ይርባ ቤቴል ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን Yirba betel Kale hewot church

  • Home
  • Ethiopia
  • Yirba
  • ይርባ ቤቴል ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን Yirba betel Kale hewot church

ይርባ ቤቴል ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን Yirba betel Kale hewot church " እኛም በክርስቶስ ፍጹም የሚሆን ሰውን ሁሉ እናቀርብ ዘንድ ሰውን ሁሉ እየገሠጽን ሰውንም ሁሉ በጥበብ ሁሉ እያስተማርን የምንሰብከው እርሱ ነው።"
(ወደ ቆላስይስ ሰዎች 1:28)
(2)

በቀን 18/08/2018ዓ.ም  በይርባ ቤቴል ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን እሁድ  በመደበኛ ፕሮግራም ላይ የተማርነው የእግዚአብሔር ቃል:🔶የዕለቱ አገልጋዮች📖  #መልዕክት አቅራብ:-       ...
26/04/2026

በቀን 18/08/2018ዓ.ም በይርባ ቤቴል ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን እሁድ በመደበኛ ፕሮግራም ላይ የተማርነው የእግዚአብሔር ቃል:
🔶የዕለቱ አገልጋዮች
📖 #መልዕክት አቅራብ:-
#ወ/ዊ ጌቱ አማኑኤል
#በመዝሙር:- /መዘመራን
#ፓ/ር_ዘማሪ_ኤርምያስ_ጴጥሮስ
➥ፕሮግራምን በመምራት :- አቶ አምባይቸው አበበ

#የመልዕክቱ ርዕስ:- ስለ ክርስቶስ ዋጋ ለመክፈል መዘጋጀት።
👉መነሻ ጥቅስ፦ 1ጴጥ 4:12-19

#መግቢያ:-
ሐዋሪያ ጴጥሮስ የኢየሱስ ሐዋሪያት መካከል አንዱ ስሆን ይህን መጽሐፍ የፃፈውም እርሱ ነው። የተፃፈበትን ጊዜ በተመለከተ ከ65-67ዓ.ም ገደማ የተፃፈ እንደሆነ የመጽሐፍ ቅዱስ ታርካዊ ዳራው ያሳያል።
➥የመጽሐፉ ተቀባዮች ስለ ክርስቶስ መከራ እየተቀበሉ በተለያዩ ሀገራት ውስጥ ተሰዶ ለተበተኑት ነው።
➥የመጽሐፉ ዓላማው:- በልዩ ልዪ መከራና ስደት ውስጥ እንኳን ብሆኑ በተከተሉት እውነተኛ ሕይወት ወደኋላ እንዳይሉ ፣ በእምነታቸው እንድፀኑ ለማበረታታት።

በዚህ ክፍል ጴጥሮስ ከእርሱ ጋር የእግዚአብሔርን መንግስት ክብር ለመውረስ በክርስቶስ የተጠሩትን እስከ መጨረሻ ድረስ መሄድ እንድችሉ መመሪያ ይሰጣቸዋል።

ጴጥሮስ በዚህ ቦታ ስለ መከራ ፤ ስለ ፈተና ፣ ስለ ፍርድ ይናገራል። በዚህ ሕይወት ስታልፉ ለማንም ያልደረሰ አስጨናቅ ነገር እንደደረሰባችሁ አርጋችሁ አትደነቁ ብሎ ይመክራቸዋል።

📌ስለ መከራ፦ የክርስቶስን መከራ መካፈል (ስለ ኢየሱስ መከራን መቀበል) ክብሩን እንድንካፈልና በመጨረሻም የክርስቶስን ደስታ እንድንካፈል ያደርገናል። መከራውን ታግሶ የማይካፈል የመጨረሻውን ክብርና ደስታ ሊካፈል አይችልም።
✔ጌታችን ኢየሱስ በሥጋው መከራን እንደተቀበለ መጨረሻም እንደ አሸነፈ አሸናፊ ለመሆን መከራን መቀበልም እንዳለ ማወቅ ያስፈልገናል።ቁ.1

📌ስለ ፈተና ፦ ከእኛ በፊት ተፈትኖ ያለፈ የከበረ ጌታ አለን።
እግዚአብሔር ሰውን ይፈትናልን?
➥አዎ ግን በክፉ አይፈትንም ይልቁንስ ክብሩን ለመግለጥ ፣ እምነታችንን ለማጽናት እንደ አብርሃም ፣ እንደ ኢዮብ ለመልካም ይፈትናል። በእግዚአብሔር ተፈትኖ የሚሸነፍ ፣ የሚወድቅ የለም። ምክንያቱም በፈተና ጊዜ እርሱ አብሮት ሆኖ ስለምረዳው።

✔ስለ ፍርድ፦ 1) ከእርሱ ጋር መከራን ለምቀበሉት እና በልዩ ልዩ ፈተና ለሚያልፉት ክርስቶስ በጽድቅ ይፈርድላቸዋል። ከፍርዱ የተነሳ ይከብራሉ ይደሰታሉ።

2) ለወንጌል እውነት የማይታዘዙ እና ልባቸውን ላደነደኑ ዓመፀኞችና ኃጢአተኞች እርሱ በጽድቅ ስፈርድ መገኛቸው ያስፈራል። ለእነርሱ የፍርዱ ውጤት እጅግ አስፈር ይሆንባቸዋል።(ከቁ.17-18)

በዚህ ሁሉ ስናልፍ እንደ እሳት በሚያቃጥል መከራና ፈተና ውስጥ ብናልፍም የምረዳንና የሚያጸናን የእግዚአብሔር መንፈስ ስላለን አንጠፋም።
" ስለ ክርስቶስ ስም ብትነቀፉ የክብር መንፈስ የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ላይ ያርፋልና ብፁዓን ናችሁ።"(ከቁ.14)

