የተዋህዶ ዕንቁ ሚዲያ

የተዋህዶ ዕንቁ ሚዲያ ጼና ሚዲያ የልባምች መብራት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtube.com/?si=MqUGSzK--4Qn7Uby

"መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፥ ሩጫውን ጨርሻለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ ወደፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል።" (፪ኛ ጢሞ. ፬፡፯)    ​ለዘመናት ያለመታከት የእግዚአብሔርን መንግሥት ወን...
08/03/2026

"መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፥ ሩጫውን ጨርሻለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ ወደፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል።" (፪ኛ ጢሞ. ፬፡፯)
​ለዘመናት ያለመታከት የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል ሲሰብኩ፣ የታወከውን ልብ በቃለ እግዚአብሔር ሲያረጋጉ፣ የጠፋውን ሲፈልጉና ቅድስት ቤተክርስቲያንን በቅንነትና በታማኝነት እንዲሁም በትጋት ሲያገለግሉ የኖሩት ታላቁ የወንጌል አርበኛ መምህር ዘለዓለም ወንድሙ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
​መምህር ዘለዓለም ለብዙዎቻችን የመንፈስ አባት፣ ለምእመናን ብርታት፣ ለወጣቶች ደግሞ አርአያ በመሆን የክርስትናን ሕይወት በተግባር ያስተማሩ የቤተክርስቲያናችን ብርሃን ነበሩ።
ዛሬ ነፍሳቸው ወደ አምላኳ ብትሄድም በአካለ ስጋም ከኛ ቢለዩብም፣ የዘሩት የወንጌል ዘር ግን በትውልድ ልብ ውስጥ ሲያፈራ ሲያብብ እንደኖረ አሁንም ለዘላለም ፍሬ ሲያፈራ ይኖራል።
​ቀንዲል ሚዲያ በዚህ መሪር ሀዘን ወቅት፦
​ለቅድስት ቤተክርስቲያን
​ለተማሪዎቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው
​እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸው በሙሉ መጽናናትን እንዲሰጠን የእርሳቸውንም ነፍስ በገነት በቅዱሳኑ ዕቅፍ ዘንድ እንዲያስርፍልን የልብ ጸሎታችን ነው💔 ነፍስ ይማርልን💔
የተወሰደ

አንቺ የወርቅ መቅጃ ነሽ እኔ የተጠማሁ ነኝልጅሽ የሕይወት ውሃከጥሜ የሚያረካኝእኔ ተሻጋሪ ነኝ ማርያም ሆነሽኝ ድልድይ ልጅሽ መድረሻዬ ነውበደስታ የሚያኖረኝአሜን አሜን አሜን
28/02/2026

አንቺ የወርቅ መቅጃ ነሽ
እኔ የተጠማሁ ነኝ
ልጅሽ የሕይወት ውሃ
ከጥሜ የሚያረካኝ
እኔ ተሻጋሪ ነኝ
ማርያም ሆነሽኝ ድልድይ
ልጅሽ መድረሻዬ ነው
በደስታ የሚያኖረኝ
አሜን አሜን አሜን

 #በምድር _ላይ_ ታሞ_ እንደመተኛት_ ክፉ_ ነገር_ የለም_ !  ታሞ_ ከመተኛት_ ስዉሯ_ ማርያም_ ትጠብቃችሁ_አሜን አሜን አሜን
28/02/2026

#በምድር _ላይ_ ታሞ_ እንደመተኛት_ ክፉ_ ነገር_ የለም_ ! ታሞ_ ከመተኛት_ ስዉሯ_ ማርያም_ ትጠብቃችሁ_
አሜን አሜን አሜን

«ኪዳነምህረት» ስንል የምህረት ቃልኪዳን ማለት ነው፡፡በዚህ ውስጥም ምህረት አድራጊው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ምህረት ተቀባይም መላው የአዳም ዘር ነው፡፡***እናታችን ቅድ...
23/02/2026

