Debre Sahel Medhanie Alem EOTC Kansas City

Debre Sahel Medhanie Alem EOTC Kansas City Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Debre Sahel Medhanie Alem EOTC Kansas City, Church, Kansas City, KS.

Debre Sahel Medhanie Alem Ethiopian Orthodox Tewahedo Church strives to fulfill the spiritual needs of its members by providing church services in a manner consistent with the Ethiopian Orthodox Tewahedo church’s faith, values and tradition.

06/01/2026

የደስታ መንፈስ

የተወደደው መምህራችን ቅዱስ ጳውሎስ ከነገረን የመንፈስ ፍሬዎች አንዱ የደስታ መንፈስ ነው።

የሰዎች ደስታ ምክንያቱ ብዙ ነው፤ ባለጠጋ በሀብቱ ብዛት፣ ንጉሥ በግዛቱ ስፋት፣ ሊቅ በዕውቀቱ፣ ገበሬ በምርቱ፣ ወታደር በጀግንነቱ ጎልማሳ በሚስቱ ደስ እየተሰኘ ይኖራል።

ከእነዚህ ሁሉ የሚሻለውና የሚበልጠው የመንፈስ ቅዱስ ደስታ ነው።
ሌሎቹ ከላይ የዘረዘርናቸውም ሆነ ያልዘረዘርናቸው ከአንዱ ተነሥተው ለሌላ የሚሰጡ ናቸው። የባለጠጎች ሀብት ደስታን የሚያመጣው ከሌሎቹ በልጦ ሲታይ ነው፤ የንጉሥም ግዛት የሚሰፋው የሌሎችን በማጥበብ ነው። የወታደርም ጀግንነት ለደስታ የሚያበቃው ሌላውን ድል በመንሣት በሞት ወይም በስደት መቅጣት ሲያስችል ነው።

ከእግዚአብሔር እጅ የምንቀበለው የመንፈስ ቅዱስ ደስታ ግን ከአንዱ ሳይነጠቅ ለሁሉም እኩል የሚሰጥ በመሆኑ ልዩ የደስታ ምንጭ ያደርገዋል።

ለዚህ ነው ቅዱስ መጽሐፍ “በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው” ብሎ የተናገረው። በአንድ ጊዜ የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ ሁሉም ተቀበሉ።

ለሚመለከቷቸው ሰዎች ጉሽ የወይን ጠጅ ጠጥተው የጠገቡ የቤተ መንግሥት ብላቴኖች ይመስሉ ነበር፤ የሰዎችም ግምት እንዲሁ ነበር። እነሱን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ከወይን ጠጅ ይልቅ የሚያስደስት እንደሆነ ማን በነገራቸው?

ለእነዚህ ሰዎች ሐዋርያት የተቀበሉትን ታላቁን ጸጋ ማን በገለጠላቸው? የመንፈስ ቅዱስን ደስታ በወይን ጠጅ ስካር ከሚገኝ ደስታ ጋር ማነጻጸራቸው ሌላ ባያውቁ ነውና።

እግዚአብሔር ሰው ከሚያውቀው በላይ የሆነ ደስታን ለሰው ማምጣት ይችላል። ጥቂት ጊዜ ዝም ቢሉ ኖሮ የስህተት ንግግር ሳይናገሩ የሐዋርያትን የደስታ ምክንያት ማወቅ በቻሉ ነበር እነሱ ግን መታገስ አልተቻላቸውምና ሳይጠይቋቸው በልባቸው ያሰቡትን ሁሉ ተናገሩባቸው።

ቅዱስ ጴጥሮስ “ለእናንተ እንደመሰላችሁ እነዚህ የሰከሩ አይደሉም ከቀኑ ሦስተኛ ሰዓት ነውና” ሥራ. 2፥15 ብሎ የስህተት ንግግራቸውን የንግግር መጀመሪያ አድርጎ ወንጌል መስበክ ጀመረ። የወንግጌል ዓላማ በተሳሳተ የሕይወት መስመር የሚነጉደውን ሕዝብ መመለስ ነውና ከስህተታቸው እንዲመለሱ አጥብቆ መከራቸው።

