Christian tube - ክርስቲያን ቲዩብ

Christian tube - ክርስቲያን ቲዩብ Sharing spiritual wisdom and truth grounded in evangelical Christian principles to inspire faith and transformation
ቤተክርስቲያንን መሰረት ያደረጉ መንፈሳዊ መረጃዎች የሚቀርቡበት ገፅ
(11)

"ሥራ በእኛ ምርጫ ነው፤ አገልግሎት የጌታ ጥሪ ነው፤ በስራ ክፍያን እንጠብቃለን፤ በአገልግሎት እንድንሰጥ ይጠበቅብናል፤ በስራ አንድን ነገር ለመቀበል ሌላ ነገር እንሰጣለን፤ በአገልግሎት አስቀድሞ የተሰጠንን መልሰን እንሰጣለን፤ ሥራ በእኛ ችሎታ ላይ ይመሰረታል፤ አገልግሎት ግን ለእግዚአብሔር በመገኘት ላይ ይመሰረታል፤ በአግባቡ የተሰራ ሥራ ምስጋናን ያስገኛል፤ በአግባቡ የተሰጠ አገልግሎት ለኢየሱስ ክብርን ያመጣል፡፡"
የዚህ አገልግሎት ዓላማ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ክብርን ለማምጣት ነው፡፡
በጌታ የተወደዳችሁ የክርስቲያን ቲዩብ ተከታዮች ብቻውን የሚያድነውን ኢየሱስን ለማያምኑ በመግለጥ ከእኛ ጋር እንድንሰራም ጋብዘናችኋል፡፡

ኢየሱስ ያለው ህይወት አለው!!

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ ክብረ በዓልን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ።የኅብረቱ ከፍተኛ አመራሮች ሰኔ 9/2018 ዓ.ም፣ በዋና ጽ/ቤ...
06/17/2026

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ ክብረ በዓልን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ።

የኅብረቱ ከፍተኛ አመራሮች ሰኔ 9/2018 ዓ.ም፣ በዋና ጽ/ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የ50 ዓመት ኢዮቤልዩ እንዲሁም የ2018 ዓ.ም የመጋቢያን ዓመታዊ ኮንፍረንስ መክፈቻና የተለያዩ ኮንፍረንሶች መከናወናቸውን ገልጸው ከሐምሌ 6/2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 9/2018 ዓ.ም የመዝጊያ ዝግጅት እንደሚደረግ አሳውቀዋል።

የክብረ በዓሉን ሂደት የሚያስተባብረውን ግብረ ኃይል የሚመሩት ወንድም የኔነህ ታደሰ፣ ኅብረቱ ከ 50 ዓመታት በፊት መስከረም 4/1968 ዓ.ም መመሥረቱን ገልጸው፣ በኅብረቱ ውስጥ ላሉ ቤተ እምነቶች እና ወንጌላውያን የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ፕሬዚዳንት መጋቢ ደረጀ ታፈሰ፣ ኅብረቱ ከ50 ዓመታት በፊት በአዳማ ከተማ የመሠረተ ክርስቶስ ይዞታ በነበረ ሥፍራ ላይ በዘጠኝ ቤተ እምነቶች መመሥረቱን አንስተው፣ በኢዮቤልዩ ክብረ በዓል ተከታታይ ሦስት ቀናት የሚኖሩ መርሐግብሮችን በመጥቀስ፣ የወንጌል አማኙ እንዲሁም የኅብረቱ አባል ቤተ እምነቶች በክብረ በዓሉ ላይ እንዲገኙ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

ከመርሐግብሮቹ መካከል የአገልጋዮች ሥልጠና፣ ከድኅረ ምርጫ ጋር በተያያዘ የኅብረቱ የሰላም አምባሳደርነት፣ ከተማ አቀፍ የወንጌል አገልግሎቶች፣ የቀደምት አባቶች እና አገልጋዮች ዕውቅና እንዲሁም የመሪዎች ጉባኤ ይገኙበታል።

የኅብረቱ ምክትል ፕሬዚዳንት መጋቢ ሰንበቱ ባሼ በበኩላቸው፣ የወንጌል አማኞች ስለዚህ መርሐግብር እንዲጸልዩ በማሳሰብ በዚህ ታላቅ ክብረ በዓል ላይ በአካል መገኘት የሚችሉ ሁሉ ደስታቸውን እንዲካፈሉ፣ ከሀገር ውጪ ያሉ ደግሞ የሚዲያ አማራጮችን በመጠቀም እንዲከታተሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ከክልል ከተሞች ለሚመጡ እንግዶች የማረፊያ እና ሌሎች አስፈላጊ ዝግጅቶች በበቂ ሁኔታ መደረጋቸውን ያሳወቁት፣ የአዲስ አበባ ኅብረት ጠቅላይ ጸሐፊ መጋቢ ሙላቱ፣ ክብረ በዓሉ ለኢዮቤልዩ ልዩ አቀባበል የምናደርግበት፣ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለቀጣዩ ኀምሳ ዓመትም በቂ ዝግጅት የምናደርግበት ነው ብለዋል።