ስለዚህ እየተፈተንክም እየተጨነክም ስለ ክርስቶስ መከራን ተቀበል ትከብራለህና።

በቀን 11/08/2018ዓ.ም  በይርባ ቤቴል ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን እሁድ  በመደበኛ ፕሮግራም ላይ የተካፈልነው የእግዚአብሔር ቃል:🔶የዕለቱ አገልጋዮች📖  #መልዕክት አቅራብ:-      ...
19/04/2026

በቀን 11/08/2018ዓ.ም በይርባ ቤቴል ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን እሁድ በመደበኛ ፕሮግራም ላይ የተካፈልነው የእግዚአብሔር ቃል:
🔶የዕለቱ አገልጋዮች
📖 #መልዕክት አቅራብ:-
#አገልጋይ አቶ ጢሞቴዎስ ኡራጎ
#በመዝሙር:- /መዘመራን
➥ፕሮግራምን በመምራት :- አቶ አብርሃም ባዊሶ

#የመልዕክቱ ርዕስ:- ድል አድራጊው ንጉሥ!
👉መነሻ ጥቅስ፦ ራዕይ 19:1-6 : 17፥14

#መግቢያ:-
የዮሐንስ ራዕይ ጸሐፍ ኢየሱስ ይወደው የነበረው ደቀ መዝሙር ዮሐንስ ነው። ሐዋሪያ ዮሐንስ ከመጽሐፍ ቅዱስ ከ66ቱ መጽሐፍት መካከል 5 መጽሐፍትን እድጽፍ በእግዚአብሔር የተመረጠ ታማኝ ጸሐፊ ነው። ይህ መጽሐፍ በትንቢት መልክ የሆነውን ፣ ቶሎ ሊሆን ያለውን በስዕል መልክ ጥልቅ የሆነ ትምህርት ይሰጣል።

ዮሐንስ ይህን የመጨረሻውን መጽሐፍ ራዕይን በፃፈ ጊዜ በእስያ ውስጥ ባለች ፍጥሞ ደሴት ተፈርዶበት ታስሮ ባለበት ጊዜ ነወ።

በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ዮሐንስ ኢየሱስን የገለጠበት ያደመቀበት ያሸበረቀበት መንገድ እጅግ ያስደንቃል።
1) ኢየሱስን በሰዎችና በእግዚአብሔር መካከል የቆመ የታመነ ሊቀ ካህን ነው ይለዋል፣ (ከምዕ. 1-3)
2) ኢየሱስን የታረደ በግ ይለዋል፣
(ከምዕ 4-5) ዮሐ 1፥29
✔ ስለ ሰው ልጆች ኃጢአት የታረደ የእግዚአብሔር በግ

3) ኢየሱስን እውነተኛ ፈራጅ(የጽድቅ ፈራጅ) ነው ይለዋል። (ከምዕ. 6-18) ሮሜ 2፥19

4) ድል ያደረገ ንጉሥ። (ምዕ. 19)
✔ በጉ የጌቶች ጌታ ስለሆነ ድል ይነሣል።
✔ ድል አድራጊው ጌታ ብቻ ሳይሆን በእርሱ፦ ድል ይነሳሉ/ያደርጋሉ።
5) በክብር የሚመለስ/የሚመጣ ጌታ ይለዋል።(ከምዕ 20-22)

ኢየሱስ የአባቱን ፈቃድ ለማከናወን ወደ ምድር በመጣ ጊዜ የባርያን መልክ በመያዝ በውርደት ነበር የመጣው። የአባቱን ፈቃድ ስለ ሰው ልጆች ኃጢአት አስፈላጊውን ዋጋ ውርደት በምመስል በሥጋው ሞቱ ፈጸመው። በእግዚአብሔር ኃይል ከሞት በኩር ሆኖ በክብር ተነሳ። ሐዋሪያቱ እያዪት ወደ ሰማይ በክብር የሄደው የድል ጌታ የወጉት ሁሉ እያዩት በክብር ተመልሶ ይመጣል።

🙏ድል አድራጊው ንጉስ ኢየሱስ!

ነገ 8:00 ስሆን መጽሐፍ ቅዱስ እና ማስታወሻ ደብተራችሁን በመያዝ በቤቴል እንገናኝ።
18/04/2026

ነገ 8:00 ስሆን መጽሐፍ ቅዱስ እና ማስታወሻ ደብተራችሁን በመያዝ በቤቴል እንገናኝ።

  :00 ሰዓት ጀምሮ። ።
15/04/2026


:00 ሰዓት ጀምሮ።

በቀን 04/08/2018ዓ.ም  በይርባ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዕለተ እሁድ  በትንሣኤው ማለዳ ላይ የተካፈልነው የእግዚአብሔር ቃል:🔶የዕለቱ አገልጋዮች📖  #መልዕክት አቅራብ:-       ...
12/04/2026

በቀን 04/08/2018ዓ.ም በይርባ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዕለተ እሁድ በትንሣኤው ማለዳ ላይ የተካፈልነው የእግዚአብሔር ቃል:
🔶የዕለቱ አገልጋዮች
📖 #መልዕክት አቅራብ:-
# ወንገላዊ ኃ/ማሪያም ሀሜሶ
#በመዝሙር:- /መዘመራን
➥ፕሮግራምን በመምራት :- የቤተ ክርስቲያንቱ ሰብሳብ
አቶ ተመስገን ጴጥሮስ
#የመልዕክቱ ርዕስ:- ኢየሱስ ተነስቷል እንጂ አልተሰረቀም ።
👉መነሻ ጥቅስ፦ ሮሜ 6:9 ዘፍ 3:1-17