«ኪዳነምህረት» ስንል የምህረት ቃልኪዳን ማለት ነው፡፡
በዚህ ውስጥም ምህረት አድራጊው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ምህረት ተቀባይም መላው የአዳም ዘር ነው፡፡
***
እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምድራዊ ቆይታዋ ዘውትር ወደ ክርስቶስ መካነ መቃብር ጎለጎታ እየወረደች ትፀልይ ነበር፡፡
***
ልጇ እና ወዳጇ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገችውን ልመናና ፀሎት ተመልክቶና ሰምቶ የምህረት ቃል ኪዳን ገባለት ፡፡
***
እንኳን የእናቱን ፀሎት እና ልመና ቀርቶ ዘውትር በኃጥያት የምንዘፈቀውን የእኛን የደካማዎችን ፀሎት የሚሰማ አምላክ የእናቱን ፀሎትና ልመና ተቀብሎ ይኸው ስለ አንቺ ፣ ስለ እናቴ ክብርና ፀጋ ሲል ይኸው ቃሌ ብሎ ቃልኪዳን አደረገ፡፡
***
በዚህም በተገባላት ቃልኪዳን መሰረት ስሟን ለሚጠሩ፣ በእርሷ አማላጅነት ለሚታመኑ በምድር በረከትን በሰማይ የዘለዓለም መንግስትን እንደሚወርሱ የምህረት እና የቸርነት ቃልኪዳን ሰጥቷታል ፡፡
***
በዚህም መሠረት ቃልኪዳኗን ምክንያት በማድረግ ኪዳነ-ምህረት እያልን እንጠራታለን!

ቅድስት ኪዳንምህረት በምልጃዋ ትጠብቀን🙏❤
16/6/2018 ዓ,ም

የኪዳነ ምሕረት መዝሙራት ስብስብ በዘማሪ ዲ/ን ኤፍሬም ፀጋዬ #መዝሙር

22/02/2026

😍🙏🙏😍

በአሰቦት ገዳም አንድ መኖክሴ በበአታቸው ውስጥ ሳሉ ተገደሉ።*** ጥር 28,  2018 ዓ.ም አሰቦት ገዳም ውስጥ በስርዓተ ምንኩስና  ፈጽመው በዓታቸው ውስጥ ያሉ አባ መብራቱ የተባሉ አንድ ...
09/02/2026

በአሰቦት ገዳም አንድ መኖክሴ በበአታቸው ውስጥ ሳሉ ተገደሉ።
***

ጥር 28, 2018 ዓ.ም አሰቦት ገዳም ውስጥ በስርዓተ ምንኩስና ፈጽመው በዓታቸው ውስጥ ያሉ አባ መብራቱ የተባሉ አንድ አባት በመሣርያ ተገድለው ተገኝተዋል።

ነፍሳቸውን በአፀደ ገነት ያኑርልን🙏😥

ጠዋት ከእንቅልፌ እንደነቃሁ፥እግዚአብሔርን ከአመሠገንኩ በኋላ  😘          አቤት ሲጣፍጥ💖ርዕሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገ/ኪዳን ግርማ (የአራቱ ጉባኤያት መምህር) ረጅም ዕድሜን ኸጤና ጋር...
09/02/2026

ጠዋት ከእንቅልፌ እንደነቃሁ፥እግዚአብሔርን ከአመሠገንኩ በኋላ 😘
አቤት ሲጣፍጥ💖
ርዕሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገ/ኪዳን ግርማ (የአራቱ ጉባኤያት መምህር) ረጅም ዕድሜን ኸጤና ጋር ያድልልን🙏😘😍

♦️አርቲስት ንብረት ገላው (እከ) ...የሰው ፊት ገረፈኝ ብለህ ጀምረህ ሳታቆመው፣ ስድብ እና ትችት ወደ ኋላ ሳያስቀርህ የጻድቁ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ቤተ ክርስቲያን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳት...
01/02/2026

♦️አርቲስት ንብረት ገላው (እከ) ...

የሰው ፊት ገረፈኝ ብለህ ጀምረህ ሳታቆመው፣ ስድብ እና ትችት ወደ ኋላ ሳያስቀርህ የጻድቁ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ቤተ ክርስቲያን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትል በደስታ ጀምረህ በጽናት ስለጨረስክ እንኳን ደስ ያለህ።

ጻድቁ ቤታቸውን እንደሰራህላቸው የአንተንም ቤት በሰማይ ይስሩልህ።

በነገራችን ላይ ዛሬ ከዕለተ ቀናቸው ጋር አያይዤ ትንሽ ነገር ልበል ብዬ ነው እንጅ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑ ሊመረቅ ኹለት ሳምንት እንደቀረው ይታወቃል። እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የካቲት ፯ እና ፰ በብጹዕ አቡነ ኤርምያስ እንደሚመረቅም ቀኑ ተቆርጧል።

