22/08/2026
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የዕርገት በዓል በደመቀ ኹኔታ ተከብሯል።
ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ/ም (መሠረተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፤ ወልድያ)
በየዓመቱ የሚከበረውና በክርስቲያኖች ዘንድ ተወዳጅ የኾነው የጾመ ፍልሰታ ወቅት ከነሐሴ 01-16 ቀን ድረስ በጾምና በጸሎት ሕጻናት ጭምር የሚያሳልፉት ኦርቶዶክሳዊ በዓል ነው።
በኹሉም አብያተክርስቲያናት ዘንድ የሚከበረው ይኽ ተወዳጅ በዓል በወልድያ መንበረ ንግሥት ደብረ ገሊላ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ዛሬ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ/ም ተጠናቅቋል።
በዓሉ የተከበረው የእመቤታችንን ዕርገት በማሰብ እንደመኾኑ መጠን የርሷን በረከት ለመቀበል ከጾምና ጸሎት ጋር በቅዱስ ቍርባን ተወስነው ይኽን ኹለት ሱባኤ ያሳለፉ ኦርቶዶክሳውያን ጥቂት የማይባሉ ናቸው።
የሰሜን ወሎ ሀገረስብከትና የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተክህነት የሥራ ክፍል ኀላፊዎችና ሠራተኞች፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ የደብሩ አገልጋዮችና ልዩ ልዩ ሠራተኞች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላትና ምእመናን/ት በተገኙበት ታቦተ ሕጉ ሥርዐተ ዑደቱን ጨርሶ በአባቶች ጸሎት ተጠናቅቋል።
መልካም በዓል ይኹንልን!
!
ርስዎም ቤተሰብ ይኹኑ!
and በማድረግ፥ አገልግሎታችንን ያግዙ!
~ YouTube፡ http://www.youtube.com/
~ Facebook፡ https://www.facebook.com/MesereteHiwotSS
~ Instagram፡ https://instagram.com/woldiamhss
~ Telegram፡ https://t.me/MesereteHiwotSS
~ TikTok፡ https://www.tiktok.com/
~ Twitter፡ https://twitter.com/WoldiaMHss