ቃለ እግዚአብሔር

ቃለ እግዚአብሔር ✝️ ድምጺ ተዋሕዶ ✝️
ትምህርተ ሃይማኖት • ስብከት • ጸሎት • ታሪኽ ቅዱሳን
የተዋሕዶ እምነትና መንፈሳዊ ትምህርቶች 🙏
Follow share Link

17/08/2026

ሮሜ 12:2 " Do not conform any longer to the pattern of this world, but be transformed by the renewing of your mind. Then ...
16/08/2026

ሮሜ 12:2
" Do not conform any longer to the pattern of this world, but be transformed by the renewing of your mind. Then you will be able to test and approve what God’s will is—his good, pleasing and perfect will"

# #

“ኣብ ፈተና እውን እንተ ዀነ እምነትካ ኣይትጣስዝኸበርኩም ኣሕዋትን ኣሓትን”ታሪኽ ፖል ኣለክሳንደር፡ ከቢድ ፈተና እኳ እንተ ኣጋጠመ ተስፋ ኸይንቘርጽ ዝምህረና ኣዝዩ ዘደንቕ ታሪኽ እዩ። ኣካ...
16/08/2026

“ኣብ ፈተና እውን እንተ ዀነ እምነትካ ኣይትጣስ
ዝኸበርኩም ኣሕዋትን ኣሓትን”

ታሪኽ ፖል ኣለክሳንደር፡ ከቢድ ፈተና እኳ እንተ ኣጋጠመ ተስፋ ኸይንቘርጽ ዝምህረና ኣዝዩ ዘደንቕ ታሪኽ እዩ። ኣካላቱ ተኣሲሩ ንብዙሕ ዓመታት ኣብ ከቢድ ኵነታት ነቢሩ፤ ነገር ግን ተስፋኡ ኣየቘረጸን። ኣብታ ዕጽውቲ ቦታ ኮይኑ ክሳብ ዕለተ ሞቱ ክሳብ ጠበቃ ኮይኑ ሂወቱ ብምስጋና ወዲእዋ።

ንሕና እውን ኣብ ሕይወትና ሓደ ሓደ ግዜ ኵሉ ማዕጾታት እተዓጽወ ዀይኑ ኪስምዓና ይኽእል እዩ። ሕማም፡ ጸገም፡ ሓዘን፡ ድኽነት፡ በይነይነት ወይ ካልእ ፈተና ኼጋጥመና ይኽእል እዩ። ነገር ግን ናይ ሎሚ ፈተና ናይ ሕይወትና ናይ መወዳእታ ምዕራፍ ኣይኰነን።

“እቶም ንእግዚኣብሔር ዝተጸበዩ ግን ሓይሎም ይሕድሱ፤ ከም ንስሪ ብክንፊ ይወጹ።”
— ኢሳይያስ 40፥31

እምነት ማለት ጸገም ኣይህሉን ማለት ኣይኰነን። እምነት ማለት ኣብ ማእከል ጸገም እውን፡ “እግዚኣብሔር ምስኣይ እዩ” ኢልካ ምቕጻል ማለት እዩ።

ሃዋርያ ጳውሎስ እውን ኣብ ብዙሕ መከራ ኸምዚ ኢሉ እዩ፦
“ሓይሊ ኣብ ዝህበኒ ብክርስቶስ ኵሉ እኽእል እየ።”
— ፊልጵስዩስ 4፥13

ስለዚ ሎሚ ኣብ ከቢድ ፈተና እንተ ኣሊኻ ተስፋ ኣይትቘረጽ። ኵነታትካ ከቢድ ኪዀነ ይኽእል እዩ፤ እግዚኣብሔር ግን ካብ ኵነታትካ ይዓቢ እዩ።

“እግዚኣብሔር ናይ ልበይ ሓይልን ዋልታይን እዩ” መዝሙር 28፥7

ምናልባሽ ሎሚ መንገድኻ ከም እተዓጽወ ዀይኑ ኪስምዓካ ይኽእል እዩ። ነገር ግን ንኣኻ እተዓጽወ ዝመሰለ መንገድ ንእግዚኣብሔር እተዓጽወ ኣይኰነን። ንሱ ሓድሽ መንገድ ኪኸፍት ይኽእል እዩ።

“ብተስፋ ተሓጐሱ፤ ብመከራ ተዓገሱ፤ ብጸሎት ጽንዑ።” ሮሜ 12፥12

ስለዚ ኣይትሕደግ። ጸሊ። ተጸበ። እመን። ቐጽል።
ኣካል ኪደክም ይኽእል እዩ፤ እምነት ግን ኪጸንዕ ይኽእል እዩ።

ኵነታት ኪልወጥ ይኽእል እዩ፤ ናይ እግዚኣብሔር ቃል ግን ኣይልወጥን እዩ።
ማዕጾ ኪዓጾ ይኽእል እዩ፤ እግዚኣብሔር ግን ካልእ ማዕጾ ኪኸፍት ይኽእል እዩ።

