Hamere Berhan St Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery

Hamere Berhan St Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Hamere Berhan St Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery, Elkwood, VA.

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

“ከዱሮ ዘመን የፈረሱት ስፍራዎች ይሠራሉ፥ የብዙ ትውልድም መሠረት ይታነጻል፤ አንተም፦ ሰባራውን ጠጋኝ፥ የመኖሪያ መንገድን አዳሽ ትባላለህ።” (ኢሳ 58፥12)
ሐመረ ብርሃን ቅዱስ አባ ሳሙኤል ገዳም እንዴትና ለምን ተመሠረተ?
የሐመረ ብርሃን ቅዱስ አባ ሳሙኤል ገዳም አጀማመሩ በሰሜን አሜሪካን ተወልደው ወይም በልጅነታቸው መጥተው ያደጉ ወጣቶች “አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር” (2ኛ ጢሞ 3፥14) እንደተባለ እግዚአብሔርን አውቀው በእግዚአብሔር ፍቅር መኖር እንዲችሉ በተከፈተላቸው የሐሙስ የሰርክ ጉባኤ መነሻነት ነው።
እንዲሁም እነዚህን ብቻ ሳይሆን ትምህርት ቤቱን አሳድጎ መጪውን ትውልድ በትምህርት እየኮተኮቱ በእግዚአብሔር ቤት ለማሳደግ ከተማሩም በኋላ ከራሳቸው አልፈው ተርፈው ወደ አገግሎቱ የሚገቡ ወጣቶች የሚቀርቡበትን መንገድ ማበጀት አስፈላጊም ስለሆነ ይህንና የመሳሰሉትን ሃሳቦች ታሳቢ በማድረግ ለትምህርትና መንፈሳዊውን ሕይወት መለማመጃ የሚሆን ገዳም የግድ አስፈልጓል።
ዛሬ ላይ ሆነን ለመጪው ትውልድ ታአሪክና ሃይማኖቱን እንዲወርስና እንዲያስቀጥል አስተካክለን አዘጋጅተን ካላስረከብነው ማንነቱ ሊጠፋበት ስለሚችል ይህን የሚሠራ ገዳምና ማሰልጠኛ አስፈልጓል።
መቼ ተመሠረተ?
ይህ ገዳም በልዩ ልዩ ምክንያቶች በጽንሰ ሃሳብ ደረጃ ቆየት ያለ ቢሆንም እንቅስቃሴው ወደመተግበር የተጀመረው ግን ወደ ስምንት ዓመት ይሆነዋል። የተለያዩ እናቶችና አባቶች ወደሌሎች እንደካቶሊክ የግብፃውያን የሆኑ ገዳማት እየሄዱ የሁለት የሦስት ቀን እረፍት አድርገው ሲመለሱና ሲነግሩን የራስ ቦታ ቢገኝ ደግሞ የሚያሰኝ እቅድ እንዲፈጠር ከእለ ከተጠቀሰው ሃሳብ ጋር ከመነጫው መካከል አንዱ ምክንያትምና ለሃሳቡ መነሻም ሆኖአል። በተጨማሪም መነኮሳት አባቶች በአግልግሎትም ይሁን በሆነው ምክንያት ሃገርቤት ካልሄዱ በስተቀር በከፋቸው ግዜ እንኳን የእረፍት ግዜና ቦታ ባለመኖሩ ብዞዎቹ ተጎድተዋል።ለአሳ ሕይወቱ በባሕር መገኘት እንደሆነ ሁሉ ለመንኩሴም ሕይወቱ ገዳም ነውና።
ከላይ እንደተገለጸው ወጣቶችም ቢሆኑ ለመንፈሳዊ አገግሎት እራሳቸውን ቢሰጡ ወደሃገር ቤት ለመንፈሳዊው ትምህርት ሲሄዱ ስለሚከብዳቸው ወደኋላ እንዳይሉ ገዳሙ የምናኔ ቦታ ብቻ ሳይሆን ትምህርት ቤትም ጭምር እንዲሆን ታቅዶ ነው መመሥረት ያስፈለገው። ከላይ በተጠቀሰው ዓመት ታስቦ እቅስቃሴው በዚህ ሃገር ያሉትን የገዳማት እንቅስቃሴን መቃኘት ተጀምሮ ፈቃድ የማግኘት ሂደቱ ቀጥሎ በዲሤምበር 2015 የመጀመሪያው ፈቃድ ከአሜሪካን መንግሥት ተገኝቷል።

