Hamere Berhan St Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery

Hamere Berhan St Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Hamere Berhan St Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery, Elkwood, VA.

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

“ከዱሮ ዘመን የፈረሱት ስፍራዎች ይሠራሉ፥ የብዙ ትውልድም መሠረት ይታነጻል፤ አንተም፦ ሰባራውን ጠጋኝ፥ የመኖሪያ መንገድን አዳሽ ትባላለህ።” (ኢሳ 58፥12)
ሐመረ ብርሃን ቅዱስ አባ ሳሙኤል ገዳም እንዴትና ለምን ተመሠረተ?
የሐመረ ብርሃን ቅዱስ አባ ሳሙኤል ገዳም አጀማመሩ በሰሜን አሜሪካን ተወልደው ወይም በልጅነታቸው መጥተው ያደጉ ወጣቶች “አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር” (2ኛ ጢሞ 3፥14) እንደተባለ እግዚአብሔርን አውቀው በእግዚአብሔር ፍቅር መኖር እንዲችሉ በተከፈተላቸው የሐሙስ የሰርክ ጉባኤ መነሻነት ነው።
እንዲሁም እነዚህን

ብቻ ሳይሆን ትምህርት ቤቱን አሳድጎ መጪውን ትውልድ በትምህርት እየኮተኮቱ በእግዚአብሔር ቤት ለማሳደግ ከተማሩም በኋላ ከራሳቸው አልፈው ተርፈው ወደ አገግሎቱ የሚገቡ ወጣቶች የሚቀርቡበትን መንገድ ማበጀት አስፈላጊም ስለሆነ ይህንና የመሳሰሉትን ሃሳቦች ታሳቢ በማድረግ ለትምህርትና መንፈሳዊውን ሕይወት መለማመጃ የሚሆን ገዳም የግድ አስፈልጓል።
ዛሬ ላይ ሆነን ለመጪው ትውልድ ታአሪክና ሃይማኖቱን እንዲወርስና እንዲያስቀጥል አስተካክለን አዘጋጅተን ካላስረከብነው ማንነቱ ሊጠፋበት ስለሚችል ይህን የሚሠራ ገዳምና ማሰልጠኛ አስፈልጓል።
መቼ ተመሠረተ?
ይህ ገዳም በልዩ ልዩ ምክንያቶች በጽንሰ ሃሳብ ደረጃ ቆየት ያለ ቢሆንም እንቅስቃሴው ወደመተግበር የተጀመረው ግን ወደ ስምንት ዓመት ይሆነዋል። የተለያዩ እናቶችና አባቶች ወደሌሎች እንደካቶሊክ የግብፃውያን የሆኑ ገዳማት እየሄዱ የሁለት የሦስት ቀን እረፍት አድርገው ሲመለሱና ሲነግሩን የራስ ቦታ ቢገኝ ደግሞ የሚያሰኝ እቅድ እንዲፈጠር ከእለ ከተጠቀሰው ሃሳብ ጋር ከመነጫው መካከል አንዱ ምክንያትምና ለሃሳቡ መነሻም ሆኖአል። በተጨማሪም መነኮሳት አባቶች በአግልግሎትም ይሁን በሆነው ምክንያት ሃገርቤት ካልሄዱ በስተቀር በከፋቸው ግዜ እንኳን የእረፍት ግዜና ቦታ ባለመኖሩ ብዞዎቹ ተጎድተዋል።ለአሳ ሕይወቱ በባሕር መገኘት እንደሆነ ሁሉ ለመንኩሴም ሕይወቱ ገዳም ነውና።
ከላይ እንደተገለጸው ወጣቶችም ቢሆኑ ለመንፈሳዊ አገግሎት እራሳቸውን ቢሰጡ ወደሃገር ቤት ለመንፈሳዊው ትምህርት ሲሄዱ ስለሚከብዳቸው ወደኋላ እንዳይሉ ገዳሙ የምናኔ ቦታ ብቻ ሳይሆን ትምህርት ቤትም ጭምር እንዲሆን ታቅዶ ነው መመሥረት ያስፈለገው። ከላይ በተጠቀሰው ዓመት ታስቦ እቅስቃሴው በዚህ ሃገር ያሉትን የገዳማት እንቅስቃሴን መቃኘት ተጀምሮ ፈቃድ የማግኘት ሂደቱ ቀጥሎ በዲሤምበር 2015 የመጀመሪያው ፈቃድ ከአሜሪካን መንግሥት ተገኝቷል።