ሎሚ ከም መወዳእታ ዝመሰለካ ነገር፡ እግዚኣብሔር ናይ ሓድሽ ምዕራፍ መጀመርታ ኪገብሮ ይኽእል እዩ።

🙏 እግዚኣብሔር ኣብ ፈተናኻ ያበርትዕካ፡ ኣብ ሓዘንካ ያጸናንዓካ፡ ጸሎትካ ይስማዕካ፡ ኣብ መንገድኻ እውን ይምራሕካ። ኣሜን። 🙏

ቃል እግዚኣብሔር
ሸር ላይክ

በፈተና ውስጥም እምነትህን አትጣልውድ ወንድሞችና እህቶች፣የፖል አሌክሳንደር ታሪክ ከባድ ፈተና ቢኖርም ተስፋ እንዳንቆርጥ የሚያስተምረን አስደናቂ ታሪክ ነው። ሰውነቱ ተገድቦ ለብዙ ዓመታት በ...
16/08/2026

በፈተና ውስጥም እምነትህን አትጣል

ውድ ወንድሞችና እህቶች፣

የፖል አሌክሳንደር ታሪክ ከባድ ፈተና ቢኖርም ተስፋ እንዳንቆርጥ የሚያስተምረን አስደናቂ ታሪክ ነው። ሰውነቱ ተገድቦ ለብዙ ዓመታት በከባድ ሁኔታ ኖረ፤ ነገር ግን ተስፋውን አልተወም።

እኛም በሕይወታችን አንዳንድ ጊዜ ሁሉም በሮች የተዘጉ ሊመስሉን ይችላሉ። ሕመም፣ ችግር፣ ሀዘን፣ ድህነት፣ ብቸኝነት ወይም ሌላ ፈተና ሊያጋጥመን ይችላል። ነገር ግን የዛሬው ፈተና የሕይወታችን የመጨረሻ ምዕራፍ አይደለም።

“እግዚአብሔርን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፎች ይወጣሉ።”
— ኢሳይያስ 40፥31

እምነት ማለት ችግር አይኖርም ማለት አይደለም። እምነት ማለት በችግር መካከልም፣ “እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ነው” ብሎ መቀጠል ነው።

ሐዋርያው ጳውሎስም በብዙ መከራ ውስጥ እንዲህ ብሏል፦

“ኃይል በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።”
— ፊልጵስዩስ 4፥13

ስለዚህ ዛሬ በከባድ ፈተና ውስጥ ከሆንክ ተስፋ አትቁረጥ። ሁኔታህ ከባድ ሊሆን ይችላል፤ ግን እግዚአብሔር ከሁኔታህ ይበልጣል።

“እግዚአብሔር የልቤ ብርታትና ጋሻዬ ነው።”
— መዝሙር 28፥7

ምናልባት ዛሬ መንገድህ እንደተዘጋ ይመስልህ ይሆናል። ነገር ግን ለአንተ የተዘጋ የሚመስለው መንገድ ለእግዚአብሔር የተዘጋ አይደለም። እርሱ አዲስ መንገድ ሊከፍት ይችላል።

“በተስፋ ደስ ይበላችሁ፤ በመከራ ታገሱ፤ በጸሎት ጽኑ።”
— ሮሜ 12፥12

ስለዚህ አትተው። ጸልይ። ጠብቅ። እመን። ቀጥል።

ሰውነት ሊደክም ይችላል፤ እምነት ግን ሊጸና ይችላል።
ሁኔታ ሊለወጥ ይችላል፤ የእግዚአብሔር ቃል ግን አይለወጥም።
በር ሊዘጋ ይችላል፤ እግዚአብሔር ግን ሌላ በር ሊከፍት ይችላል።

ዛሬ እንደ መጨረሻ የሚመስልህ ነገር፣ እግዚአብሔር የአዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ ሊያደርገው ይችላል።

🙏 እግዚአብሔር በፈተናህ ያበረታህ፣ በሐዘንህ ያጽናናህ፣ ጸሎትህን ይስማህ፣ በመንገድህም ይምራህ። አሜን። 🙏

ቃለ እግዚኣብሔር
ሸር ላይክ

+ ለምን ትቀናለህ? +   በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል፡፡ መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደረሰ መናኝ ነበር፡፡ ...
16/08/2026

