳናቸው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡
ሰብአ ሰገልን በኮከብ ምልክት የመራቸው ይህ ገብርኤል ነው፡፡
ድንግል ማርያምና ሕፃኑን ክርስቶስን በምድረ በዳ በስደታቸው የመራ ይህ ገብርኤል ነው፡፡
የብርሃን ራስ ወርቅ የተቀዳጀ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡
የአሸናፊና የኃይል መልአክ ገብርኤል ነው፡፡
ነበልባላዊ ዖፈ ሰማይ ገብርኤል ነው፡፡
"የመልአኩ ጥበቃ እና ረድኤት አይለየን
ቅዱስ ገብርኤል ሆይ ስወስቱን ወጣቶች ከሚያቃጥል እሳት እንዳዳንካቸው እኛንም በዚህ አለም ከሚታየውና ከሚሰማው ክፉ ነገር አውጣን🙏🙏🙏♥♥

05/24/2021

Eastern Orthodox Church

05/24/2021

Send a message to learn more

በዓታ ለማርያምባዕታ ለማርያም በእለተ ቀኗ ከክፉ ነገር ሁሉ ትሰውራችሁ።እናታችን ቅድት ድንግል ማርያም ከአባቷ ከእያቀብና ከእናቷ ከሐና ሐምሌ 30 ራእይ አይተው ነሐሴ 7 በብስራተ መልአክ በ...
05/11/2021

በዓታ ለማርያም
ባዕታ ለማርያም በእለተ ቀኗ ከክፉ ነገር ሁሉ ትሰውራችሁ።
እናታችን ቅድት ድንግል ማርያም ከአባቷ ከእያቀብና ከእናቷ ከሐና ሐምሌ 30 ራእይ አይተው ነሐሴ 7 በብስራተ መልአክ በፈቃደ እግዚአብሔር እሑድ ተፀነሰች።
በእናቷ ማህፀን ሳለች ብዙ ታምራትን አድርጋለች የሞተውን ሳሚናስ ከሙት አስነስታዋለች።ይህም ሳሚናስ የጦሊቅ ልጅ ከኤዶቅ ካአጎቱ ቤት ሄዶ የሞተው ለቀብር ስወስዱት ከመንገድ ባሳረፉት ጊዜ ሐናም የአጎትዋ ልጅ ነበርና ለማልቀስ ብትደርስ ዘመዶቿ ሁሉ ተሰብስበው ሲላቀሱ እርሷም እየዞረች ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ብድግ ብሎ ተነሳቶ ስብሐት ለኪ እሙ ለፀሐይ ጽድቅ ማርያም ሆይ ለአብ ሙሽራው ለወልድ ወላድቱ ለመንፈስ ቅዱስ ጽርሐ ቤቱ ተፈስሒ ደስ ይበልሽ ብሎ ሰገደላት።
መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በእናቱ በኤልሳበጥ ማህፀን ሳለ ለእናታችን ማርያም እንደ ሰገደላት ሰላም ለኪ እንዳላት
{ ሉቃ.1፥41 } ይህም የሞተው ሳምናስ ከሞተበት ተነስቶ ሰገደላት።
☞ ይህንን ታምራት ስትሰራ በሐና ማህፀን 9 ወር ተቀመጠች። ግንቦት መባቻ ዕለት{ ግንቦት 1} ልባኖስ በምትባል አከባብ ተወለደች። በስምንተኛውም ቀን ስሟን "ማርያም" ብለው አወጡላት።
☞ እናታችን ማርያም በእናት አባቷ ቤት 3 ዓመት ተቀመጠች። መዝሙረኛው ዳዊት አባቷ በ{ መዝ 44፥10-11 }ላይ ልጄ ሆይ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ ንጉስ ውበትሽን ወድዶአልና እርሱ ጌታሽ ነውና እንዳለ እናታችን ቅድት ድንግል ማርያም በ3 ዓመቷ የስለት ልጅ ናትና በተመቅደስ ወስደው ለካህኑ ለዘካርያስ ሰጧት።
☞ ቀኑም የታህሳስ ባታ ነበር።መልአኩ ፋኑኤል ከሰማይበመሰቦ ወርቅ ህብስተ ሰማያዊ በብርሃን ጽዋ ስቴ ሕይወት ይዞ ረቦ ታያቸው።እመቤታችንንም በአንዱ ክንፍ ጋርዶ በአንዱ ክንፉም አጎናፅፎ ህብስቱን አብልቷት ወይኑን አጠጥቷት እመቤቴ ሆይ! መንገድ ባስመታሁሽ ማርኝ ብሎ የብርሃን መሶብ የብርሃን ጽዋ ይዞ ወደ ሰማይ አረገ።
☞እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም ሕብስተ ሰማያዊ እየተመገ በች ስቴ ሕይወት እየጠጣች ከንጹሓን ይልቅ ንጽሕት የሆንሽ አንቺ ነሽ ከማይነቅዝ ዕንጨት እንደ ተሰራ በወርቅ እንደ ተጌጠና ዋጋው ብዙ በሆነ በሚያበራ ዕንቁ እንደተለበጠ ታቦት በቤተ መቅደስ ውስጥ የኖርሽ የተመረጥሽ ድንግል ነሽ እንዳለ እትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ በአንቀጸ ብርሃን ቁጥር 6እንዲህ ሆና መላእክት ምግቧን እያመጡላት እየጎበኟት ከመላእክት ጋራ እየተጫወተች እየዘማረች 12 ዓመት በቤተ መቅደስ ተቀመጠች።
☞ የእናታችን የድንግል ማርያም ምልጃ ጸሎት በረከት እረድኤት ከእኛ ከቃልኪዳን ልጆቿ እንዲሁ የአስራት ሃገሯ ከሆነች ከእትዮጵያ ዘወትር አይለያት አይለየን አሜን።