ሐዋርያት የተቀበሉት ጸጋ ሰዎችን በማዳን ወደ ሚበልጠው ደስታ እንዲሸጋገሩ የሚያደርግ ነውና ጴጥሮስ አስራ አንዱን ጓደኞቹን አስከትሎ ለሰዎች የሚድኑበትን ቃል ነገራቸው።

በእሳት አምሳል ወርዶ ሐዋርያትን ደስ ያሰኛቸው መንፈስ ቅዱስ በዚያ የተሰበሰቡትን ሕዝቡን በቃሉ ደስ ያሰኛቸው ጀመር።
በቋንቋቸው ሲናገሩ ቢሰሟቸው በጥቂቱ ደስ አላቸው፤ ከነቢያት ቃል ጠቅሰው በነገሯቸው ጊዜ ደግሞ ደስታ ተጨመረላቸው።

መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው ደስ የተሰኙ ሐዋርያት በዚያው ቀን ለሦስት ሺህ ሰዎች የደስታ ምክንያት ሆኑ። መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው እንዲህ ነው ለሰዎች የደስታ እንጂ የኃዘን ምክንያት መሆን አይችልም።

መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው ብቻዬን ይድላኝ አይልም። መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው አንድ ጊዜ ተናግሮ የሰሙትን ሰዎች ሁሉ ተከታዮቹ ማድረግ ይችላል። ምክንያቱም የሚናገረው የማይለወጠውን እውነት ስለሆነ ነው።

መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው የሚሰሙትን ሰዎች ወደ እግዚአብሔር ሳያደርሳቸው ከክርስቶስ ጋር ሳያገናኛቸው አይተዋቸውምና እነዚህን ሰዎች “በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ” አላቸው።

በዓል ለማክበር የተሰሰቡ ለመንፈሳዊ አገልግሎት የሚፋጠኑ በኦሪት በነቢያት የሚያምኑ ቢሆኑም በዚህ ሁሉ አገልግሎታቸው ለኃጢአት ሥርየት የሚያበቃ ምንም አይነት አገልግሎት አልነበራቸውም። የኃጢአት ሥርዬት የማያሰጥ አገልግሎት እየደጋገሙ ሲያከናውኑ መኖር እንዴት የሚያሳዝን ነው።

ከዚህ የድግግሞሽ ከኃጢአት ነጻ የማያወጣ ሥነ ሥርዓት ነጻ ሊያወጣቸው ቅዱስ ጴጥሮስ መስበክ ጀመረ። ደስታቸውን ቃሉን በመስማት ይጀምራሉ፤ ቃሉን በመፈጸም ደስታቸውን ፍጹም ያደርጋሉ።
ቅዱሳን ሐዋርያት ደስታቸው ፍጹም የሚሆነው ሰዎችን ወደ ክርስቶስ በማቅረብ ነው፤ የሰዎችም ደስታ የሚጀምረው ከክርስቶስ ጋር በመገናኘታቸው ነው።

ለሚድኑትም ለሚያድኗቸውም የደስታ ቀን ነበር - በዓለ ሃምሳ። ይህ ደስታቸው ወደ ጾምና ጸሎት ፊታቸውን ዘወር እንዲያደርጉ አድርጓቸዋል። በመጀመሪያ በጸሎት ሲተጉ ሳሉ አገኛቸው ሥራ. 1፥14፤ ክዚያ በኋላ ደግሞ በጦምና በጸሎት ሲያመልኩት ተገለጠላቸው ሥራ. 13፥1-2 መንፈስ ቅዱስን የተቀበለ ሰው አገልግሎቱ እየሰፋ ይሄዳል እንጂ አይቀንስም። ነፍሳችን የመንፈስ ቅዱስን ደስታ የምትካፈለው አገልግሎት በጨመርን ቁጥር ነውና።