የገዳሙ እውቅናና ሕጋዊነት
ይህ ገዳም የሀገሪቱ ለሃይማኖት የተሰተው ሕግ በሚያዝዘው መሠረት ከኮመንዌልዝ ኦፍ ቨርጂኒያ ሙሉ ፈቃዱን ከአገኘን በኋላ ከነብይሎው ወደ ሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አባ ፋኑኤል አቅርበን ቡራኬ ተቀብለናል። የሙሉ ፈቃድደብዳቤውንም በመጠባባቅ ላይ እንገኛለን።

ገዳማችን የሚመሠረተው ዓላምውም ይሁን ይዘቱ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምን የክህናት ማሰልጠኛ የዛሬው ኮሌጅን አብነት ያደረገ ነው። የተለያዩ የገዳማት ቅርጾች/ሥርዓቶች/ አሉ። ከቅርጾቹ/ከሥርዓቱ/ አንዱ የአንድነት ገዳም የሚባለው ነው። የዝዋይ ገዳማችንም ይህ ቅርጽ ያለው በመሆኑ እኛ ይህንን ቅርጽ ነው የምንከተለው።ስለዚህ ገዳማችን የአንድነት ገዳም ሆኖ ይቋቋማል ማለት ነው።


ቦታው ከተገዛ በኋላ ቅድሚያ የሚሰጠው ትልቁ አባት አባ ጎርጎርዮስ የዝዋይ ሐመረ ብርሐን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምን ሲመሠርቱ ቤተክርስቲያን ከመሥራታቸው በፊት የእንግዶች ማረፊያ ነው የሠሩት። ቤተክርስቲያን የሚሠሩም ይሁን ገዳሙን የሚረዱ እንግዶች መጀመሪያ ማረፊያ ያስፈልጋቸዋል በማለት።የሚገርመው ደግሞ እኛ እግዚአብሔር ቢፈቅድልን በእንግድነት የሚመጡም ይሁኑ በአገግሎት የሚሳተፉ የተገኘው ቦታ ይዘት ሁሉም ነገር የተዘጋጀ ነው።ቦታው እንደተገዛ የመጀመሪያ ሥራችን ለእንግዶችና ለአገጋዮች ማረፊያን ማመቻቸት ይሆናል ማለት ነው።