ከዛሬ 50 ዓመት በፊት ኅብረቱ ሲመሠረት ከነበሩት አባቶች መካከል አንዱ የሆኑት ጋሽ መኮንን ደሳለኝ፣ ኅብረቱ በወቅቱ በነበሩ አባል ቤተ እምነቶች መካከል የነበረውን የዶክትሪን ልዩነት ወደ አንድነት ያመጣ እና ቤተክርስቲያን ችግር ውስጥ በነበረችበት ወቅት የተመሠረተ መሆኑን ገልጸዋል። ጋሽ መኮንን አክለውም፣ በወቅቱ በተከታታይ በቤተክርስቲያን ላይ በመጣው ስደት፣ ያልተሰደዱት ወገኖች የተሰደዱትን መያዝ የቻሉት ኅብረቱ በመቋቋሙ ምክንያት እንደሆነ አስምረው ሲናገሩ፣ ያኔ በዘጠኝ ቤተ እምነቶች የተቋቋመው ኅብረት፣ ዛሬ ከ120 በላይ ቤተ እምነቶች እንደሚገኙበት በመግለጽ ጭምር ነው።

የክብረ በዓሉ አስተባባሪ ግብረ ኃይል መሪ የሆኑት ወንድም የኔነህ ታደሰ፣ መርሐግብሩ ላይ መገኘት የሚቻለው በምዝገባ እንደሆነና አማኞች ጽ/ቤት በመገኘት ወይም በስልክ መመዝገብ እንደሚችሉ፣ ደብዳቤ እና የስልክ ጥሪ ደርሷቸው ምላሽ ያልሰጡ ቤተ እምነቶችም በቶሎ መልስ እንዲሰጡ አሳስበዋል። በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ በጎ ፈቃደኛ ወንጌላውያን ከክልል ከተሞች የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል እያደረጉ ያሉትን ትብብርም አድንቀው ተግባሩ እንዲቀጥል አበረታተዋል።

ሐምሌ 9/2018 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ኅብረቱ በሚያሳውቀው ቦታ ላይ በሚደረገው መርሐግብር፣ የኅብረቱ የመጀመሪያው መተዳደሪያ ደንብ እና ቃለ ጉባኤዎች እንዲሁም በኅብረቱ የተከናወኑ ሥራዎችን የያዘ ኅትመት በዕለቱ ለተመልካች የሚቀርብ ይሆናል።

የኅብረቱ መሪዎች ከሚዲያ አካላት የክብረ በዓሉን ቦታ እንዲሁም ወጣቱን ትውልድ በተመለከተ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

የኅብረቱ መሪዎች የክብረ በዓሉን ቦታ በቀጣይ እንደሚያሳውቁ ገልጻው፣ ወጣቱ ትውልድ ከእነርሱ ጽናትን እንዲማር እና ፈተናዎችን አልፎ ለእግዚአብሔር መንግሥት እንዲቆም አባታዊ ምክራቸውን ከባርኮት ጋር አስተላልፈዋል።

ቃልኪዳን ሙሉጌታ ለክርስቲያን ቲዩብ

አስቀድሞ ሀሰተኞችን በግልፅ የተቃወመዉ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት 50ኛ አመቱን ሊያከብር ነዉ...
06/16/2026

አስቀድሞ ሀሰተኞችን በግልፅ የተቃወመዉ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት 50ኛ አመቱን ሊያከብር ነዉ...

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

ለዘመናዊ መኖሪያዎትና ለንግድዎ ጥንካሬ በመሀል ከተማ​1.የንግድ ሱቆች 👉​ ከ 8.2 እስከ 205 ካሬ አማራጭ ድረስ8 ካሬ ፦ 2.8 ሚ ብር  100% ሲከፍሉ 2.3 ሚ ብር ብቻ ​2. የመኖሪ...
06/16/2026