#መግቢያ:-
ሃለሉያ እንኳን ደስ አለን። የደስታችን ምክንያቱ ምንድ ነው ከተባልን የኢየሱስ ከሞት መነሳቱ ነው።
✔ ደስ ይበለን! ከሞት ፍርሃት ፣ ከኃጢአት ባርነት ፣ከጨለማው አገዛዝ/ሥልጣን ፣ ከእግዚአብሔር ጽድቅ ቁጣ ፣ ከገሃነም ፍርድ ፣ ከሁለተኛ(ከዘላለም) ሞት ሊያድነን የሞትና የስዖል መክፈቻ ያለው ጌታ የሰጠውን የትንሣኤውን ተስፋ ለማረጋገጥ ከሙታን በኩር ሆኖ ተነስቶአልና ደስ ይበለን።

📖 እግዚአብሔር ሰውን በምድር ላይ እርሱን እንድያመልክና ለፈቃዱ እንድታዘዝ መልካምም እንድያደርግ ፈጥሮታል። ይሁን እንጂ ሰው ለተፈጠረበት ዓላማ ፀንቶ መኖር አልቻለም። በእግዚአብሔር ላይ አመጸ። ከእርሷ እንዳይበሉ የታዘዙበትን በማድረግ ተላለፈ። ከዚህ የተነሳ ከእግዚአብሔር ጋር ከነበረው ጠናማ ኅብረት ተቋረጠ ፤ ከእግዚአብሔር ሕይወት ተለዩ። ይህን በሰይጣን ተንኮል ኃጢአት በመስራት የጠፋውን ሰው በዚያው ይቅር/ይጥፋ ብሎ አልተወውም። የጠፋውን በኃጥአት የሞተውን ሰው የሚያድንበትን መንገድ ዘረጋለት። (ዘፍ 3:15)

የተባለው ዘመን እስክደርስ ድረስ ሕዝቡ ከኃጥአታቸው እንድድኑ ብዙ መመርያ ብሰጣቸውም ከመተላለፍ ፍጹም ልሆኑና ልድኑ አልቻሉም።

ዘመኑ በደረሰ ጊዜ ክርስቶስ በሥጋ ወደ ምድር መጣ። ኃጢአት የሚጠይቀውን ዋጋ ሁሉ በሥጋው ሞቱ ከፈለ።
በመጽሐፍ ቅዱሳች ውስጥ ብዙ ሰዎች ሞቶ ተስቷል ይሁን እንጂ ሁሉም ተመልሰው ሞቷል።
። ይህ ከሞት የተነሣው ኢየሱስ ለእኛ ጌታችን ነወ።
(ሉቃስ 24:1-8)

✔ እንድሞት አሳልፈው የሰጡት የአይሁድ ፃፍዎች እና ፈርሳውያን ከሞተና መቃብር ከወረደ ቦኋላም እነሳለሁ ብሎ ነበርና ይነሳ ይሆናል በማለት መቃብሩን በብርቱ ጠባቅዎች አስጠበቁ። #መነሳቱን በሰሙ ጊዜ የሚሆኑትን አጥተው በቦታው የነበሩትን ወታደሮች ብዙ ገንዘብ በመክፈል ምስጥሩ እንዳይገለጥ አሉአቸው።
! ።
ኢየሱስ ከሙታን ከተነሳ በኃላ ለደቀ መዛሙርቱ ታላቅ ተልዕኮ ሰጥቷቸዋል። ዛሬ እኛም እንድናደርግ የተሰጠን አደራ ነው። እርሱም:-
1) ወደ ዓለም ሁሉ እንዲንሄድ እና በወንጌል ሰውን ሁሉ እንድንደርስ፣(ማቴ 28:18-20)
2) በሞቱ ኃጢአታችንን ይቅር እንዳለን እኛም የበደሉንን ይቅር እንድንል ታዘናል።(ማቴ 6:14 ሉቃ 23:34 ሐ/ሥ 7:60 ቆላስያስ 3:12)

🙏 እንደተናገረው ተነስቷል! ትንሣኤ ሆኖልናል።

11/04/2026

#እልልልልልልልልልል! !
🔶በክርስቶስ ኢየሱስ ሞት እና ትንሣኤ ፤
እና የተወደዳች ፣ ትንሣኤን ያገኛችሁ ፣ ሞት የተሻረላችሁ ፣ ድቅድቁ ጨለማ የተወገደላችሁ ፣ የእግዚአብሔርን ልጅነት ያገኛችሁ ፣ መንግስቱን ለመወረስ ሕያው ተስፋ የተቀበላች ፣ በቅርብና በሩቅ ያላችሁ የእግዚአብሔር ልጆች(ቅዱሳን) በሙሉ እንኳን ለዚህ ታላቅ ምስጥር ለተገለጠበት ፤ ሞት በሕወይት ለተሻረበት/ለተሸነፈበት ለፋስካው በዓል እንኳን በሰለም አደረሳችሁ።
#እንኳን ደስ አለን/አላችሁ ኢየሱስ ተነስቷልና በዓሉ ለደስታና ለትንሣኤ ይሁንላችሁ።

(የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 24)
----------
2፤ ድንጋዩንም ከመቃብሩ ተንከባሎ አገኙት፥
3፤ ገብተውም የጌታን የኢየሱስን ሥጋ አላገኙም።
4፤ እነርሱም በዚህ ሲያመነቱ፥ እነሆ፥ ሁለት ሰዎች የሚያንጸባርቅ ልብስ ለብሰው ወደ እነርሱ ቀረቡ፤

5፤ ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ፥ እንዲህ አሉአቸው። ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።

🙏መልካም የትንሣኤ በዓል!