+ ለምን ትቀናለህ? +

በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል፡፡ መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደረሰ መናኝ ነበር፡፡ የአጋንንቱ ጭፍራ በአለቃቸው ተመርተው ይህንን መነኩሴ ለማሳት ዘመቱ፡፡ ተራ በተራ ወደ እርሱ እየሔዱ የፈተና ወጥመዳቸውን ዘረጉበት፡፡ በዝሙት ሊፈትኑት ሞከሩ፡፡ አልተሳካም፡፡ በምግብም ሞከሩ ድል ነሣቸው፡፡ የሚያውቁትን የፈተና ስልት በተለያየ መንገድ እየተገለጹ አንዴ ሰው አንዴ መልአክ እየመሰሉ ሊጥሉት ቢሞክሩም አልቻሉም፡፡

አለቃቸው ይኼን ጊዜ በሉ እኔ የማደርገውን ተመልከቱ አላቸውና መንገደኛ መስሎ ወደ መነኩሴው ቀረበ፡፡ በጆሮው የሆነ ነግሮት ወዲያው ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ይህንን ጊዜ አጋንንቱ እያዩት መነኩሴው መንፈሳዊ ገጽታው ተገፍፎ ፊቱ በቁጣና በንዴት ሲለዋወጥ ተመለከቱት፡፡ በዚህም ተደንቀው ምን ብለህ ነው ያሸነፍከው? ብለው አለቃቸውን ጠየቁት፡፡ እርሱም እንዲህ አላቸው፦ ‘ከአንተ ጋር ያደገውና ከአንተ ጋር የተማረው ጓደኛህ እኮ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾመ’ ብዬ ነገርኩትና ወጣሁ፡፡ አሁን ልቡ በቅናት እየነደደ ነው አላቸው፡፡ አጋንንቱ በደስታ ጨፈሩ፡፡

ሰይጣን የቅናትን ኃይል ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ መጽሐፈ ቅዳሴ ሞትን ሲገልጸው ‘በሰይጣን ቅናት ወደ ዓለም የገባ’ ይለዋል፡፡ ሰይጣን በሰው ልጅ ጸጋ ቀንቶ አዳምና ሔዋንን በፈጣሪያቸው እንዲቀኑና አምላክ መሆን እንዲመኙ አድርጎ ዓለምን ያመሰቃቀለ ነውና ይህንን መነኩሴ ለመጣል ለሺህ ዓመታት ብዙዎችን ወግቶ የጣለባትን ሰይፉን መዘዘበት፡፡ መነኩሴው የእኩያውን መሾም ሲሰማ ቅናቱን መቋቋም አቃተው::

ቅናት እጅግ ክፉ ኃጢአት ነው፡፡ ሰው ቢዘሙት ቢሰክር በሥጋው ነው:: ቅናት ግን በምታስተውል ነፍሱ ውስጥ የሚበቅል መርዝ ነው፡፡ ቃየልን በየዋህ ወንድሙ ላይ ያስጨከነው ቅናት ነበር፡፡ የአቤል ስኬት ለቃየል ውድቀት መስሎ ስለተሰማው በግፍ ሊገድለው በቃ፡፡

ዮሴፍ የለበሳት ቀለምዋ ብዙ የሆነ ጌጠኛ ቀሚስ በወንድሞቹ ዘንድ የመረረ ጥላቻን አትርፋለት ነበር፡፡ አንዱ አጊጦ አምሮ ሲታይ ቢሞትና ቢገላገሉት ደስ የሚላቸው የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡

ዮሴፍም አርፎ አልተቀመጠም፡፡ እየሔደ ሕልሙን ይነግራቸው ነበር፡፡ ስለ ሕልሙም የበለጠ ጠሉት ይላል፡፡ ወዳጄ ሕልምህን ዝም ብለህ ለሰዎች አትዝራ፡፡ ሕልም ስልህ ተኝተህ የምታየውን ብቻ ማለቴ አይደለም፡፡ ራእይህን ፣ ተስፋህን ዕቅድህን ሲያውቁ የሚንገበገቡ የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡ ፍቺው ባይገባቸውም ባልተፈታ ሕልም ይጠሉሃል፡፡ ምንም ነገር ሳታደርግ እንኳን "ለምን አለምከው?" ብለው ጥርስ ይነክሱብሃል፡፡ ዮሴፍ ግን ይኼ ስላልገባው ነገራቸው፡፡ ወዳጄ አንተም ሕልምህን እንደ ዮሴፍ በየዋህነት የምትዘራ ከሆንህ እንግዲህ የዮሴፍ አምላክ ይጠብቅህ፡፡