የገዳሙ እውቅናና ሕጋዊነት
ይህ ገዳም የሀገሪቱ ለሃይማኖት የተሰተው ሕግ በሚያዝዘው መሠረት ከኮመንዌልዝ ኦፍ ቨርጂኒያ ሙሉ ፈቃዱን ከአገኘን በኋላ ከነብይሎው ወደ ሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አባ ፋኑኤል አቅርበን ቡራኬ ተቀብለናል። የሙሉ ፈቃድደብዳቤውንም በመጠባባቅ ላይ እንገኛለን።

ገዳማችን የሚመሠረተው ዓላምውም ይሁን ይዘቱ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምን የክህናት ማሰልጠኛ የዛሬው ኮሌጅን አብነት ያደረገ ነው። የተለያዩ የገዳማት ቅርጾች/ሥርዓቶች/ አሉ። ከቅርጾቹ/ከሥርዓቱ/ አንዱ የአንድነት ገዳም የሚባለው ነው። የዝዋይ ገዳማችንም ይህ ቅርጽ ያለው በመሆኑ እኛ ይህንን ቅርጽ ነው የምንከተለው።ስለዚህ ገዳማችን የአንድነት ገዳም ሆኖ ይቋቋማል ማለት ነው።


ቦታው ከተገዛ በኋላ ቅድሚያ የሚሰጠው ትልቁ አባት አባ ጎርጎርዮስ የዝዋይ ሐመረ ብርሐን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምን ሲመሠርቱ ቤተክርስቲያን ከመሥራታቸው በፊት የእንግዶች ማረፊያ ነው የሠሩት። ቤተክርስቲያን የሚሠሩም ይሁን ገዳሙን የሚረዱ እንግዶች መጀመሪያ ማረፊያ ያስፈልጋቸዋል በማለት።የሚገርመው ደግሞ እኛ እግዚአብሔር ቢፈቅድልን በእንግድነት የሚመጡም ይሁኑ በአገግሎት የሚሳተፉ የተገኘው ቦታ ይዘት ሁሉም ነገር የተዘጋጀ ነው።ቦታው እንደተገዛ የመጀመሪያ ሥራችን ለእንግዶችና ለአገጋዮች ማረፊያን ማመቻቸት ይሆናል ማለት ነው።