09/04/2026
በቀን 27/07/2018ዓ.ም  በይርባ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዕለተ እሁድ ጧዋት በመደበኛ ፕሮግራም ላይ የተካፈልነው የእግዚአብሔር ቃል:🔶የዕለቱ አገልጋዮች📖  #መልዕክት አቅራብ:-   ...
05/04/2026

በቀን 27/07/2018ዓ.ም በይርባ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዕለተ እሁድ ጧዋት በመደበኛ ፕሮግራም ላይ የተካፈልነው የእግዚአብሔር ቃል:
🔶የዕለቱ አገልጋዮች
📖 #መልዕክት አቅራብ:-
#አገልጋይ አቶ ጴጥሮስ ድንጋሞ
#በመዝሙር:- /መዘመራን
➥ፕሮግራምን በመምራት :- ወ/ሮ አስቴር በዴራ

#የመልዕክቱ ርዕስ:- እኛ የብርሃን ልጆች ነን እንጂ የጨለማ ልጆች አይደለም።
👉መነሻ ጥቅስ፦ ት/ኢሳያስ 66:1-22
ዮ.ራዕይ 21:25

#መግቢያ:-

ነቢዩ ኢሳያስ የደቡብን እስራኤል ይሁዳን እና የብንያም ልጆች ያገለገለ ከታላላቅ ነቢያት ውስጥ አንዱ የሆነና በጣም ሰፍ ይዘት ያለውን መጽሐፍ የጻፈው ብርቱ ነቢይ ነው። ታላላቅ ነቢያት ውስጥ እንድመደብ ያደረገውም ነገር የመጽሐፉ ይዘትና ጥልቀት ነው። መጽሐፉ 66 ምዕራፍ ያሉት ስሆን በይዘቱ መሠረት በሁለት ይከፈላል።
1) የእስራኤል ልጆች በኢየሩሳሌም የሚኖሩ የይሁዳ እና የብንያም ነገድ የሆኑቱ በተደጋጋም የእግዚአብሔርን ሥርዓት እና ሕግ በመተላለፋቸው እና ባለመታዘዛቸው ልደርሳቸው ስለምችል ፍርድ።(ከምዕራብ 1-39)
2) እግዚአብሔር በአባቶቻቸው ዘመን የገባላቸውን ቃል ኪዳን አስቦ ከምደርሳቸው ፍርድ በጽድቅ ፈርዶ ልያድናቸው ፣ ልታደጋቸው እና እንደገና እንደሚያጽናናቸው ያስተምራል።
(ከምዕ 40-66)

#በዚህ ክፍል እግዚአብሔር ለኢየሩሳሌም ሕዝብ ኪዳኑን አስቦ በጽድቅ ፈርዶ የተወሰደባቸውን ምርኮ እንዴት እንደምመለስላቸው ተስፋ ይሰጣቸዋል።

ከቁ.1-22 ድረስ የተዘረዘሩ እጅግ ብዙ ተስፋዎች አሉ።
#ከተሰጡትም ተስፋዎች፦
1) የጨለማሽ ጊዜ አልፎል ፣ ከእንግዲህ ተነስተሽ አብሪ። (ከቁ. 1-3 ፤ 19-20)
2) ምርኮሽ ፥በረከትሽ ይመለሳል ፤ ልጆችሽም ከተበተኑበት ሁሉ ይሰበሰባሉ ። (ከቁ.4- 6 ፤ 11 ፤ 14)
3) የአምላክሽ ክብር በአንቺ ላይ ስለምወጣ ደስታሽ ፍጹም ይሆናል ፣ ትከብሪያለሽም።( ከቁ.5 ፤ 9 ፤ 15)
4) አምላክሽ ፊቱን ወደ አንቺ ስለመለሰ መጻተኞች ቅጥርሽን ይሰራሉ ፣ ነገስታትም ያገለግሉሻል። (ቁ. 10 ፤ 16-17)
5) ከዚህ በኋላ በሮችሽና ቅጥሮችሽን ዳር ድንበርሽን እኔ ስለምጠብቅ ሠላምሽ የበዛ ይሆናል። (ከቁ. 18)
6) ብርቱ ሕዝብ አደርግሻለሁ ይላታል። (ከቁ. 21-22)

ያነ ይህ ቃል የተነገረዉ በብሉይ ክዳን ዘመን በኢየሩሳለም ለሚኖሩት ለእስራኤል ልጆች ነበር። ዛሬ ግን ለይርባ ቤቴል ቤ/ያንና ለመላዉ ኢትዮጵያ ሆኖሃል:: የእግዚአብሔር ብርሃን ሁል ጊዜ በእኛ ላይ ነዉ።
ለዘላለም ደግሞ እግዚአብሔር የከፈተዉ በር ሁልጊዜ ክፍት ነዉ::
👉 እግዚአብሔር ለእኛ የከፈትልን በር
✔ ሁል ጊዜ ክፍት የሆነ
#የማይቋረጥ በረከት ያለባተ
📌 ቤጉ ኢየሱስ የሚያቤራት ናት
ይህ ብርሃን ሁልጊዜ እንድበራልን እግዚአብሔርን መፍራት አለብን :: እግዚአብሔርን የሚፈሩ እሳት ውስጥ ብገቡም ይወጣሉ ፣ ባህር ተከፍሎ ይሻገራሉ እንጂ ሰጥመው አይቀሩም ምክንያቱም እግዚአብሔርን ስለምፈሩ::
✔ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ስጸልዩ ፀሎታቸዉ መልስ ያገኛሉ ፣ በሰላምም ይኖራሉ::
እግዚአብሔርን የሚፈሩ ቤተሰብ ለልጆቻችዉ መልካም ምሳሌ ይሆናሉ:: ስለዝህ ባልና ሚስት በቤታችሁ እግዚአብሔርን በመፍራትና እንደቃሉ በመኖር ለሚመጣው ትውልድ መልካም ምሳሌ ልትሆኑ ይገባል።
📌 ይህም ባል ለሚስቱ መልካም በማድረግ ፣
📌 ሚስትም ለባልዋ መልካም ሚስት በመሆን ነው።