ቅናት እጅግ ከባድ ነው፡፡ እረኛው ዳዊት ጎልያድን የገደለ ዕለት የተዘፈነለት መዘዘኛ ዘፈንም ነበረ፡፡ ‘ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ’ ብለው ዘፈኑለት፡፡ ይህች ዘፈን በሳኦል ጆሮ ስትደርስ ዳዊት ላይ ብዙ ጦር አስወረወረች፡፡ ሳኦሎች ሌላ ሰው ከእነርሱ በላይ ሲመሰገን የሰሙ ዕለት በቅናት ታውረው ገበታ ላይ ሳይቀር ሰይፍ ይመዛሉ፡፡

የጠፋው ልጅ ወንድምን አስበው፡፡ (ሉቃ 15:20) ወንድሙ ከጠፋበት ተመልሶ ደስታ ሲደረግ እርሱ ግን ከፍቶት ውጪ ቁጭ አለ፡፡ ወዳጄ ቅናት ከቤተ ክርስቲያንና ከእግዚአብሔር መንግሥት ያስወጣል፡፡ የሌላው ስኬት ካበሳጨህ እንደጠፋው ልጅ ወንድም ውጪ ቁጭ ብለህ አፈር እየጫርክ ‘እምቢየው አልገባም’ እያልክ እያልጎመጎምክ ትቀራለህ፡፡

ክርስቶስ ላይ አይሁድ ያቀረቡት ትችት ሁሉ ለሕግ ከመቆርቆር ሳይሆን ከቅናት ነበር፡፡ ጲላጦስ እንኳን ‘በቅናት አሳልፈው እንደሠጡት ያውቅ ነበር’ ይላል፡፡ አንዳንዴ ሰዎች ቅናታቸውን በሌላ ነገር እንደ አይሁድ ሸፍነው ትችት ያቀርባሉ፡፡ ለእግዚአብሔር ሕግ እንደተቆረቆሩ ፣ ለሥርዓቱ እንዳዘኑ መስለው ውስጣቸው ያለውን ቅናትና ጥላቻ ያንጸባርቃሉ፡፡

የሰንበት መሻር ፣ ለቄሣር ግብር መከፈል ፣ የመቅደሱ በሦስት ቀን ፈርሶ መሠራት እንዳንገበገባቸው እርር እያሉ ቢናገሩም እውነታው ግን ቅናት ነው፡፡ ‘የቤትህ ቅናት በላኝ’ እንዳለው ጌታ በየዘመኑ የሰዎች ቅናት ብዙ ንጹሐንን ትበላለች፡፡

ወዳጄ በሌላው ትቀና እንደሆን አሁኑኑ ከዚህ ውስጥን በልቶ ከሚጨርስ ካንሰር ራስህን አድን፡፡

ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ በምድር ላይ እግዚአብሔር የፈጠረው አንተን የሚመስል ሌላ ሰው የለም፡፡ ካንተ ቀድሞም በትክክል አንተን የሆነ ሰው አልተፈጠረም ለወደፊትም አይፈጠርም፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞ ያልሠራው ደግሞም የማይሠራው ምርጥ ዕቃው ነህና ራስህን ከሌላ ጋር አታወዳድር፡፡

ለአንተ ብቻ የሠጠው ጸጋ አለና ሌሎችን መመልከት ትተህ ውስጥህ ያለውን ውድ ማንነት ቆፍረህ አውጣ፡፡ ያንተ ሕይወት ቁልፍ የተቀበረው አንተው ውስጥ ነው፡፡ ሌሎችን ረስተህ ወደ ራስህ ጠልቀህ ግባ፡፡ መብለጥ ከፈለግህም አሁን ያለውን ራስህን ብለጠውና ሌላ ትልቅ አንተን ሁን፡፡

በቅናት እንዳትቃጠል ሌሎችን ሰዎችንም ውደዳቸው፡፡ ከወደድሃቸው ‘ፍቅር አይቀናም’ና የእነርሱ ስኬት የደስታህ ምንጭ ይሆናል፡፡ የቅናት ስሜት ሲሰማህም ‘ቀናተኛ ልቤን ፈውስልኝ’ ብለህ ለምነው፡፡

‘በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን’ ሮሜ 13፡13

መነሻ ሃሳብ:- የአንድ በቅናት ጦስ ሊያበሩ ሲችሉ የከሰሙ ሰው ታሪክ

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!

ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-

የጽሑፍ ምንጭ ድ. ሄሎክ ሃይለ
ቃለ እግዚኣብሔር

13/08/2026

Adress

Gothenburg
43531

Aviseringar

Var den första att veta och låt oss skicka ett mail när ቃለ እግዚአብሔር postar nyheter och kampanjer. Din e-postadress kommer inte att användas för något annat ändamål, och du kan när som helst avbryta prenumerationen.

Kontakta Heliga Platser

Skicka ett meddelande till ቃለ እግዚአብሔር:

Genvägar

Dela