ለዘመናዊ መኖሪያዎትና ለንግድዎ ጥንካሬ በመሀል ከተማ

​1.የንግድ ሱቆች
👉​ ከ 8.2 እስከ 205 ካሬ አማራጭ ድረስ

8 ካሬ ፦ 2.8 ሚ ብር
100% ሲከፍሉ 2.3 ሚ ብር ብቻ

​2. የመኖሪያ አፓርትመንቶች

የካሬ አማራጮች
👉ባለ2 መኝታ ፦100፣111፣121፣ 134
እና 149 ካሬ

100 ካሬ ፦ 10.6 ሚ ብር
100% ለሚከፍሉ 9 ሚ ብር ብቻ

👉ባለ3 መኝታ ፦185 እና 193 ካሬ

185 ካሬ፦ 19.5 ሚ ብር
100% ሲከፍሉ 16,589,875

👉​ቅድመ ክፍያ: 10%
​ቀሪ ክፍያ: 8.5% በግንባታ ሂደት
(ወይም በየ 3 ወሩ) የሚከፈል።

👉​ልዩ ዕድል: ግንባታው ከመጠናቀቁ በፊት ንብረቱን መልሶ የመሸጥ (Resale) ዕድል ተመቻችቷል።


​ለበለጠ መረጃ
​📞 0912695957 🟢 WhatsApp
📞 0908438888 🟢 WhatsApp

 ...ባሳለፍነው ቅዳሜ ሰኔ 6 በከተማው ያሉ ክርስቲያን ነጋዴዎች፣ ስራ ፈጣሪዎች፣ የድርጅት ስራአስኪያጆች ባጠቃላይ እንደሀገር አሉ የምንላቸው ክርስቲያን የቢዝነስ ሰዎች የቸርች መለያየት ሳ...
06/16/2026

...
ባሳለፍነው ቅዳሜ ሰኔ 6 በከተማው ያሉ ክርስቲያን ነጋዴዎች፣ ስራ ፈጣሪዎች፣ የድርጅት ስራአስኪያጆች ባጠቃላይ እንደሀገር አሉ የምንላቸው ክርስቲያን የቢዝነስ ሰዎች የቸርች መለያየት ሳይገድባቸው ፣ የስራ መራራቅ ሳያስቆማቸው በአንድ ላይ ተሰባስበዋል። አሰባሳቢው ደግሞ የኢትዮጵያ ኢቫንጄሊካል ቢዝነስ ኔትወርክ (EBN) በየሶስት ወሩ የሚያዘጋጀው የኔትወርኪንግ የቁርስ እና የፀሎት መርሀግብር በማሪዮት ሆቴል በመዘጋጀቱ ነው።
በዚህ እጅግ ደማቅ በነበረ Mindset Matters በሚል ርዕስ በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ እጅግ በጣም በርካታ የንግዱ ማህበረሰብ የተገኘ ሲሆን በጣም አስደናቂ የትምህርት ፣ የሕብረት ፣ እርስበርስ ኔትወርክ የማድረግ ፣ የአምልኮ ጊዜም እግዚአብሔር ሰጥቶናል።
EBN ክርስቲያን ነጋዴዎች ታማኝ እግዚአብሔርን የሚፈሩ በእምነታቸው ጠንካራ በአይምሮ የበለፀጉ በብልሀት የሚሰሩ ውጣማ ሰዎች እንዲሆኑ እያደረገ ላለው ትልቅ ስራ በእውነት የላቀ ምስጋና ይገባዋል...

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ ክብረ በዓልን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ።የኅብረቱ ከፍተኛ አመራሮች ሰኔ 9/2018 ዓ.ም፣ በዋና ጽ/ቤ...
06/16/2026

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ ክብረ በዓልን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ።

የኅብረቱ ከፍተኛ አመራሮች ሰኔ 9/2018 ዓ.ም፣ በዋና ጽ/ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የ50 ዓመት ኢዮቤልዩ እንዲሁም የ2018 ዓ.ም የመጋቢያን ዓመታዊ ኮንፍረንስ መክፈቻና የተለያዩ ኮንፍረንሶች መከናወናቸውን ገልጸው ከሐምሌ 6/2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 9/2018 ዓ.ም የመዝጊያ ዝግጅት እንደሚደረግ አሳውቀዋል።

የክብረ በዓሉን ሂደት የሚያስተባብረውን ግብረ ኃይል የሚመሩት ወንድም የኔነህ ታደሰ፣ ኅብረቱ ከ 50 ዓመታት በፊት መስከረም 4/1968 ዓ.ም መመሥረቱን ገልጸው፣ በኅብረቱ ውስጥ ላሉ ቤተ እምነቶች እና ወንጌላውያን የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ፕሬዚዳንት መጋቢ ደረጀ ታፈሰ፣ ኅብረቱ ከ50 ዓመታት በፊት በአዳማ ከተማ የመሠረተ ክርስቶስ ይዞታ በነበረ ሥፍራ ላይ በዘጠኝ ቤተ እምነቶች መመሥረቱን አንስተው፣ በኢዮቤልዩ ክብረ በዓል ተከታታይ ሦስት ቀናት የሚኖሩ መርሐግብሮችን በመጥቀስ፣ የወንጌል አማኙ እንዲሁም የኅብረቱ አባል ቤተ እምነቶች በክብረ በዓሉ ላይ እንዲገኙ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