ገዳሙ ውስጥ ለተገልጋዮች በየደረጃቸው የሚሰጡ አገግሎቶች ሥርዓታቸው፦

1. የገዳሙ ዕቅድ የንግዶች ቤት ሲዘጋጅ ከሁሉ በፊት ሥርዓተ ገዳም በሚፈቅደው መሠረት የወንዶችንና የሴቶችን ማረፊያ በመለየት ለሱባኤ/ለጸሎትም/ ይሁን ለአገግሎት ለሚመጡ ምእመናን የሚሆን ሥፍራ ማዘጋጀት የመጀመሪያው ሥራችን ይሆናል።
2. አቅም በሚፈቅደው መሠረት የአብነት ትምህርቶች የሚሰጡበትን መሠረታዊ ነገር በማሟላት ሁኔታዎች ያመቻቻል።
3. ከዚህም ሌላ የተለያዩ የበገናና የመሳሰሉትን ሃገሩን ሊመጥን ቤተክርስቲያናችንና ሃገራችንም ሊያስተዋውቅ የሚችልበትን መንገድ በማሰናዳት ትምህርቱ እንዲሰጥ ለማድረግ ሃሳቡ አለን።
4. እንደዚሁም ገዳሙና የአካባቢውን አብያተ ክርስቲያናትን ሊረዱ የሚችሉ ልዩ ልዩ የምሥጢራት መፈጸሚያና አዘጋጅቶ ለማቅረብና በተጨማሪም የእደ ጥበባት ውጤቶችን የሆኑትን እንደ ዕጣንና ሌሎችም ንዋያተ ቅድሣት የራቀውን በማቅረብ፣ መዘጋጀት የሚቻለውን ደግሞ በማዘጋጀት ለማቅረብ ገዳሙ ይተጋል።።
5. በሰሜን አሜሪካና በሌሎችም ክፍለ አለማት ያሉትን ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች ፍጹም በሆነ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት የታነጹ ሆነው ለዓለማችን መልካም ሆነው መልካም እንዲሠሩ ከራሳቸው አስተማሪዎችን መልምሎ ተገቢውን ኮርስ አዘጋጅቶ ማሰልጠንና አሰልጣኞችንም በማውጣት ግብረ ገብነት ያላቸው ወጣቶችን መፍጠር ሌላው ዓላማችን ነው።ለአዲሱ ትውልድ የግድ ከራሱ የወጣ አስተማሪ ስለሚያስፈልገው።
6. ከሁሉም በላይ በየቤቱ፣በእስር ቤት፣በልዩ ልዩ ሱስና ጥገኛ በሆነ ክፉ አመለካከት ተይዘው ያሉ ወጣቶችን ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን በሚያስፈልገው ሁሉ የባህርይ ለውጥ አምጥተው እንደዚሁ ከህብረተሰቡ ጋር በመልካም ግንኙነት አንድ ሆነው እንዲገለገሉ ማገገልም እንዲችሉ ማድረግም የገዳሙ ተጨማሪ ዓላማና ዕቅድም ነው።
7. በተጨማሪም የወጣቶች ጉዳይ ብቻ ሳይሆን አረጋውያን አባቶችና እናቶች መንፈሳዊ እንክብካቤ በማጣት በብዙ ችግር እንደሚኖሩ የታወቀ ነውና የነርሱም ጉዳይ የሚታሰብበትና የገዳሙ ምናልባትም የረጅሙ ግዜ ዕቅድ ሊሆን ይችላል።
8. ለምእመናን ሁሉ እንደ አስፈላጊነቱ የምክር አገግሎትና ለንስሐ፣ለጋብቻ ለመሳሰሉት ተገቢውን ትምህርት ሰጥቶ ለሚዘጋጁበት የሕይወት ጉዞ ሁሉ በኮርስ መልክ ትምህርት መስጠትና ለክብር ማብቃት ገዳሙ አቅዷል።
9. ትልቁ የቦታው መተዳደሪያም እርሻው ነው።መናንያኑ የሚተዳደሩት ከምእመናን ምጽዋት ጠብቀው ሳይሆን በራሳቸው እየሠሩ ስለሆነ በባለሞያ እየታገዙ ጤናማ የሆነ ምግብ አምርተውም ከራሳቸውም አልፈው ተርፈው ለህብረተሰቡ በማቅረብ ገቢያቸውን ያሳድጋሉ።
ወደፊት በገዳሙ ውስጥ ሊሟሉ የሚገባችው፦
1. የመናንያን ልዩ ሥፍራ/ማረፊያ/ቦታ
2. የወንዶችና የሴቶች የተለያዩ ማረፊያዎች
3. በጊዜውና ለወደፊት የተማሪዎች መማሪያና ማረፊያ
4. ቤተክርስቲያን ከነቤተልሔሙ
5. ለመናንያን ለተማሪዎችና ለሕዝብም የሚሆን ሙሉ የሆነ ከንኪችኑ የምግብ አዳራሽ ናቸው
ቦታው ለአገግሎት ብቁ እስሚሆን ድረስ ከደጋፊዎች የሚያስፈልጉ ነገርሮች ፦
• ገዳሙ ራሱን ችሎ በራሱ መንቀሳቀስ እስከሚችል ድረስ የዚህ በረከት ተካፋይ መሆን የሚፈልጉ ሁሉ ባለው ማገልገል ይችላል።እውቀት ያለው በእውቀቱ፣ጉልበት ያለው በጉልበቱ፣ገንዘብ ያለው በገንዘቡ ኦርቶዶክሳዊ የሆነ ሁሉ የዚህ ታሪካዊን የገዳም ምሥረታ ሥራ ላይ በመሳተፍ አሻራውን በማስቀመጥ በአምላኩ ዘንድ በመዝገበ ሕይወቱ ስሙን ያጽፍ።

