Ancient Orthodox/ጥንታዊቷ ኦርቶዶክስ

Ancient Orthodox/ጥንታዊቷ ኦርቶዶክስ ይህ Ancient Orthodox/ጥንታዊቷ ኦርቶዶክስ ፔጅ ነው ✅ Follow ✅share ✅Like በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ
(1)

ግንቦት 1/2018                                👉በስመ   አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን   በከበረዉ  #ትንሣኤው ለምናከብርበት ለእናታችን   አመታዊ የልደ...
05/08/2026

ግንቦት 1/2018


👉በስመ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን በከበረዉ #ትንሣኤው ለምናከብርበት ለእናታችን አመታዊ የልደት መታሠቢያዋ ክብረ በዐል እንዲሁም አመታዊ መታሠቢያ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን

" ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም"

👉ጴጥርቃ እና ቴክታ የሚባሉ ሰዎች #በኢየሩሳሌም በአንድነት ተጋብተው ይኖሩ ነበር

👉እነዚህም #በእግዚአብሔር የሚያምኑ የተወደዱ ጻድቃን ደግ ሰዎች ነበሩ እነዚህም ሰዎች በእግዚአብሔርም በሰውም ዘንድ ባለፀጎች ነበሩ ነገር ግን ሐብታቸዉን የሚወርሳቸው ልጅ አልነበራቸውም መካን ነበሩ አንድ ቀን ጴጥርቃም ቴክታን እህቴ ሆይ ይህን ሁሉ የሰበሰብነውን ገንዘባችንን ምን እናደርገዋለን ልጅ የለን የሚወርሰን

👉 አንቺም መካን ነሽ እኔም ካንቺ በቀር ሌላ ሴት አላውቅም አላት እርሱአም ወንድሜ ሆይ ለኔ ልጅ ቢነሳኝ አንተም እንደኔው ሆነህ ትቀራለህን ከሌላ ደርሰህ ውለድ እንጂ ብላ ብታሰናብተው እንደዚ ያለ ነገር እንኩአንስ ላደርገው በልቦናዬ እንዳላስበው ያውቅብኛል አላት

👉እርሱዋም የሚያደርገውን የሚያውቅ የለም ትላንትና ማታ በህልሜ ነጭ ጥጃ ከማህፀኔ ስትወጣ ያችም ነጭ ጥጃ ሌላ ነጭ ጥጃ ስትወልድ እንዲሁ እስከ 7ት ትውልድ ሲዋለድ ሰባተኛይቱ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃዋም ፀሃይን ስትወልድ አየሁ አለችው

👉እርሱም በጠዋት ከህልም ፈቺ ዘንድ ሂዶ የነገረችውን ሁሉ ነገረው ያም ህልም ፈቺ #እግዚአብሔር በምህረቱ አይቱአቹሀል በሳህሉ መግቡአችሁአል 7 አንስት ጥጆች መውለዳቹ 7 ሴቶች ልጆች እና የልጅ ልጆች ትወልዳላቹ ከቤታቹ ሰባተኛይቱ ጨረቃ መውለዱአ ከሰው የበለጠች #ከመላእክትም የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላቹ የፀሃይ ነገር ግን አልታወቀኝም አለው

👉እርሱም የነገረውን ሁሉ ሄዶ ነገራት እርሷም እንጃ አምላከ #እስራኤል የሚያደርገውን ማን ያውቃል ብላ ዝም አለች

👉ከዛም ፀንሳ በ9 ወሯ ሴት ልጅ ወለደች ስሙአንም ሄሜን ብለው አወጡላት ሔሜንም አድጋ ለአካለ መጠን ስደርስ አጋብተዋት በስምንተኛ ቀኑአም ደርዲ ብለው ስም አወጡላት

👉ደርዲም አድጋ እንዲሁ ሴት ወለደች እና ቶና አለቻት ቶናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሲካር አለቻት ሲካርም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሴትና አለቻት ሴትናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሄርሜላ አለቻት ሄርሜላም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ንጽህት ቅድስት ክብርት የምትሆን #እመቤታችንን የምትወልደውን #ሃናን ወለደች

👉ከጴጥርቃና ከቴክታ የተወለዱ 67 ወንዶች ልጆች አሉ ትውልድ ለመቁጠር ትንቢት አልተነገረላቸውም ሱባኤ አልተቆጠረላቸውምና አልተፃፈም ይህቺም ሃና በስርአት በቅጣት አደገች ለአእምሮ ስትበቃ አካለ መጠን ስደርስ ከቤተ መንግስት ወገን ከነቅዱስ ዳዊት ወገን ከሆነው(መጽሃፍ ቅዱስ ይገልጸዋል) ከቅዱስ እያቄም ጋር አጋቡአት