ከመርሐግብሮቹ መካከል የአገልጋዮች ሥልጠና፣ ከድኅረ ምርጫ ጋር በተያያዘ የኅብረቱ የሰላም አምባሳደርነት፣ ከተማ አቀፍ የወንጌል አገልግሎቶች፣ የቀደምት አባቶች እና አገልጋዮች ዕውቅና እንዲሁም የመሪዎች ጉባኤ ይገኙበታል።

የኅብረቱ ምክትል ፕሬዚዳንት መጋቢ ሰንበቱ ባሼ በበኩላቸው፣ የወንጌል አማኞች ስለዚህ መርሐግብር እንዲጸልዩ በማሳሰብ በዚህ ታላቅ ክብረ በዓል ላይ በአካል መገኘት የሚችሉ ሁሉ ደስታቸውን እንዲካፈሉ፣ ከሀገር ውጪ ያሉ ደግሞ የሚዲያ አማራጮችን በመጠቀም እንዲከታተሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ከክልል ከተሞች ለሚመጡ እንግዶች የማረፊያ እና ሌሎች አስፈላጊ ዝግጅቶች በበቂ ሁኔታ መደረጋቸውን ያሳወቁት፣ የአዲስ አበባ ኅብረት ጠቅላይ ጸሐፊ መጋቢ ሙላቱ፣ ክብረ በዓሉ ለኢዮቤልዩ ልዩ አቀባበል የምናደርግበት፣ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለቀጣዩ ኀምሳ ዓመትም በቂ ዝግጅት የምናደርግበት ነው ብለዋል።

ከዛሬ 50 ዓመት በፊት ኅብረቱ ሲመሠረት ከነበሩት አባቶች መካከል አንዱ የሆኑት ጋሽ መኮንን ደሳለኝ፣ ኅብረቱ በወቅቱ በነበሩ አባል ቤተ እምነቶች መካከል የነበረውን የዶክትሪን ልዩነት ወደ አንድነት ያመጣ እና ቤተክርስቲያን ችግር ውስጥ በነበረችበት ወቅት የተመሠረተ መሆኑን ገልጸዋል። ጋሽ መኮንን አክለውም፣ በወቅቱ በተከታታይ በቤተክርስቲያን ላይ በመጣው ስደት፣ ያልተሰደዱት ወገኖች የተሰደዱትን መያዝ የቻሉት ኅብረቱ በመቋቋሙ ምክንያት እንደሆነ አስምረው ሲናገሩ፣ ያኔ በዘጠኝ ቤተ እምነቶች የተቋቋመው ኅብረት፣ ዛሬ ከ120 በላይ ቤተ እምነቶች እንደሚገኙበት በመግለጽ ጭምር ነው።

የክብረ በዓሉ አስተባባሪ ግብረ ኃይል መሪ የሆኑት ወንድም የኔነህ ታደሰ፣ መርሐግብሩ ላይ መገኘት የሚቻለው በምዝገባ እንደሆነና አማኞች ጽ/ቤት በመገኘት ወይም በስልክ መመዝገብ እንደሚችሉ፣ ደብዳቤ እና የስልክ ጥሪ ደርሷቸው ምላሽ ያልሰጡ ቤተ እምነቶችም በቶሎ መልስ እንዲሰጡ አሳስበዋል። በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ በጎ ፈቃደኛ ወንጌላውያን ከክልል ከተሞች የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል እያደረጉ ያሉትን ትብብርም አድንቀው ተግባሩ እንዲቀጥል አበረታተዋል።

ሐምሌ 9/2018 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ኅብረቱ በሚያሳውቀው ቦታ ላይ በሚደረገው መርሐግብር፣ የኅብረቱ የመጀመሪያው መተዳደሪያ ደንብ እና ቃለ ጉባኤዎች እንዲሁም በኅብረቱ የተከናወኑ ሥራዎችን የያዘ ኅትመት በዕለቱ ለተመልካች የሚቀርብ ይሆናል።

የኅብረቱ መሪዎች ከሚዲያ አካላት የክብረ በዓሉን ቦታ እንዲሁም ወጣቱን ትውልድ በተመለከተ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

