ቅድስት ማርያም ጽዋ በታይዋን

ቅድስት ማርያም ጽዋ በታይዋን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታ?

እነሆ እኛ ከእናት ሃገራችን ርቀን በታይዋን መዲና፤ታይፔ ከተማ የምንኖር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች ቀን ተቆጥሮ ጊዜ አልፎ የመጣንለትን ዓላማ ከግብ አድርስን ወደ ሀገራች እስክንመለስ እግዚአብሔርን የምናመስግንበት ስለ ሐይማኖታችን የምንወያይበት መድረክ ይሆነን ዘንድ ይህን ጽዋ መርሓ ግብር በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም ጥቅምት ፪፩፤፪፻፫ ዓ ም በታይዋን መዲና ታይፔ ፤ በታይዋን ብሔራዊ ሳይንስና ስነ መላ (ቴክኖሎጂ)ዩኒቨርሲቲ ቅጽር ግቢ ውስጥ ተመሰረተ።

10/01/2016

“እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኀኒት ተወልዶላችኋል ሉቃ.2፥11”

እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡

በታይዋን መዲና ታይፔ፤የልደት በዓል አከባበር። ታህሳስ 2008 (ጃንዋሪ 2016)

++"በመስቀሉ ገነትን የከፈለ ክርስቶስን እናወድሰዋለን" ቅዱስ ያሬድ++ለእኛ ለምናምን ቅዱስ መስቀል ወደ ሰማይ የምንደርስበት መሰላል ነው፡፡ ለማያምኑ ግን ወደ ሰማይ እንዳይደርሱ የሚሰናከሉ...
27/09/2015

++"በመስቀሉ ገነትን የከፈለ ክርስቶስን እናወድሰዋለን" ቅዱስ ያሬድ++

ለእኛ ለምናምን ቅዱስ መስቀል ወደ ሰማይ የምንደርስበት መሰላል ነው፡፡ ለማያምኑ ግን ወደ ሰማይ እንዳይደርሱ የሚሰናከሉበት እንቅፋት ነው፡፡
በክርስቶስ አምናለሁ የሚል ሁሉ እንደ አይሁድ «መስቀሉን አይግፉ» ነገር ግን እንደ ቅድስት ዕሌኒ መስቀሉን ይፈልግ፤ መስቀል ከሁሉ ነገር በላይ ነውና፡፡» http://www.kmariamtsiwa.com/2011/09/blog-post_5119.html

+++ እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ በሰላም እና በጤና ፤ እንዲሁም ፤ በደህና አደረሳችሁ አደረሰን++++“ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፏል...
12/09/2015

+++ እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ በሰላም እና በጤና ፤ እንዲሁም ፤ በደህና አደረሳችሁ አደረሰን++++

“ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፏል፤ እነሆ፣ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።” 2ኛ ቆሮ 5፣17

የታይዋን ቅድስት ማርያም ጽዋ ማህበር አባላት በቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቅዱስ ሚናስ ቤተክርስቲያን ርእሰ ዓውደ ዓመት ቅዱስ ዮሐንስን በጋራ ሲያከብሩ።

01/09/2015

******** ለማስተርስ ወይም ዶክትሬት ዲግሪ ነፃ የትምህርት እድል ፈላጊዎች ********

ስም፦ National Cheng Kung University – NCKU፣ ታይዋን

NCKU has ranked the 14th and 26th in engineering and materials science fields by 2011 Essential Science Indicators (ESI).

የስልጠና ዘርፍ፦ Communication & Journalism, Law, Education, Psychology, Political Science, Management, Commerce (including Accounting), Electrical & Electronics Engineering, Mechanical & Aerospace Engineering, Chemical Engineering, Civil Engineering, Materials Science and Engineering, Industrial Engineering & Management, Environmental Engineering, Landscape Architecture & Architecture, Art, Design, Chinese Literature, Foreign Languages & Literatures, History, Physical Education, Leisure Studies, Nursing, Public Health, others, Mathematics & Statistics, Physics & Astronomy, Chemistry, Geography & Geosciencs, Computer Science, Life science & Biology, others, Others
ለተጨማሪ መረጃ:[email protected] or [email protected]

https://admissions.oia.ncku.edu.tw/college/open.programs

********ለትምህርት ፈላጊዎች**********National Taiwan University of Science and Technology ለፀደይ 2016 እ.ኤ.አ. ት/ት ዘመን (spring semi...
31/08/2015

********ለትምህርት ፈላጊዎች**********

National Taiwan University of Science and Technology ለፀደይ 2016 እ.ኤ.አ. ት/ት ዘመን (spring semister) የነፃ ትምህርት (scholarship) አመልካቾችን እየተቀበለ ይገኛል። ሰለሆነም የማስተርስ ወይም የዶክትሬት ድግሪ የነፃ ትምህርት እድል የምትፈልጉ እና መስፈርቱን የምታሟሉ ከዝህ በታች የተመለከተውን መሲብ (link) በመጫን ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን፤ የታይዋን ቅድስት ማርያም ጽዋ ማህበር በቀጣይም በታይዋን ተመሳሳይ የነፃ ትምህርት እድል የሚሰጡ ዩኒቨርሲቲዮችን መረጃ ምናስተላልፍ መሆኑን እናሳውቃለን።

http://www-e.ntust.edu.tw/files/14-1089-39728,r641-1.php

ለተጨማሪ መረጃ:[email protected] or [email protected]

NTUST Scholarship... Taiwan Scholarship .. Financial Aid... Southeaset Asian Scholarship...