• በመዝሙር 126፥127 ”እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ፥ ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ፤ እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ፥ ጠባቂ በከንቱ ይተጋል። “ እንደተባለ ሁላችንም ለሥራው ምክንያቶች እንጂ ዋናዎች አይደለንም። እርሱ ሁሉን የሚችል አምላክ በሃገራችን ኢትዮጵያ ብዙ ምክንያት አድርጎ ብዙ ታላላቅ የታሪክ ቦታዎችና ታላላቅ ሥራዎች ያሰራቸው ብዙ ሰዎች ነበሩት። ዛሬ ሁሉችንም መመኘትም ሆነ መጸለይ ያለብን ነገር ቢኖር የነዚያ ደጋግ አባቶችና እናቶች አምላክ እኛንም ምክንያት አድርገኸን ይህን ሥራ ጀምረን እንድንፈስም እርዳን ብለን ጸሎታችንን እናድርግ። አምላከ ቅዱስ ሳሙኤል ሥራችንን ይባርክልን

“ባንዝልም በጊዜው እናጭዳለንና መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት። (ገላ 6፥9)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

04/12/2026

He is risen! Truly, He is risen!

Timket celebration at St. Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery, 18429 Youngs Ln, Elkwood, VA 22718.
01/20/2026

Timket celebration at St. Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery, 18429 Youngs Ln, Elkwood, VA 22718.

12/18/2025

We invite you to the annual celebration in honor of Saint Abba Samuel of Waldebba as we commemorate his holy departure.

📆 Date: Sunday, December 21, 2025

📍 Location: 18429 Youngs Ln, Elkwood, VA 22718

🕔 Time: 5am

Join us for this sacred occasion to reflect on the life and legacy of a revered saint who dedicated his life to faith and spiritual guidance. All are welcome to participate in prayer and blessings.

11/21/2025

“ስጡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ ይሰፈርላችኋልና፥” ሉ 6:38

ይህ ወቅት በተለይ በሰሜን አሜሪካን ልዩ የእርዳታ (Giving Tuesday) ወቅት ነው።ሁሉም በአቅሙ ለአብያተ ክርስርስቲያናትም ይሁን ለእርዳታ ሥራየፌስቡክ ባለቤት በሚያደርገው ማች በማድረግ ለሚፈጽመው በጎ ተግባር ሁሉም እንዳቅሙ የሚችለውን ያደርጋል። 🙏 እኛ ም የገዳማቸ‍እን ልጆች ደጋፊዎች በነህ 2:18 “እነርሱም፦ እንነሣና እንሥራ፡ አሉ። እጃቸውንም ለበጎ ሥራ አበረቱ። “ በምንችለው ተባብረን ለገዳማችን የቤተክርስቲያን ሥራ ለማገዝ ይሆን ዘንድ የታቀደውን ግብ ለመድረስ ጥቂት ቀናት ብቻ ይቀሩናል፣ እጃችሁን ለዚህ በጎ ሥራ እንድተዘረጉልን መንፈሳዊ ጥሪአችንን እናቀርብላችኋለን።

ሁላችንም እኛ ብቻ ሳንሆን ወዳጆቻችን ሁሉ የአባቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ገዳም የቤተክርስተ‍ኢያን ሥራ የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ ይህንን መንፈሳዊ ጥሪ በማዳረስ መንፈሳዊ ግዴታችንን እንወጣ።
” እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ……”2ኛ ቆሮ፡9፡7፡፡

የስጦታ ትንሽ የለውምና ብዙ ሆነን የምንችላት ትንሽ ስጦታ በዝታ ፈቃደ እግዚአብር ታክሎባት ትልቅ ትሠራለችና የምንችለውን በማድረግ የታሪክ ባለቤት እንሁን።
💒 በተቻላችሁ የገዘብ ልገሳ በማድረግ እንዲሆም ለወዳጅ ዘመድ ሀሳቡን በማካፈል ለምትተባበሩን ሁሉ በጻቁ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ስም ምስጋናችንን እናቀርባለን። የጻድቁ ረድኤት በረከት ጸሎት ከሀገራችን ከ ኢትዮጵያ በዚህች በለንባት አሜሪካ ጋር ይሁን
ገዳሙ