የኅብረቱ መሪዎች የክብረ በዓሉን ቦታ በቀጣይ እንደሚያሳውቁ ገልጻው፣ ወጣቱ ትውልድ ከእነርሱ ጽናትን እንዲማር እና ፈተናዎችን አልፎ ለእግዚአብሔር መንግሥት እንዲቆም አባታዊ ምክራቸውን ከባርኮት ጋር አስተላልፈዋል።

ቃልኪዳን ሙሉጌታ ለክርስቲያን ቲዩብ

 #ኢየሱስ...ከዚህ በፊት አልተዘጋም ምዕራፌ እና ድኛለሁ በሚሉ ተወዳጅ የዝማሬ አልበሞቹ እናውቀዋለን። በገጠር በከተማ በጣም በብዙ የቤተክርስቲያን መድረኮች በታለቅ ትጋት አገልግሎናል ዘማሪ...
06/15/2026

#ኢየሱስ...
ከዚህ በፊት አልተዘጋም ምዕራፌ እና ድኛለሁ በሚሉ ተወዳጅ የዝማሬ አልበሞቹ እናውቀዋለን። በገጠር በከተማ በጣም በብዙ የቤተክርስቲያን መድረኮች በታለቅ ትጋት አገልግሎናል ዘማሪ አሰግድ አበበ። አሁን ደግሞ ጌታ ረድቶት ከዘጠኝ አመት በኋላ ኢየሱስ የተሰኘ ድንቅ የዝማሬ አልበም ይዞልን መጥቷል። ቅዳሜ ሰኔ 20 በአዲስ ኪዳን ካህናት (ማርሲል) በታላቅ ድምቀት ይመረቃል።
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።
አሴ እንኳን እግዚአብሔር ረዳህ

 ...በመንፈስ ፣ በስጋ፣ በነፍስ የምንሰራበትመ የምንባረክበት፣  የምንለወጥበት ፣ የምንድንበት ደግሞም የማይረሳ እፁብ ድንቅ ትዝታዎች የምናስቀርበት ተወዳጁ መልካም ወጣት ምዝገባ ዛሬ  ጀመ...
06/15/2026

...
በመንፈስ ፣ በስጋ፣ በነፍስ የምንሰራበትመ የምንባረክበት፣ የምንለወጥበት ፣ የምንድንበት ደግሞም የማይረሳ እፁብ ድንቅ ትዝታዎች የምናስቀርበት ተወዳጁ መልካም ወጣት ምዝገባ ዛሬ ጀመረ። የዘንድሮው ደግሞ ልዩ ነው አስቀድመን እንመዝገብ....

 የአርሞንዔም ተሃድሶ ቤ/ክ ለብዙ አመታት ስታከብር የቆየችው በዓለ ኀምሳ " ታላቅ ሀገራዊ የምስጋና በዓል" ዘንድሮ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስትያናት ካውንስል ጋር በመተባበር ...
06/15/2026



የአርሞንዔም ተሃድሶ ቤ/ክ ለብዙ አመታት ስታከብር የቆየችው በዓለ ኀምሳ " ታላቅ ሀገራዊ የምስጋና በዓል" ዘንድሮ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስትያናት ካውንስል ጋር በመተባበር ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም ከ9:00 ጀምሮ መንፈስ ቅዱስን እንኳን መጣህልን በማለት የምናመስግንበት በዓል በታላቀሰ ድምቀት ተከብሯል...

 ...እንሆ መልካም ዜና ሙዚቃ መማር ለምትፈልጉ ልጆች።መና ስቱዲዮ በመጭው ክረምት የሚውዚክ ፕሮዳክሽን ኮርሶችን አዘጋጅቷል።ሙዚቀኛ መሆን ለምትፈልጉ ፣ ሙዚቃ ለምትወዱ ሁሉ ታላቅ እድል ይዞ...
06/14/2026

...
እንሆ መልካም ዜና ሙዚቃ መማር ለምትፈልጉ ልጆች።
መና ስቱዲዮ በመጭው ክረምት የሚውዚክ ፕሮዳክሽን ኮርሶችን አዘጋጅቷል።
ሙዚቀኛ መሆን ለምትፈልጉ ፣ ሙዚቃ ለምትወዱ ሁሉ ታላቅ እድል ይዞ መጥቷል እንዳያመልጣችሁ። ወላጆች ልጆቻችሁን ያለን ጥቂት ቦታ ሳይሞላ ያስመዝግቧቸው።
ለመመዝገብ፦ 0911308803 ይደውሉ

Address

Arizona City, AZ

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Christian tube - ክርስቲያን ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Christian tube - ክርስቲያን ቲዩብ:

Share