+++ ደብረ ታቦር +++💐💐💐💐💐 እንኳን ለደብረታቦር በዓል በሰላም አደረሳችሁ 💐💐💐💐💐በቤተ ክርስቲያናችን ከሚከበሩት ከዘጠኙ ዓበይት በዓላት አንዱ ደብረ ታቦር ነው፡፡ በዓሉ በየዓመቱ ነሐሴ...
19/08/2015

+++ ደብረ ታቦር +++
💐💐💐💐💐 እንኳን ለደብረታቦር በዓል በሰላም አደረሳችሁ 💐💐💐💐💐

በቤተ ክርስቲያናችን ከሚከበሩት ከዘጠኙ ዓበይት በዓላት አንዱ ደብረ ታቦር ነው፡፡ በዓሉ በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን በድምቀት ይከበራል፡፡ ታቦር ከገሊላ ባሕር በምዕራባዊ ደቡብ በኩል 10ኪ.ሜ ርቆ የሚገኝ ተራራ ነው፡፡ ይህ ተራራ ከባሕር ጠለል 572 ሜትር ከፍታ አለው፡፡ «ባርቅ የተባለው ጦረኛ ሕዝበ እስራኤልን ይዞ በመዝመት ሲራ የተባለውን የሕዝብ ጠላት በታቦር ድል ነስቶ አሸንፏል» (መሳፍንት.4፡6-14)፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ረጅም ተራራ የወጣው ብርሃነ መለኮቱን ክብሩን ለመግለጽ ነው፡፡ በዚህ ተራራ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙሴና ከኤልያስ ጋር ተነጋግሮአል፡፡ እነዚህም ሁለት ታላላቅ ሰዎች በበብሉይ ኪዳን ጊዜ ስለ ክርስቶስ ትንቢት የተናገሩ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ያስተማሩ ቅዱሳን ነቢያት ነበሩ፡፡
More ://www.kmariamtsiwa.com/2012/08/blog-post_16.html

+++ጾመ ፍልሰታ+++ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያትን አብነት አድርገው ሐዋርያት የተቀበሉትን በረከት ለማግኘት ኦርቶዶክሳዊያን የሚጾሙት ጾም ነው።http://www.kmariamtsiwa.com/2014/0...
07/08/2015

+++ጾመ ፍልሰታ+++
ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያትን አብነት አድርገው ሐዋርያት የተቀበሉትን በረከት ለማግኘት ኦርቶዶክሳዊያን የሚጾሙት ጾም ነው።
http://www.kmariamtsiwa.com/2014/08/blog-post.html

💐💐💐💐💐💐💐💐 እንኳን ደስ አላችሁ 💐💐💐💐💐💐በታይዋን የቅድስት ማርያም ጽዋ በዚህ ዓመት ለዶክትሬት ድግሪ ጥናታቸውን ያጠናቀቁ አባላቱን፤ ዶ/ር አንደበት ገዳሙ ፣ ዶ/ር ምንባለ አድማስ እና ...
27/07/2015

💐💐💐💐💐💐💐💐 እንኳን ደስ አላችሁ 💐💐💐💐💐💐

በታይዋን የቅድስት ማርያም ጽዋ በዚህ ዓመት ለዶክትሬት ድግሪ ጥናታቸውን ያጠናቀቁ አባላቱን፤ ዶ/ር አንደበት ገዳሙ ፣ ዶ/ር ምንባለ አድማስ እና ዶ/ር አማረ አረጋኅኝን እንኳን ደስ አላችሁ እያለ በዕውቀታችሁ ወገናችሁን እና ቤተክርስቲያንን የምትጠቅሙ እንድትሆኑ ስንመኝ የመንፈስ ቅዱስ መሪነት የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት እንዳይለያችሁ በመጸለይ ነው።
💐💐እግዚአብሔር ይባርካችሁ ። የአገልግሎት ዘመናችሁን ይባርክላችሁ ፠💐💐💐💐

+++++++++++ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም+++++++++++ +++++++++++በእመቤታችን ልደት ምክንያት ዛሬ ደስታ ሆነ+++++++++‹‹ወካዕበ ይደምፅ ዜና ልደትኪ እስመ ለይ...
08/05/2015

+++++++++++ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም+++++++++++ +++++++++++በእመቤታችን ልደት ምክንያት ዛሬ ደስታ ሆነ+++++++++