ግን አንድ ነገር ስትናገር ሰምቻለሁ። አሁንም እባካችሁ በመጨረሻም ቢሆን ጥቂት ነገር የሚቀር አለና በጎደሎ አይመረቅ። እስከዛሬ እጃችሁን የዘረጋችሁም ገና ዛሬ የሰማችሁም የመጨረሻውን በረከት ታፍሱ ዘንድ ለጎደሎው እጃችሁን ዘርጉ ብለህ ነበር።

በዚሁ አጋጣሚ ይኽንን ጥሪ እኔም ላልሰሙት እንዲሰሙ ደግሜዋለሁ።

አሁን እጄን ልዘርጋ የሚል ካለ የደብሩን አካውንት ይኸው።1000653028206
ስልክ 09 20 71 50 50
ደብረ መንክራት ቆብ ተ/ሃይማኖት

ለጊዜው በቋንቋዬ ነሽ ሚዲያ በኩል እነዚህ ተልከዋል።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
♦️እናታችን ወ/ውልታ 100 ዶላር
♦️ወንድማችን ወልደ ጻድቅ 10,000 ብር
♦️ስሙን እግዚአብሔር ያውቀዋል 15,000

በሉ ይህንን ያነበባችሁ ኹላችሁ በሰሜን ወሎ ገጠር ውስጥ ካለው የአባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በጎደሎ ሳይመረቅ በረከት ተሻሙ።

ዲ/ሉልሰገድ ቋንቋዬ ነሽ ሚያ የተወሰደ

😍😍😍😍😍😍😍
25/01/2026

😍😍😍😍😍😍😍

ይህንን ቻናል ሰብስክራይብ በማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ። ለወዳጅዎም በማጋራት የእግዚአብሔር ቃል እንዲዳረስ የበኩልዎን ይወጡ። 👇👇👇 https://y...

ጎንደር በቆላድባ የታየው ተአምር ቀጥሏል — ፀበል ፈለቀ! "የእግዚአብሔር ድንቅ ስራ በቆላድባ ከተማ ተገለጠ!"ትላንት ማታ በጎንደር በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ ቆላድባ ከተማ በዋርካው ላይ የታየ...
01/01/2026

ጎንደር በቆላድባ የታየው ተአምር ቀጥሏል — ፀበል ፈለቀ!

"የእግዚአብሔር ድንቅ ስራ በቆላድባ ከተማ ተገለጠ!"

ትላንት ማታ በጎንደር በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ ቆላድባ ከተማ በዋርካው ላይ የታየው የቅድስት ኪዳነ ምህረት ተአምራዊ ምስል መላውን ዓለም ሲያስደንቅ መቆየቱ ይታወሳል። አሁን ደግሞ ሌላ እጅግ የሚያስገርም ተጨማሪ ተአምር ተከስቷል!

የእናታችን የኪዳነ ምህረት ምስል በታየበት በዚያው ስፍራ፣ በአሁኑ ሰዓት አስደናቂ ፀበል ፈንድቶ ወጥቷል! * ህዝቡ እየተፈወሰ ነው፦ በቦታው የሚገኘው ህዝብ በፀበሉ እየተጠመቀ ይገኛል፤ እግዚአብሔር በቸርነቱ ድውያንን እየፈወሰ፣ የታመሙትን እየዳሰሰ መሆኑ እየተነገረ ነው።

* በስፍራው ያለው ምዕመን በደስታ እልልታና በምስጋና ድምፅ አካባቢውን ሞልቶታል። "ዛፉን እንዳይቆረጥ መሳሪያ የሰበረች እናታችን፣ ዛሬ ደግሞ ለልጆቿ ፈውስን አፈለቀች" በማለት ህዝቡ ምስክርነቱን እየሰጠ ነው።

* በዋርካው ላይ የቅድስት ኪዳነ ምህረት ምስል በግልጽ ታየ።
* ዛሬ ደግሞ ለብዙዎች መዳኛ የሚሆን ፀበል ፈንድቶ ወጣ!
እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው! ቸርነቱና ምህረቱ ለሁላችንም ይሁን።

ይህንን የእግዚአብሔርን ስራ ለዓለም ሁሉ እንዲደርስ በማድረግ ምስክር ይሁኑ!

Via Hellen ከስፍራው

Address

Aleta Wendo
Wendo

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የተዋህዶ ዕንቁ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share