ሐዋርያት ለአገልግሎታቸው መጀመሪያና መንፈስ ቅዱስንም ተቀብለው ደስ ቢላቸው በታላቅ ደስታ ጀመሩትን ይህንን ታላቅ ጾም ስንጾም ለመንፈሳዊ አገልግሎታችን መከናወን ምክንያት የሚሆነንን የመንፈስ ቅዱስን ረድ ኤት እናገኛለን።

እንደ ሐዋርያትም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የሆነውን የመንፈስ ደስታን እንቀበላለንና በፍጹም ልባችን ደስ እያለን ልንጾም ይገባናል።

እንኳን አደረሳችሁ።
ሰይጣንን ድል የምንነሣበት ጾም ያድርግልን።
©️ ስምዓኮነ መልአከ / Simakone Melak

የእሁድ ሥርዓተ አምልኮችንን በዩቲዩብ ላይ ብቻ እያሰራጨን ነው። እባክዎን እዚያው ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ። የዥረቶቻችንን እና የቪዲዮዎቻችንን ማሳወቂያዎች ለማግኘት የደወል ምልክቱን ...
05/31/2026

የእሁድ ሥርዓተ አምልኮችንን በዩቲዩብ ላይ ብቻ እያሰራጨን ነው። እባክዎን እዚያው ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ። የዥረቶቻችንን እና የቪዲዮዎቻችንን ማሳወቂያዎች ለማግኘት የደወል ምልክቱን ጠቅ ያድርጉ።

We are broadcasting our Sunday Liturgy ONLY on YouTube now. Please subscribe to our channel there. Click the bell icon to get notifications of our streams and videos.

መድሀኒአለም | Divine Liturgy | Amharic - 31st May 2026Medhane Alem (መድሀኒአለም) Ethiopian Orthodox Tewahedo Church of Kansas City, Kansas USA

05/10/2026

Sunday Service English 10 May 2026

05/03/2026

Sunday Service 3 May 2026

05/03/2026

ወረብ
ትዌድሶ

05/03/2026

ክርስቶስ ተንሥአ ሙታን

ደስ አላት ቤተክርስቲያን በጣም ደስ አላትሙሽራው ሙሽሪት ልጆቿ በቅዱስ ቁርባኑ ተዋህዱላት።
05/02/2026

ደስ አላት ቤተክርስቲያን በጣም ደስ አላት
ሙሽራው ሙሽሪት ልጆቿ በቅዱስ ቁርባኑ ተዋህዱላት።

All glory and honor be to God:Today, our hearts rejoice as we witnessed a beautiful Holy Matrimony in the sacred house o...
05/02/2026

All glory and honor be to God:

Today, our hearts rejoice as we witnessed a beautiful Holy Matrimony in the sacred house of God:
Through the grace of Christ, Aberham and Lidia have been united not only in love, but in faith, commitment, and divine purpose:

As it is written in the Holy Scripture, “What God has joined together, let no one separate.” — The Holy Bible:

Marriage in the Orthodox Church is not just a union of two people, but a sacred covenant where Christ is at the center:

May the Lord bless their journey together, strengthen them in times of trial, and fill their home with peace, joy, and unshakable faith:

May their love reflect Christ’s love for His Church, growing deeper each day in patience, forgiveness, and grace:

Let us keep Aberham and Lidia( ብሥራት ገብርኤል ና አፀደ ማርያም )in our prayers as they begin this holy journey together:

May God bless this union abundantly, and may their love be a light to the world:

04/26/2026

Sunday Service 26 April 2026

04/19/2026

Holy Liturgy - 19th April 2026

Medhane Alem (መድሀኒአለም) Ethiopian Orthodox Tewahedo Church of Kansas City, Kansas USA

Address

Kansas City, KS

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Sahel Medhanie Alem EOTC Kansas City posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Debre Sahel Medhanie Alem EOTC Kansas City:

Featured

Share

Category