👉 ስለዚህ ልጆቼ በ ት/ኢሳያስ 60:22 ላይ ቃሉ እንደምነግረን ሁላችንም በመጀምሪያ በእግዚአብሔር ፊት ዝቅ ስንል አምላካችን ደግሞ ከሁሉም በላይ ከፍ ያደርገናል::
📖ልጆቼ የምመክራችሁ ለእግዚአብሔር ቃል እንድትታዘዙ ፣ የቤ/ያን መሪዎችና የቀደሙ አባቶቻችሁን እንድትሰሙ ፣ ከቤተክርስቲያ አንዳትርቁ እና እርስበርሳችሁ እንድትዋደዱ ነወ። ይህን ሁሉ ስታደርጉ የእግዚአብሔር ብርሃን በላያችሁ ለዘላሌም ይበራል::

#ማጠቃለያ:-
እግዚአብሔር መቼም ብሆን የቃል ኪዳን ሕዝቡን አይጥልም። የወደቁ፣ የተጣሉ ፣ የተረሱና የተተው ብመስላቸውም የእንደገና አምላክ ኪዳኑ አስቦ ስነሳ የጨለማውን ወራቶቿን ያስረሳታል ምርኮዋንም ሁሉ ይመልስላታሌ።

🙏እግዚአብሔር በብዙ መከራና ጭንቅ ያለችውን ምድራችንን ያስብ። በጦርነት እያለቁ ያሉትን ሁሉ ኃያሉ አምላክ እርሱ ያስባቸው ሠላምንና እርቅ ያውርድልን።

🙏 ሠላም ለሀገራችን ሠላም ለምድራችን ይሁን! የእግዚአብሔር የክብሩ ብርሃን በዙሪያችን ይብራልን! አሜን!

በቀን 20/07/2018ዓ.ም  በይርባ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዕለተ እሁድ ጧዋት በመደበኛ ፕሮግራም ላይ የተካፈልነው የእግዚአብሔር ቃል:🔶የዕለቱ አገልጋዮች📖  #መልዕክት አቅራብ:-   ...
29/03/2026

በቀን 20/07/2018ዓ.ም በይርባ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዕለተ እሁድ ጧዋት በመደበኛ ፕሮግራም ላይ የተካፈልነው የእግዚአብሔር ቃል:
🔶የዕለቱ አገልጋዮች
📖 #መልዕክት አቅራብ:-
#አገልጋይ አቶ ሽመልስ ወንድዬ
#በመዝሙር:- /መዘመራን
➥ፕሮግራምን በመምራት :- አቶ ባራራ ቆርሳ

#የመልዕክቱ ርዕስ:- ቃሉን ስሙ ለሰማችሁትም ቃል ታዘዙ/ተገዙ።
👉መነሻ ጥቅስ፦ ዘፍ 22: 1-19 ምሳሌ 1:33

#መግቢያ:-
በዛሬው ትምህርታችን የእግዝአብሔርን ቃል ስለመስማት እንዲሁም ስለመታዘዝ እንማማራለን። በመስማትና በመታዘዝ ውስጥ ያሉ በረከቶችንም እናያለን።
በዚህ ክፍል እግዚአብሔር ለራሱ ልዩ ፣ የሚሰማውንና የሚታዘዝለትን በኩር የሚሆን ሕዝብ ለማዘጋጀት አስቦ የጠራው የአብርሃምን ታርክ እንናገኛለን።
በምዕ.12:1 ላይ አብርሃም ለእግዝአብሔር ጥሪ(ለሰማው ድምጽ) የሰጠውን ተግባራዊ ምላሽና መታዘዙን ያሳየናል።
➥እግዚአብሔር አብርሃምን ጠርተው ዝም ብሎ አልተወውም ኪዳን ገብቶለት አወጣው እንጅ።
📌የገባለትም ኪዳን ይህ ነበር
(ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 12)
2፤ ታላቅ ሕዝብም አደርግሃለሁ፥ እባርክሃለሁ፥ ስምህንም አከብረዋለሁ፤ ለበረከትም ሁን፤
3፤ የሚባርኩህንም እባርካለሁ፥ የሚረግሙህንም እረግማለሁ፤ የምድር ነገዶችም ሁሉ በአንተ ይባረካሉ።

እግዚአብሔር ጠርቶት እያለ አብርሃም ያለ ልጅ ብዙ ዓመታትን ኖረ፣ አረጄ ፣ ደከመ ሳራም እንደዚሁ ፈጽማ ተስፋ በመቁረጥ ወደ አጋር ታመለክት ነበር።
🔶በመጨረሻም ተናግሮ ማድረግን የሚችል ፣ የገባውን ኪዳን የማይረሳ የሚፈጽም ፣ ጠርቶ ያወጣው የለየው የዘመናት ሁሉ ጌታ ታምራትን አደረገ ሳራም ጸንሳ ይስሃቅን ወለደችለት።
እግዚአብሔር ይህን የሚወደውንና በተስፋው ኪዳን የተገኘውን ልጅ ይስሃቅን እንድሠዋለት አብርሃምን ጠየቀው። ከባድ ፈተና ነው። አብርሃም ግን ከሳራም ጋር አልተማከረም ሊያደረገው በልቡ ወሰነ። ከይስሃቅ ይልቅ እግዚአብሔርን ይወደዋልና።