‹‹ወካዕበ ይደምፅ ዜና ልደትኪ እስመ ለይሁዳ ይቤሎ አቡሁ ያዕቆብ ዕጓለ አንበሳ ወበእንተዝ ሰመይኩኪ ወለተ አናብስት በከመ ይቤ ሰሎሞን ንዒ እም ሊባኖስ መርዓት ንዒ ወትወጽዒ እምግበበ አናብስት ጥቀ ግሩም ዜና ልደትኪ እም ህዝብ ዘይሜካህ ወእነገድ ኅሩይ››
ትርጉም፦ ዳግመኛም የአንበሶች ልጅ ነሽ እልሻለሁ፤የልደትሽ ዜና እንደ አንበሳ ጩኸት እንደ ሴት አንበሳ ድምጽ ነውና፤ይሁዳን አባቱ ያዕቆብ የአንበሳ ግልገል ብሎታልና ስለዚህም የአናብስት ልጅ አልሁሽ፤ሰሎሞን እንዲህ ሲል እንደተናገረ ሙሽራዪት ሆይ ከሊባኖስ ተራራ ነዪ፤ከአንበሶች ጒድጓድ ወጥተሸ ነዪ፡፡ ከምርጥ ነገድነት የተነሣ ከሚመካ ወገን የመወለድሽ ዜና እጅግ ግሩም ነው) በማለት አመስጥሮታል፡፡(አርጋኖን ዘሠሉስ)

++++ ሰማዕታተ ሊቢያ +++
20/04/2015

++++ ሰማዕታተ ሊቢያ +++

++++እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ትንሣኤ በሰላም አደረሳቸሁ++++ +++ክርስቶስ ተንስዓ እሙታን++++++المسيح قام++++++Христос Воскресе+++...
12/04/2015

++++እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ትንሣኤ በሰላም አደረሳቸሁ++++

+++ክርስቶስ ተንስዓ እሙታን+++
+++المسيح قام+++
+++Христос Воскресе+++
+++復活節快樂+++

"በእርሱ ሞት ከብረናል፤ በመለኮቱ ሞት ሳይኖርበት በሥጋ ሞተ፤ ምንጊዜም ቢሆን እርሱ የሕይወት ልጅ ሕይወት ነው፤ ይኸውም ከእግዚአብሔር አብ የተወለደው ልደት ነው፡፡ ክርስቶስ በሥጋ በመጣ ጊዜ ሞት እንዲህ ድል ተነሣ፤ መፍረስ መበስበስም በእርሱ /በክርስቶስ/ እንዲህ ጠፋ፤ ሞትም ድል ተነሣ፡፡ ሕማምን ሞትን ገንዘብ አደረገ፤በሥጋው የሞተው ሞትም የእኛን ባሕ ርይ በመዋሐዱ ነው፤ ከዚህ በኋላ ተዋሕዶውን አስረዳ፤ ሞት ሰው የመሆን ሥራ ነውና፤ ከሙታን ተለይቶ መነሣትም አምላክ የመሆን ሥራ ነውና፤ እነዚህ ሁለት ሥራዎችን /ሞትን፤ ትንሣኤን/ እናውቃለን፡፡ በሥጋ ሞተ እንዳልን ዳግመኛ በሥጋ ተነሣ እንላለን፤ ስለ ትንሣኤም የእርሱ ገንዘብ እንደሆነ፤ ሙስና መቃብርም እንዳላገኘው ይነገራል፤ ይህ ለመለኮት አይነገርም፤ የተነሣው ሥጋው ነው እንጂ፡፡" /ቅዱስ ቄርሎስ ሃይ. አበ. 72፥12፣72፥35፣ 79፥9/

+++ የጌታችን እና የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ስቅለት+++ጌታ ሆይ ለአንተ እገዛለሁ፡፡ ቸር ለሆንከው ለአንተም ምስጋናን ዘወትር አቀርባለሁ ፡፡ ብቻህን ቅዱስ ወደሆንከውም አንጋጥጣለ...
10/04/2015

+++ የጌታችን እና የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ስቅለት+++

ጌታ ሆይ ለአንተ እገዛለሁ፡፡ ቸር ለሆንከው ለአንተም ምስጋናን ዘወትር አቀርባለሁ ፡፡ ብቻህን ቅዱስ ወደሆንከውም አንጋጥጣለሁ፡፡ የሰውን ልጅ ሁሉ በምታፈቅረው በአንተ ፊትም በመገዛት እንበረከካለሁ፡፡ አንተንም አከብርሃለሁ፡፡ ምክንያቱም የአብ አንድያ ልጁ የሆንኸው፣ የፍጥረት ሁሉ ገዢ፣ ኃጢአት የሌለብህ፣ ስለእኔ ስለተናቅሁት ኃጢአተኛ ሰው ስትል፣ ኃጥአን ነፍሳት ከኃጢአት እስራት ነጻ ይወጡ ዘንድ ራስህን ለመስቀል ሞት አሳልፈህ ሰጥሃልና፡፡ ስለዚህ ድንቅ የሆነው ቸርነትህ ጌታሆይ ምን ልክፈልህ! (ቅዱስ ኤፍሬም)

Address

Taipei

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቅድስት ማርያም ጽዋ በታይዋን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ቅድስት ማርያም ጽዋ በታይዋን:

Share