👉 እነዚህ ቅዱሳን #እያቄም እና #ሃና በአንድነት ተጋብተው ሲኖሩ ልጅ አጡ ከእለታት አንድ ቀን ወደ ቤተ እግዚአብሄር ሂደው ሲፀልዩ ሲያዝኑ ዋሉ












ሚያዚያ 2/2018                                                            የማይሞት እርሱ ሞተ ሞትን ይሽረዉ ዘንድ ሞተ                     ...
04/10/2026

ሚያዚያ 2/2018


የማይሞት እርሱ ሞተ ሞትን ይሽረዉ ዘንድ ሞተ
ሙታንን ያድናቸዉ ዘንድ ሞተ

👉የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን #የክርስቶስ ሕማምና መከራውን ለማሰብ ከሆሳዕና ሰንበት ጀምሮ እስከ ትንሳኤ ያለውን ሳምንት ብላ ትጠራዋለች በእዚህ ሳምንት ውስጥ ያሉ ቀናት ሁሉ እያንዳንዳቸው የተለያየ ምስጢር ተፈፅሞባቸዋል ዕለተ አርብ ግን የሁሉ ነገር መገባደጃ ጌታችን አምላካችን ነገረ ድህነቱን የፈፀመበት በመሆኑ ይለያል

👉ቤተክርስቲያንም በዓል አድርጋ አይሁድ ያደረሱበትን ስቃይ ፣ መገረፍና መመታቱን ፣ መቸንከርና መሰቀሉን ፣ ፈጣሪ ሆኖ ሳለ እያሰበች በልዩ ሥርዓት ታከብረዋለች

👉ይህ ይባላል ምዕመናን ይህን በዓል እንደሌላው ጊዜ በመብል በመጠጥ ሳይሆን በፆምና በስግደት ያከብሩታል የበረቱት ከሌሊት ጀምሮ የዘገዩም ከእኩለ ቀን በፊት ባሉት ሰዓታት ቀድመው በየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ይሰባሰባሉ

👉በዚህች ዕለት በቤተ መቅደስ ውስጥ በምሳሌና በምስጢር የተዋበ ሥርዓት ይከናወናል አገልግሎቱን የሚመሩት ካህናትና ዲያቆናት ከተገኘ ሐዘን ነውና የመቅደሱ (የቅድስተ ቅዱሳኑ) መጋረጃም እንዲሁ ይለብስና ይዘጋል ከፊቱም እንደ አልጋ ያለ ነገር መጎናፀፊያ ተነጥፎበት ይዘጋጅና በላዩ ላይ ቅዱስ ወንጌል ፣ ጻሕልና ጽዋዎች ይቀመጣሉ

👉የሞቱ ምሳሌ የሆነ በዚያው ላይ ይዘረጋል በራስጌና በግርጌውም የወርቅ ለምድ ይደረጋል ከእነዚህ ሁሉ ንዋያተ ቅዱሳት ጋር ሦስት የመፆር መስቀሎችም እንዲሁ በመካከል ፣ በቀኝና በግራ አብረው ይቆማሉ በመካከለኛው መስቀል ላይ ይደረግበታል

👉ከዚሁ ጎንና ጎን ደግሞ በገመድ እየሳቡ የሚያጥኑባቸው ፅንሐዎች በተዘጋው የመቅደስ መጋረጃ ላይ በገመድ ታስረው ይሰቀላሉ ይህም ጌታችን በሰቃዮቹ አይሁድ እጁ በገመድ ታስሮ ወደፊትና ወደኋላ እየተጎተተ መንገላታቱን ለማሳየት ነው ይህ ሁሉ በአምላካችን ላይ የሆነውን ለማሰብ ነው

👉ምንባባቱ ፣ በዕዝል የሚዜመው ዜማ በየሰዓቱ የሚደረገው እያንዳንዱ ክንውን ሲታከልበት ደግሞ ይህች ቤተ ክርስቲያን ምን ያህል መሆኗን ፤ ይህ ሁሉ የሚከወንባት ዕለተ እንደሆነች እንረዳለን

👉እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሣኤሁ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም "አሜን ኪራላይሶን"

















❗️እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም❗️ የቃል ኪዳን ልጆችሽንና የአሥራት ሀገርሽን ኢትዮጵያን ታደጊ! አሜን!!እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይሀገራችን ኢትዮጵያ ሰላም እና ፍቅ...
03/30/2026

❗️እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም❗️


የቃል ኪዳን ልጆችሽንና የአሥራት ሀገርሽን ኢትዮጵያን ታደጊ! አሜን!!

እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ

ሀገራችን ኢትዮጵያ ሰላም እና ፍቅር አንድነትን ይሰጠን ዘንድ ከልጅሽ ከወዳጅሽ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ለምኝልን አሜን አሜን አሜን🙏❤

🚸🚸🚸

እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ወርኃዊ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!!ዛሬ መጋቢት 19/7/2018 ዓ.ም ወርኀዊው በዓለ ገብርኤልን አስመልክቶ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ስ/ወንጌልና ሐ...
03/28/2026

እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ወርኃዊ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!!

ዛሬ መጋቢት 19/7/2018 ዓ.ም ወርኀዊው በዓለ ገብርኤልን አስመልክቶ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ስ/ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ ዋና ክፍል ያዘጋጀው “ዐውደ ወንጌል ዘተዋሕዶ” ዛሬ ማታና ነገ ማታ በሠርኩ ክፍለ ሰዓት በልዩ ድምቀት ይከናወናል። ጥናታዊ ጽሑፍም ይቀርባል። ሁላችንም በሰዓቱ እንገኝ ዘንድ ቤተ ክርስቲያን ትጣራለች።

🥀 ገብርኤል መልአከ ራማ 🥀ገብርኤል መልአከ ራማ (2)ስንጠራህ ፈጥነህ ድረስ ድምጽህን እንስማ ትንቢቱ ሲፈጸም ዘመኑ ሲያበቃከቀናት ሳትዘገይ ሳይጎድል ደቂቃወደ ድንግል መጥተህ ደስታን አበሰር...
03/27/2026

🥀 ገብርኤል መልአከ ራማ 🥀

ገብርኤል መልአከ ራማ (2)
ስንጠራህ ፈጥነህ ድረስ ድምጽህን እንስማ


ትንቢቱ ሲፈጸም ዘመኑ ሲያበቃ
ከቀናት ሳትዘገይ ሳይጎድል ደቂቃ
ወደ ድንግል መጥተህ ደስታን አበሰርክ
የአምላክን ሰውን መሆን ለዓለሙ ሰበክ(2)

ከውኃ እና ከእሳት ከሞት አመለጡ
በእሳቱ መካከል ለጥፋት ቢሰጡ
አንተ ባለህበት በየትኛውም ስፍራ
ምንም ቦታ የለው ሞትና መከራ (2)

አዝ።።።።።።።
የመንገዴ መሪ ፈውስ ነህ ለህመሜ
ገብርኤል ስትመጣ በዛልኝ ሰላሜ
ደስታን አብሳሪ ተሸክመህ ዜና
ዛሬም ለአገራችን ምስራች ይዘህ ና(2)

አዝ።።።።።።

አንጌቤናይቱ ቅድስት ኢየሉጣ
ስለአንተ ትመስክር እስከ ልጇ ትምጣ
እሳት ነህ ገብርኤል ነባልባልባ አስወጋጅ
የአምላክ መወለድ ለዓለም ምታውጅ(2)

❣️ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ❣️

 #ቅደሚልኝ ከፊት ጉዞዬ እንዲቀናያላንቺ ጎዳናው አይገፋምናእጠብቅሻለሁ በመጠበቂያዬመመኪያዬ ድንግል አንቺ ነሽ ተስፋዬ ኪዳንሽ ነው መበርቻዬ ፀሎትሽ ነው መደገፊያዬሞገሴ ነሽ መድመቂያዬአርማዬ...
03/24/2026

#ቅደሚልኝ ከፊት ጉዞዬ እንዲቀና
ያላንቺ ጎዳናው አይገፋምና
እጠብቅሻለሁ በመጠበቂያዬ
መመኪያዬ ድንግል
አንቺ ነሽ ተስፋዬ
ኪዳንሽ ነው መበርቻዬ
ፀሎትሽ ነው መደገፊያዬ
ሞገሴ ነሽ መድመቂያዬ
አርማዬ ነሽ መለያዬ
#ኪዳነምህረት

መጋቢት 12/2018                                           መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ በፊቱ ተጠንቀቁ          ቃሉኑም አድምጡ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት...
03/21/2026

መጋቢት 12/2018


መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ በፊቱ ተጠንቀቁ
ቃሉኑም አድምጡ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት
ብትሰሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት ዘፀ.23፥21-22

👉በስመ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን በፆምና በፀሎት ለምንማፀንበት ለመልአኩ ወርሐዊ መታሠቢያ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን

👉መጋቢት ዐሥራ ሁለት በዚች ዕለት #እግዚአብሔር ቅዱስ #ሚካኤልን ወደ ጠንቋዩ በለዓም ላከው

👉 ተጓዙ በኢያሪኮ ፊት ለፊት በዮርዳኖስ ማዶ ባለው በሞዓብ ሜዳ ሰፈሩ የሴፎር ልጅ ባላቅ እስራኤል በአሞራውያን ላይ ያደረገውን ሁሉ አየ ብዙም ነበረና ሞዓብ ከሕዝቡ እጅግ ፈራ ከእስራኤልም ልጆች የተነሣ ሞዓብ ደነገጠ ሞዓብም የምድያምን ሽማግሌዎች በሬ የለመለመውን ሣር እንደሚጨርስ ይህ ጭፍራ በዙሪያችን ያለውን ሁሉ ይጨርሳል አላቸው በዚያን ጊዜም የሴፎር ልጅ ባላቅ የሞዓብ ንጉሥ ነበረ

👉በወንዙ አጠገብ ባለችው በሕዝቡ ልጆች ምድር በፋቱራ ወደ ተቀመጠው ወደ ቢዖር ልጅ ወደ በለዓም እነሆ ከግብፅ የወጣ ሕዝብ አለ እነሆም በአቅራቢያችንም ተቀምጦአል አሁንም ይህ ሕዝብ ከእኔ ይበልጣልና ልወጋቸውና ከምድሪቱ ላሳድዳቸው እችል እንደ ሆነ እባክህ ና ርገምልኝ አንተ የመረቅኸው ምሩቅ የረገምኸውም ርጉም እንደ ሆነ አውቃለሁና ብሎ ይጠሩት ዘንድ መልእክተኞቹን ላከ

👉የሞዓብ ሽማግሌዎችና የምድያም ሽማግሌዎችም የምዋርቱን ዋጋ በእጃቸው ይዘው ሄዱ ወደ በለዓምም መጡ የባላቅንም ቃል ነገሩት እርሱም ዛሬ ሌሊት በዚህ እደሩ #እግዚአብሔርም እንደሚነግረኝ እመልስላችኋለሁ አላቸው የሞዓብም አለቆች በበለዓም ዘንድ ተቀመጡ እግዚአብሔርም ወደ በለዓም መጥቶ እነዚህ በአንተ ዘንድ ያሉ ሰዎች እነማን ናቸው አለው

👉በለዓምም #እግዚአብሔርን የሞዓብ ንጉሥ የሴፎር ልጅ ባላቅ እነሆ ከግብፅ የወጣ ሕዝብ የምድርን ፊት ሸፈነ አሁንም ና እርሱንም ርገምልኝ ምናልባት እወጋው አሳድደውም ዘንድ እችል እንደ ሆነ ብሎ ወደ እኔ ልኮአል አለው #እግዚአብሔርም በለዓምን ከእነርሱ ጋር አትሂድ የተባረከ ነውና ሕዝቡን አትረግምም አለዉ በለዓምም ሲነጋ ተነሥቶ የባላቅን አለቆች ከእናንተ ጋር እሄድ ዘንድ #እግዚአብሔር አልፈቀደምና ወደ ምድራችሁ ሂዱ አላቸው

👉የሞዓብ አለቆች ተነሡ ወደ ባላቅም መጥተው በለዓም ከእኛ ጋር ይመጣ ዘንድ አልፈቀደም አሉት ባላቅም ደግሞ ከፊተኞች የበዙና የከበሩ ሌሎችን አለቆች ሰደደ ወደ በለዓምም መጥተው የሴፎር ልጅ ባላቅ ክብርህን እጅግ ታላቅ አደርገዋለሁና የተናገርኸውንም ሁሉ አደርግልሃለሁና እባክህ ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ ምንም አይከልክልህ እባክህ ና ይህን ሕዝብ ርገምልኝ አለ ብለው ነገሩት

👉በለዓምም መልሶ የባላቅን ባሪያዎች ባላቅ በቤቱ የሞላውን ወርቅና ብር ቢሰጠኝ በትንሹ ወይም በትልቁ ቢሆን የአምላኬን #የእግዚአብሔርን ቃል እተላለፍ ዘንድ አይቻለኝም አሁንም እግዚአብሔር ደግሞ የሚነግረኝን አውቅ ዘንድ እባካችሁ ዛሬ ሌሊት ደግሞ በዚህ እደሩ አላቸው #እግዚአብሔርም ወደ በለዓም በሌሊት መጥቶ ሰዎቹ ይጠሩህ ዘንድ መጥተው እንደ ሆነ ተነሣ ከእነርሱም ጋር ሂድ ነገር ግን የምነግርህን ቃል ብቻ ታደርጋለህ አለው

👉በለዓምም ሲነጋ ተነሣ አህያይቱንም ጭኖ ከሞዓብ አለቆች ጋር ሄደ እርሱም ስለ ሄደ እግዚአብሔር ተቆጣ የእግዚአብሔርም መልአክ ሊቋቋመው በመንገድ ላይ ቆመ

Address

New York, NY

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ancient Orthodox/ጥንታዊቷ ኦርቶዶክስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share