➥ይስሃቅ ማነው?
1)በምወዳት በሳራ የተወለደለት የተወደደ ልጅ፣
2) የተስፋ ቃል ልጅ ፤
3) በሽምግልናው ዘመን ያገኘው ልጁ ነው።

✔ይህን ማድረግ ቀላል አይደለም።

እግአብሔር ከእርሱ በላይ የሚንወድ አንዳች ነገር እንድኖር እንደማይፈልግ ልያስተምረን አብርሃምን ፈተነው። አብርሃምም ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅርና ቦታ ለማንም ማጋራት እንደሌለብን ምሳሌ ልሆነን ፈተናውን በመታዘዝ በድል ተወጣ። ከይስሃቅም የቀረበለትን ጥያቄ በእምነት እግዚአብሔር ያዘጋጃል ብሎ መልሶለት አለፈ በመጨረሻም የተማመነበት ጌታ አላሳፈረውም አዘጋጀለት። የአብርሃም አምላክ ይባረክ🙏
📌የእግዚአብሔርን ቃል ለምሰሙና ለሚታዘዙት ምን ይሆንላቸዋል?
1) ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸው ኅብረት ይጠነክራል፣ (22: 12)
2) እግዚአብሔር ቃል ኪዳኑ እንደገና ያድሳል(22: 17)
3) እግዚአብሔር የሰጠውን በረከት ያበዛለታል እንጅ አይነሳውም/አይወሰድበትም።(22:10-13)
4) ያርፋል እንጅ በምንም አይናወጥም።(ምሳሌ 1:33)

#ማጠቃለያ:-
እግዚአብሔርን ቃል መስማት እንዲሁም ለሰማነው ቃል መታዘዝ በረከት ፣ እረፍት ነው። እንስማው እንታዘዝ እንባረካለን። የአብርሃምንና የልጁን የይስሃቅን የመስማትና በእምነት የመታዘዝ ሕይወት ምሳለነትን እንከተል።
🙏እግዚአብሔር ቃሉን በመስማትና በመታዘዝ ይባርከን።

በቀን 13/07/2018ዓ.ም  በይርባ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዕለተ እሁድ ጧዋት በመደበኛ ፕሮግራም ላይ የተካፈልነው የእግዚአብሔር ቃል:📖  #መልዕክት አቅራብ:-               ...
22/03/2026

በቀን 13/07/2018ዓ.ም በይርባ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዕለተ እሁድ ጧዋት በመደበኛ ፕሮግራም ላይ የተካፈልነው የእግዚአብሔር ቃል:
📖 #መልዕክት አቅራብ:-
#አገልጋይ አቶ ወርቁ ኡጋሞ
#በመዝሙር:- /መዘመራን
➥ፕሮግራምን በመምራት :- ወጣት እዮኤል ማቴዎስ

#የመልዕክቱ ርዕስ:- እግዚአብሔር ሕዝቡን እንዴት እንደምያኖር ያውቃል ።
👉መነሻ ጥቅስ፦ ዮሐ 6፡1-15 1ነገ 17:1-24

#መግቢያ:-
የዮሐንስ ወንጌል ጸሐፍ እራሱ ኢየሱስ ይወደው የነበረው ደቀ መዝሙር ዮሐንስ ነው። ሐዋሪያ ዮሐንስ ከመጽሐፍ ቅዱስ ከ66ቱ መጽሐፍት መካከል 5 መጽሐፍ እድጽፍ በእግዚአብሔር የተመረጠ ታማኝ ጸሐፊ ነው።በዚህ መጽሐፉ ከሌሎች ወንገላት ሀሳብ በተለየ መልኩ ኢየሱስንና የሠራቸውን ሥራ አልቆ የሚያንፀባርቅ መጽሐፍ ነው።

በዚህ ክፍል ኢየሱስ ክርስቶስ ከሠራቸው ታምራቶች ውስጥ አንድን ታምራት እናነባለን ። እርሱም ኢየሱስ በተራራው ስብከቱ የተሰበሰቡትን ብዙ ሕዝብ እያስተማረ ለሦሰት ቀናት ቆዬ። ከሦስት ቀንም ቦኋላ ከእኔ ጋር የቆዩትን እንዴት በባዶ አሰናብታቹሃለሁ? አለ።
📌ከእርሱ ጋር የቆዩ በባዶ አይሸኙም/አይሰናብቱም።
📌ከእርሱ ጋር መቆየትን ባህላችንና ልማዳችን እናደርግ።
✔ እርሱ ሊያደርግ ያለውን ያውቅ ነበረና ደቀ መዝሙርቱን ጠየቀ እንዲህ እያለ ''በእጃችሁ ምን አለ?'' እነርሱም ከሁለት ዓሳና ከአምስት እንጄራ ውጭ ምንም የለንም ብለው መለሱለት። ደግሞም ተስፋ በመቁረጥ ለዚህ ሁሉ ሕዝብ በ200 ዲናር እንጄራ ብገዛ እንኳን አይበቃም/አይደርስም አሉ።
🔶 ኢየሱስ ያንን ጥቅቱን አበዛ ሁሉም በፈለጉት መጠን በሉ ጠገቡም በዚህ ብቻ አላበቃም 12 መሶብ ተረፈ።
🔶ከኢየሱስ ጋር መቆየት ከለመድን ጥቅቱ ነገራችን ይበዛልናል ፣ እንጠግባለን ፣ ይትረፈርፍልናልም።

(መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ ምዕራፍ 17)
----------
3፤ ከዚህ ተነሥተህ ወደ ምሥራቅ ሂድ፥ በዮርዳኖስም ትይዩ ባለው በኮራት ፈፋ ውስጥ ተሸሸግ።
4፤ ከወንዙም ትጠጣለህ፥ ቍራዎችም በዚያ ይመግቡህ ዘንድ አዝዣለሁ።
8፤ ተነሥተህም በሲዶና አጠገብ ወዳለችው ወደ ሰራፕታ ሂድ፥ በዚያም ተቀመጥ፤
9፤ እነሆም፥ ትመግብህ ዘንድ አንዲት ባልቴት አዝዣለሁ የሚል የእግዚአብሔር ቃል መጣለት።

ኤልያስም ለእግዚአብሔር ቃል ታዞ የሚበላ የሚጠጣ ነገር ወደሌለበት ወደ ምድረበዳ ወረደ በዚያም በሚያኖር አምላክ እስከ ቀጠረለት ቀን ድረስ በታምራት ኖረ። ለራሷ የሚትበላውን ያላገኘችውን ባልቴት መጋቢ አድርጎ ስያዘጋጅ ሥራው እጅግ ያስደንቃል።
📖አያችሁ እግዚአብሔር የሚታመኑበትንና እርሱን ሰምተው የሚታዘዙለትን በምድረበዳ እህልና ውሃ በሌለበት እንኳ እንዴት እንደሚያኖር ያውቃል።

#ማጠቃለያ
ከእርሱ ጋር መቆየት ጊዜን ማጥፋት ወይም ማባከን አይደለም። ይልቁንስ መታደልና ማትረፍ ነው እንጅ። ከእርሱ ጋር እንቆይ ፤ ከእርሱ ጋር የሚቆዩትን እንዴት በታምራት እንደሚያኖር እርሱ ያውቃልና። በችኮላ አንውጣ ስፍራችንን አንልቀቅ።
📌ከእርሱ ጋር መቆየት ይልመድብን።
🙏 እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር በመቆየት ይባርከን። አሜን!

ቀን 06/07/2018 ዓ.ም በእሁድ መደበኛ አምልኮ ላይ ፕሮግራም መሪ:- አገልጋይ ሙሉቀን ደጋጋ   #መዘምራን :-  👍መልእክት አቅራቢ:-  ፓ/ር ዘማሪ ኤርሚያስ ጴጥሮስ👍ርዕስ:-  እንድህ...
15/03/2026

ቀን 06/07/2018 ዓ.ም በእሁድ መደበኛ አምልኮ ላይ ፕሮግራም መሪ:- አገልጋይ ሙሉቀን ደጋጋ
#መዘምራን :-
👍መልእክት አቅራቢ:- ፓ/ር ዘማሪ ኤርሚያስ ጴጥሮስ
👍ርዕስ:- እንድህ የምትፈሩት ስሌምንድነው?
መነሻ ጥቅስ:-ማር 4:35
2ዜና 20:1
ዘፀአት 14:10
በመጀመሪያ እግዚአብሔር የተናገረን
አዕምሮህን እጠርጋለሁ ፤ልብህን አጸዳለሁ ፤ ሰዉነትህን እፈውሳለሁ::
👍መከራ ስመጣ በውስጣችን ያለውን ኢየሱስን ያስረሳናል
ግን መፍራትን ትተን በውስጣችን ያለውን ኢየሱስን ማስነሳት አለብን:: ኢየሱስ ስነሳ በመጀመሪያ ያስደነገጠንን መከራችንን ይገስፃል ፥ እረፍትም ይሰጠናል::
ከዚያም አንደበታችን በሳቅ ፣ልባችንን በደስታና በመገረም ይሞላል::
👉ዛሬም በብዙ መከራ የተከበባችሁና በጠላት ከበባ ብዛት የፈራችሁ አትፈሩ ፍርሃታችሁን የሚያስወግድላችሁ ኢየሱስ አለላችሁና::
👉መከራ ስበዛባችሁ ወደ የትኛውም አቅጣጫ ፍታችሁን አታዙሩ።፤ ይልቁኑስ ረዳታችሁ በሚሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ብቻ አድርጉ። ቅዱሱ መጽሐፍ በመዘሙር 121:1 ላይ እንደምለን ማለት ነው።
👉ኃይልና ችሎታ በእጁ ነዉና ሊያቆመው/ሊያቋቁመው የሚችል ኃይል የለም ::
👉 ሁልጊዜ አይኖቻችን እርሱን ብቻ ይዪ ያን ጊዜ በከበቡን ላይ የእግዚአብሔር እጅ ትገለጣለችና። #ምክንያቱም ሰልፉ የእግዚአብሔር እንጅ የኛ አይደለምና:: በዚያን ጊዜ አንተ ዝም ብለህ ትቆማለህ እርሱ ስለ አንተ ይዋጋልሃል። ምክንያቱም አንተ የምትዋጋህ አይደለምህና ተዋግህ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነውና::
👍 ከዚያም በኋላ አንተ ለእግዚአብሔር ትሰግዳለክ፣ እግዚአብሔርን ታመሰግናህ፣ ለእግዚአብሔር የምስጋናን መዝሙርም ትዘምራለህ:: ለምን?:- እግዚአብሔር ስላንተ ተዋግቶ ጠላትህን ፈጽሞ አጥፍቷልና::
👉ስለዚህ ተዋግቶ አሸንፎ ለሕዝቡ ድልን እና ምርኮን የምሰጥ እግዚአብሔር ከሆነ የእኛ መጨነቅ እና መፍራት ዋጋ ስለሌለው ቅዱሳን የሆንን እኛ በእርሱ ብቻ እንታመን እርሱ ስለ እኛ ይዋጋልና ፥ ምርኮንም ይሰጠናልና:: በእግዚአብሔር አብ ፣ በእግዚአብሔር ወልድ ፣ በእግዚአብሔር መንፈስ የቅዱስ በአንድ አምላክ ስም ብቻ መታመነ ይሁንልን አሜን::