ገዳሙ ውስጥ ለተገልጋዮች በየደረጃቸው የሚሰጡ አገግሎቶች ሥርዓታቸው፦

1. የገዳሙ ዕቅድ የንግዶች ቤት ሲዘጋጅ ከሁሉ በፊት ሥርዓተ ገዳም በሚፈቅደው መሠረት የወንዶችንና የሴቶችን ማረፊያ በመለየት ለሱባኤ/ለጸሎትም/ ይሁን ለአገግሎት ለሚመጡ ምእመናን የሚሆን ሥፍራ ማዘጋጀት የመጀመሪያው ሥራችን ይሆናል።
2. አቅም በሚፈቅደው መሠረት የአብነት ትምህርቶች የሚሰጡበትን መሠረታዊ ነገር በማሟላት ሁኔታዎች ያመቻቻል።
3. ከዚህም ሌላ የተለያዩ የበገናና የመሳሰሉትን ሃገሩን ሊመጥን ቤተክርስቲያናችንና ሃገራችንም ሊያስተዋውቅ የሚችልበትን መንገድ በማሰናዳት ትምህርቱ እንዲሰጥ ለማድረግ ሃሳቡ አለን።
4. እንደዚሁም ገዳሙና የአካባቢውን አብያተ ክርስቲያናትን ሊረዱ የሚችሉ ልዩ ልዩ የምሥጢራት መፈጸሚያና አዘጋጅቶ ለማቅረብና በተጨማሪም የእደ ጥበባት ውጤቶችን የሆኑትን እንደ ዕጣንና ሌሎችም ንዋያተ ቅድሣት የራቀውን በማቅረብ፣ መዘጋጀት የሚቻለውን ደግሞ በማዘጋጀት ለማቅረብ ገዳሙ ይተጋል።።
5. በሰሜን አሜሪካና በሌሎችም ክፍለ አለማት ያሉትን ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች ፍጹም በሆነ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት የታነጹ ሆነው ለዓለማችን መልካም ሆነው መልካም እንዲሠሩ ከራሳቸው አስተማሪዎችን መልምሎ ተገቢውን ኮርስ አዘጋጅቶ ማሰልጠንና አሰልጣኞችንም በማውጣት ግብረ ገብነት ያላቸው ወጣቶችን መፍጠር ሌላው ዓላማችን ነው።ለአዲሱ ትውልድ የግድ ከራሱ የወጣ አስተማሪ ስለሚያስፈልገው።
6. ከሁሉም በላይ በየቤቱ፣በእስር ቤት፣በልዩ ልዩ ሱስና ጥገኛ በሆነ ክፉ አመለካከት ተይዘው ያሉ ወጣቶችን ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን በሚያስፈልገው ሁሉ የባህርይ ለውጥ አምጥተው እንደዚሁ ከህብረተሰቡ ጋር በመልካም ግንኙነት አንድ ሆነው እንዲገለገሉ ማገገልም እንዲችሉ ማድረግም የገዳሙ ተጨማሪ ዓላማና ዕቅድም ነው።
7. በተጨማሪም የወጣቶች ጉዳይ ብቻ ሳይሆን አረጋውያን አባቶችና እናቶች መንፈሳዊ እንክብካቤ በማጣት በብዙ ችግር እንደሚኖሩ የታወቀ ነውና የነርሱም ጉዳይ የሚታሰብበትና የገዳሙ ምናልባትም የረጅሙ ግዜ ዕቅድ ሊሆን ይችላል።
8. ለምእመናን ሁሉ እንደ አስፈላጊነቱ የምክር አገግሎትና ለንስሐ፣ለጋብቻ ለመሳሰሉት ተገቢውን ትምህርት ሰጥቶ ለሚዘጋጁበት የሕይወት ጉዞ ሁሉ በኮርስ መልክ ትምህርት መስጠትና ለክብር ማብቃት ገዳሙ አቅዷል።
9. ትልቁ የቦታው መተዳደሪያም እርሻው ነው።መናንያኑ የሚተዳደሩት ከምእመናን ምጽዋት ጠብቀው ሳይሆን በራሳቸው እየሠሩ ስለሆነ በባለሞያ እየታገዙ ጤናማ የሆነ ምግብ አምርተውም ከራሳቸውም አልፈው ተርፈው ለህብረተሰቡ በማቅረብ ገቢያቸውን ያሳድጋሉ።
ወደፊት በገዳሙ ውስጥ ሊሟሉ የሚገባችው፦
1. የመናንያን ልዩ ሥፍራ/ማረፊያ/ቦታ
2. የወንዶችና የሴቶች የተለያዩ ማረፊያዎች
3. በጊዜውና ለወደፊት የተማሪዎች መማሪያና ማረፊያ
4. ቤተክርስቲያን ከነቤተልሔሙ
5. ለመናንያን ለተማሪዎችና ለሕዝብም የሚሆን ሙሉ የሆነ ከንኪችኑ የምግብ አዳራሽ ናቸው
ቦታው ለአገግሎት ብቁ እስሚሆን ድረስ ከደጋፊዎች የሚያስፈልጉ ነገርሮች ፦
• ገዳሙ ራሱን ችሎ በራሱ መንቀሳቀስ እስከሚችል ድረስ የዚህ በረከት ተካፋይ መሆን የሚፈልጉ ሁሉ ባለው ማገልገል ይችላል።እውቀት ያለው በእውቀቱ፣ጉልበት ያለው በጉልበቱ፣ገንዘብ ያለው በገንዘቡ ኦርቶዶክሳዊ የሆነ ሁሉ የዚህ ታሪካዊን የገዳም ምሥረታ ሥራ ላይ በመሳተፍ አሻራውን በማስቀመጥ በአምላኩ ዘንድ በመዝገበ ሕይወቱ ስሙን ያጽፍ።