††† እንኳን ለጌታችንና አምላካችን መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ዓመታዊ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!...
04/30/2021

††† እንኳን ለጌታችንና አምላካችን መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ዓመታዊ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† መድኃኔ ዓለም †††

††† ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ለእኛ ሲል በፈጸመው የማዳን ሥራ በዚሕ ዕለት ክፉዎች አይሁድ ከምሽቱ 3:00 ጌቴሴማኒ ውስጥ ያዙት::
ሙሉውን ሌሊት ከቀያፋ ወደ ሐና: ከሐና ወደ ቀያፋ ሲያመላልሱት: አስረው ሲደበድቡት አድረዋል::

*ዝም ቢላቸው ዓይኑን ሸፍነው በጥፊ መቱት:: ምራቃቸውን ተፉበት:: ዘበቱበት:: ራሱንም በዘንግ መቱት:: እርሱ ግን ሁሉን ታገሰ::

*በጧት ከገዢው ዘንድ ሞት እንዲፈረድበት አቀረቡት:: በሠለስት (ሦስት ሰዓት ላይ) አካሉ እስኪያልቅ እየተዘባበቱ 6,666 ገረፉት:: ሊቶስጥሮስ አደባባይ ላይ እርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት::

*ስድስት ሰዓት ላይ በረዣዥም ብረቶች አምስት ቦታ ላይ ቸንክረው ሰቀሉት:: ሰባት ታላላቅ ተአምራት በምድርና በሰማይ ታዩ::
ዓለም በጨለማ ሳለች ጌታ በመስቀል ላይ ሰባት ቃላትን ተናገረ::

*ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ በባሕርይ ሥልጣኑ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ:: በዚያች ሰዓትም ወደ ሲዖል ወርዶ የታሠሩትን ሁሉ ፈታ:: አሥራ አንድ ሰዓት ላይ ደጋጉ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር በአዲስ መቃብር ቀበሩት::

*በዚያች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተቃጠለ:: ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍፁም ለቅሶን አለቀሰ:: ቅዱሳት አንስት በዋይታ ዋሉ:: (ማቴ. 27:1, ማር. 15:1, ሉቃ. 23:1, ዮሐ. 19:1)

††† ለእኛ ለኀጥአን ፍጡሮቹ ሲል ይህንን ሁሉ መከራ የታገሰ አምላክ ስለ አሥራ ሦስቱ ኅማማቱ: አምስቱ ቅንዋቱ: ስለ ቅዱስ መስቀሉ: ስለ ድንግል እናቱ ለቅሶና ስለ ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስ ብሎ ይማረን::

††† መድኃኔ ዓለም ከወዳጆቹም ጸጋ ክብርን ያድለን::

††† "የተጠራችሁለት ለዚህ ነው:: ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሏልና:: እርሱም ኃጢአት አላደረገም:: ተንኮልም በአፉ አልተገኘበትም:: ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም:: መከራንም ሲቀበል አልዛተም . . . እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ::" †††
(፩ጴጥ. ፪፥፳፩-፳፭)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

Address

Reston, VA
20190

Telephone

+15713321720

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mella posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share