በቀን 29/06/2018ዓ.ም ዕለተ እሁድ ጧዋት በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የልጆች ሁለንትናዊ አገልግሎት 15ኛ ዙር በልጆች ዓመታዊ በዓል ላይ የተካፈልነው የእግዚአብሔር ቃል:📖 ...
08/03/2026

በቀን 29/06/2018ዓ.ም ዕለተ እሁድ ጧዋት በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የልጆች ሁለንትናዊ አገልግሎት 15ኛ ዙር በልጆች ዓመታዊ በዓል ላይ የተካፈልነው የእግዚአብሔር ቃል:
📖 #መልዕክት አቅራብ:-
#ፓ/ር አስራት ከፊያለው
#በመዝሙር:- /መዘመራን

#የመልዕክቱ ርዕስ:- ድርሻዬ እና ድርሻቸው።
👉መነሻ ጥቅስ፦ ኤፌ 6:1-4

#መግቢያ:-
የመጽሐፍ ጻፊው ሐዋሪያው ጳውሎስ ስሆን ይህ መጽሐፍ በሮም እስር ቤት ሆኖ ከጻፋቸው መጽሐፍት መካከል አንዱ ነው።
የመጽሐፉ አስተዋጽዖ
1) ከምዕራፍ 1-3 በክርስቶስ በማመን ስለምገኙ ዘርፈ ብዙ በረከቶች እና ስለመሠረታዊ ክርስትና በጥልቀት የሚያወራ ስሆን፣
2)ከምዕራፍ 4-6 አማኝ በዓለም ውስጥ ስኖር እንዴት መኖር እንዳለበት የሕይወት መመሪያዎችን በየደረጃ ይሰጣል።

ሐዋሪያው በዚህ ክፍል ዳግም ተወልደው በእግዚሐብሔር በተሰብ ውስጥ የተቆጠሩ ወላጆች እና ልጆች መካከል ልኖር ስለምገባው ኅብረት ግልጽ መመሪያ ይሰጣል።
🔶ለክርስትያን ቤተሰብ የእግዚአብሔር ቃል የሁሉም ነገር መሠረት/መመሪያ ነው።
🔶 ለእግዚአብሔር ቃል ያልተገዛ ለሌላ ለምንም አይገዛም ልገዛም አይችሉም።
📌 በቤተሰብ ውስጥ ያሉ ባለ-ድርሻ አካላት በሁለት ከፍለን እናያለን።( ልጆች እና ወላጆች)

⓵የልጆች ድርሻ በቤተሰብ ውስጥ፣
✔ለወላጆቻቸው መታዘዝ:- ለምንድ ነው መታዘዝ ያስፈለገው?
1) ልጆች የጌታ ስለሆኑ እና ጌታ ታዛዥነትታችንን ስለሚ
2) መታዘዝ ተገቢ ስለሆነ
3) መታዘዝ የጌታ ትዕዛዝ ስለሆነ
ስንታዘዝ ምን እንሆናለን?
📌ጌታን ደስ እናሰኛለን፣
📌የወላጆቻችን ልብ ያርፋል፣
📌 እንባረካለን።
✔ ወላጆቻቸውን ማክበር:- ይህ ማለት ለወላጆች ፍቅርን ፣ እንክብካበንና ስፍራ መስጠትን ያመለክታል።
➥ልጆች ወላጆቻቸውን መታዘዝ ያለባቸው ስለወለዱአቸው ብቻ ሳይሆን ከሰማይ የተሰጠ ትዕዛዝም ስለሆነ ነው።
🔶ወላጆችን የማክበር በረከቶች
1) በተሰጠን ምድር ረዥም ዕድሜ መኖር(ዕድሜን መጥገብ)፣
2) በነገር ሁሉ መሳካት፣
3) በመልካም ፍሬ መሞላት፣

➁ የወላጆች ድርሻ በቤተሰብ ውስጥ፣(ምሳሌ 22:15 ፤ 19:20)
✔ በእግዚአብሔር ቃል ምክርና ተግሳጽ ማሳደግ፣ ➥ምክር ማለት ስለ ልጁ አካሄድ ሀሳብ በመስጠት መከታተል (ትክክለኛ መንገድ እንድሄድ አቅጣጫ ማሳየት) ማለት ነው።
➥ተግሳጽ ማለት ወላጆች ለልጆች የሚሰጡት የቅጣት ዕርምት ነው።
✔ ልጆችን አለማስቆጣት:- ይህ ማለት ልጁ በስህተት መንገድ ስሄድ እያዪ አለመገሠጽ ማለት አይደለም።
🔶 ወላጆች ልጆችን በምን ያስቆጣሉ?
📌 በልጆች ላይ የማያንጽ ነገር በመናገር ፣ ከስተታቸው እንድማሩ ከማበረታታት ይልቅ በመኮነን፣ በፊታቸው በአንድ አቋም ባለመቆም ፣ አድልዖ በማድረግ ፣ የገቡትን ቃል ሳይፈጽሙ በመቅረት ፣ ለልጆች ትልቅ መስሎ የሚታያቸውን ነገር በማቅለል ወዘተ።

#ማጠቃለያ፦
ክርስትናችን ክርስቶስን እየመሰለ እንድቀጥል ፣ የነገ የሀገር እና የቤተ ክርስቲያን ተረካቢዎችን እንዲሁም ''ለወንጌል እኔ አለሁ'' የምል ትውልድ ለማፍራት ከፈለግን በእግዚአብሔር ቃል መሠረት ዛሬ በትውልዱ ላይ በተገብው መንገድ አስፈላጊውን ዋጋና በመክፈል መሥራት አለብን።

Address

Yirba

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ይርባ ቤቴል ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን Yirba betel Kale hewot church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share