📲 https://www.facebook.com/donate/844998314550403/?fundraiser_source=external_url

“ከመቅደሱ ረድኤትን ይላክልህ፥ ከጽዮንም ያጥናህ ።ቍርባንህን ሁሉ ያስብልህ፤ የሚቃጠል መሥዋዕትህን ያለምልምልህ። እንደ ልብህ ይስጥህ፡ ፈቃድህንም ሁሉይፈጽምልህ።”መዝ 19/20:2-4

11/16/2025

Today we are officially launching our Giving Tuesday fundraising campaign 🙏🏾 We only have a few days until Giving Tuesday to reach our goal and we need your help.

This Giving Tuesday, we invite everyone to join us in supporting Abba Samuel Monastery. Your gift will help us begin building our new church a house of prayer, peace, and spiritual renewal for generations to come.

Every donation, no matter the size, brings us closer to our goal and helps us start the building readiness. Together, let’s share in this holy mission and spread the blessings of faith and community.

Please use the QR code or the link below to donate and share with others. Let’s make this Giving Tuesday a day of grace and giving from the heart.

🌐 https://www.facebook.com/donate/844998314550403/?fundraiser_source=external_url

“Each one must give as he has decided in his heart, not reluctantly or under compulsion, for God loves a cheerful giver.” 2 Corinthians 9:7

Hamere Berhan Saint Abba Samuel EOT Monastery invites you to our Season of Flowers (ዘመነ ጽጌ) youth event!📅 Saturday, Octo...
09/24/2025

Hamere Berhan Saint Abba Samuel EOT Monastery invites you to our Season of Flowers (ዘመነ ጽጌ) youth event!

📅 Saturday, October 11
🕚 11:30 AM – 2:30 PM

🌼 Kids learn about ዘመነ ጽጌ
🌿 Explore the monastery garden
🌱 Learn how to plant
🌸 Parents & kids plant their own flower
🥤 Refreshments served

Join us with your family and share with others
May God bring us all safely to this blessed day!

Looking forward to seeing everyone this Saturday!
09/10/2025

Looking forward to seeing everyone this Saturday!

08/10/2025

The Fast of the Dormition of St. Mary begins tomorrow, August 7. A sacred time of prayer, repentance, and spiritual renewal in the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. Join us at Hamere Berhan Saint Abba Samuel EOT Monastery as we honor the Dormition of the Holy Mother of God, St. Mary.📍 18429 Youngs Ln, Elkwood, VA 22718. Check the flyer for full service schedule. Can’t make it in person? Join virtually:📞 Dial-in: (605) 475-4887🔢 Access Code: 718023📲 Also available on the Free Conference Call (FCC) App (App Store, Google Play, or Web)🙏🏾 May this fast be a time of spiritual strength, healing, and renewal.Through the intercession of St. Mary, may God grant you a safe, fruitful, and blessed fast.

Glory to God 🙏🏾We invite you to come and take part in Holy Liturgy every Sunday @ 6am
05/29/2025

Glory to God 🙏🏾

We invite you to come and take part in Holy Liturgy every Sunday @ 6am

Wishing Everyone a Blessed Fasting SeasonToday marks the beginning of Abiy Tsome (The Great Lent), a sacred time of pray...
02/24/2025

Wishing Everyone a Blessed Fasting Season

Today marks the beginning of Abiy Tsome (The Great Lent), a sacred time of prayer, fasting, and repentance in the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. May this season bring spiritual renewal, strength, and closeness to God.

"Return to me with all your heart, with fasting, with weeping, and with mourning; Rend your hearts and not your garments. Return to the Lord your God, for He is gracious and compassionate, slow to anger and abounding in love."
— Joel 2:12-13

May your journey through this holy season be filled with peace, humility, and spiritual growth. Melkam Abiy Tsome!

Address

Elkwood, VA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hamere Berhan St Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Hamere Berhan St Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery:

Share