• በመዝሙር 126፥127 ”እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ፥ ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ፤ እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ፥ ጠባቂ በከንቱ ይተጋል። “ እንደተባለ ሁላችንም ለሥራው ምክንያቶች እንጂ ዋናዎች አይደለንም። እርሱ ሁሉን የሚችል አምላክ በሃገራችን ኢትዮጵያ ብዙ ምክንያት አድርጎ ብዙ ታላላቅ የታሪክ ቦታዎችና ታላላቅ ሥራዎች ያሰራቸው ብዙ ሰዎች ነበሩት። ዛሬ ሁሉችንም መመኘትም ሆነ መጸለይ ያለብን ነገር ቢኖር የነዚያ ደጋግ አባቶችና እናቶች አምላክ እኛንም ምክንያት አድርገኸን ይህን ሥራ ጀምረን እንድንፈስም እርዳን ብለን ጸሎታችንን እናድርግ። አምላከ ቅዱስ ሳሙኤል ሥራችንን ይባርክልን

“ባንዝልም በጊዜው እናጭዳለንና መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት። (ገላ 6፥9)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

08/28/2026

On his 40th day, this beloved baby boy received the Sacrament of Holy Baptism, according to the tradition of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church.

May God protect him, strengthen him in the faith, and guide him throughout all the days of his life. 🙏🏾

እባክዎ በዚህ ልዩ ቀን ላይ እንዲገኙልን በአክብሮት እንጋብዛለን። በተጨማሪም፣ መገኘት ለሚፈልጉ ሌሎች ሰዎች እንዲያጋሩ አደራ እንላለን::በእምነትና በምስጋና ይህንን ልዩ ቀን በአንድነት እን...
08/27/2026

እባክዎ በዚህ ልዩ ቀን ላይ እንዲገኙልን በአክብሮት እንጋብዛለን። በተጨማሪም፣ መገኘት ለሚፈልጉ ሌሎች ሰዎች እንዲያጋሩ አደራ እንላለን::

በእምነትና በምስጋና ይህንን ልዩ ቀን በአንድነት እንድናከብር እንሰብሰብ።

08/26/2026

Peace and blessings to all. May God's grace reach you wherever you are.

We are honored to invite you to the Memorial Celebration of our Righteous Father, Saint Abba Samuel of Waldebba, on Saturday, September 19, 2026. Join us for this blessed event and partake in the spiritual blessings of the day.

18429 Youngs Ln, Elkwood, VA 22718

We kindly request your presence and encourage you to share this invitation with others who may wish to attend. Let us come together in faith and gratitude for this special occasion.

08/21/2026

As we come to the final day of the blessed Fast of Filseta, may our prayers, fasting, and praises be received before God.

May the intercession and blessings of our Holy Mother, the Virgin St. Mary, be with us all, and may God grant us the grace to complete this holy fast in peace

08/17/2026

God bless the choir for the beautiful hymn. May they hear the hymns of the holy angels.

Wishing everyone a blessed week ahead. As we enter the final days of the Fast of the Assumption, may God grant us strength to complete this holy fast with prayer, faith, and devotion, and may we be blessed to joyfully celebrate the Feast of the Assumption of our Holy Mother, the Virgin Mary.

07/20/2026

Zare Lene by Zemarit Abonesh Adinew!

By the grace and mercy of God, we give thanks for the recovery of our dear sister, Zemarit Abonesh. After being hospitalized and undergoing multiple surgeries, God has carried her through every trial and granted her strength and healing.

Today, she came to the monastery to offer her heartfelt testimony, giving thanks to God for His mercy, protection, and the countless blessings He has bestowed upon her.

May our Lord continue to strengthen and protect Zemarit Abonesh, granting her many years of good health, peace, and joy. May He also bless and watch over her entire family.

"Give thanks to the Lord, for He is good; His mercy endures forever." Psalm 118:1

04/12/2026

He is risen! Truly, He is risen!

Timket celebration at St. Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery, 18429 Youngs Ln, Elkwood, VA 22718.
01/20/2026

Timket celebration at St. Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery, 18429 Youngs Ln, Elkwood, VA 22718.

12/18/2025

We invite you to the annual celebration in honor of Saint Abba Samuel of Waldebba as we commemorate his holy departure.

📆 Date: Sunday, December 21, 2025

📍 Location: 18429 Youngs Ln, Elkwood, VA 22718

🕔 Time: 5am

Join us for this sacred occasion to reflect on the life and legacy of a revered saint who dedicated his life to faith and spiritual guidance. All are welcome to participate in prayer and blessings.

Address

Elkwood, VA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hamere Berhan St Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Hamere Berhan St Abba Samuel Ethiopian Orthodox Tewahedo Monastery:

Shortcuts

Share