ሳሌም ሚዲያ ጉራጌ ሀገረ ስብከት/Gurage Diocese

ሳሌም ሚዲያ ጉራጌ ሀገረ ስብከት/Gurage Diocese ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሳሌም የጉራጌ ሀገረ ስብከት የፌስቡክ ገጽ ነው።

በኤነር ደብረ መንክራት ቅዱስ አማኑኤል ገዳም የዕርገት በዓል በድምቀት ተከበረ➺➺➠➺➺➺➠➠➠➠➠➠➠➠➠ በጉራጌ ሀገረ ስብከት በሚገኘው በኤነር ደብረ መንክራት ቅዱስ አማኑኤል ገዳም፣ የጌታችን...
21/05/2026

በኤነር ደብረ መንክራት ቅዱስ አማኑኤል ገዳም የዕርገት በዓል በድምቀት ተከበረ
➺➺➠➺➺➺➠➠➠➠➠➠➠➠➠

በጉራጌ ሀገረ ስብከት በሚገኘው በኤነር ደብረ መንክራት ቅዱስ አማኑኤል ገዳም፣ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የዕርገት በዓል ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ መሥራችና የበላይ ኃላፊ በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት ተከብሯል።

የቅዳሴው ፍጻሜን ተከትሎ የታቦተ ሕጉ ዑደት በብፁዕነታቸው አባታዊ ምሪት በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ በካህናትና በመነኮሳት፣ በሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራንና በምዕመናን ታጅቦ ተከናውኗል። በመቀጠልም የገዳሙ ሰንበት ተማሪዎች ዕለቱን የሚዘክሩ ያሬዳዊ ዝማሬዎችን አቅርበዋል።
ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በሰጡት ትምህር ወንጌል፤ የዕርገት በዓል ከዘጠኙ ዓበይት በዓላት አንዱ መሆኑን ገልጸው፤ ዕርገት የሚለው ትርጉሙም "ወደ ላይ መውጣት፣ ከፍ ከፍ ማለት" እንደሆነ አስረድተዋል። ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም መጥቶ፣ ተሰቅሎ ዓለምን ካዳነና ከትንሣኤው በኋላ ለሐዋርያት በተለያየ ጊዜ እየተገለጠ ካስተማራቸው በኋላ፣ በ40ኛው ቀን እየባረካቸው ማረጉን አብራርተዋል።
ደቀ መዛሙርቱ በአካል ሲለያቸው መጀመሪያ ላይ ቢፈሩም፣ ጌታ ግን አስቀድሞ *"ልባችሁ አይፍራ፤ እኔ ከሄድኩ በኋላ ቦታ አዘጋጅላችኋለሁ"* በማለት የሰጣቸውን ተስፋ አስታውሰዋል። በዚህም ምክንያት ዕርገቱ በሰማይ በመላእክት፣ በምድርም በሰው ልጆች ዘንድ ታላቅ ደስታን ያመጣና ተጎሳቁሎ የነበረው የሰው ሥጋ በአብ ቀኝ በአምላካዊ ክብር የተቀመጠበት መሆኑን ገልጸዋል።

ብፁዕነታቸው በዋናነት ከበዓሉ የምንማራቸውን ዝርዝር ትምህርት ያስተማሩ ሲሆን። የገነት በር ተዘግቶበት ለነበረው የሰው ልጅ ክርስቶስ የሰውን ሥጋ ለብሶ በማረጉ ሰብአዊ ክብር የተገለጠበትና የከበረበት በዓል ነው፤ አምላካችን ሞትን ድል አድርጎ መነሣቱ የሰው ልጅ ሞትን ድል ማድረጉንና ድኅነቱ መጠናቀቁን የሚያሳይ ነው፤ ክርስቶስ በማረጉ፣ በጎ ለሠሩ ሰዎች የሰው ዓይን ያላየው መንግሥተ ሰማያት መዘጋጀቱን ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል።

ብፁዕነታቸው ሲቀጥሉ መንግሥተ ሰማያት የቅዱሳንና የተመረጡት መኖሪያ እንጂ ምግባር ለሌላቸው ስላልሆነች፣ ምእመናን ምግባራቸውን ሊያቀኑና በበጎ ሥራ ሊተጉ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በተጨማሪም ጌታ ሲያርግ ሐዋርያትን "ኃይል እስክትለብሱ ድረስ ከኢየሩሳሌም አትውጡ" ማለቱን በማንሳት፣ እዚህ ላይ የተጠቀሰችው ኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን መሆንዋንና ምእመናንም መዳናቸው እስኪረጋገጥ ድረስ ከቤተክርስቲያን መራቅ እንደሌለባቸው መክረዋል።

ብፁዕነታቸው ትምህርታቸውን ሲያጠቃልሉም፦ "‘ላዕለ ይኩን ሕሊናክሙ’ (ልባችሁ/ሐሳባችሁ በሰማይ ይሁን) የተባለው መንግሥቱን እያሰብን እንድንኖር ነው፤ ዓለም እንደ እንስሳ አቀርቅሮ የምድርን ነገር ብቻ በሚያስብበት በዚህ ዘመን፣ እኛ ግን ሐሳባችንና ልባችን ሰማያዊ ሊሆን ይገባል"* በማለት አባታዊ ምክርና ቃለ ምዕዳን አስተላልፈዋል።

በተያያዘ ዜና፣ በገዳሙ በአዲስ መልክ ሊገነባ የታሰበውንና በ1,500 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፈውን ዘመናዊ የሕንጻ ቤተክርስቲያን ግንባታ የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠዋል። ብፁዕነታቸው አያይዘውም፣ ይህ ታሪካዊ ገዳም ጥንታዊ ይዘቱንና ታሪኩን ጠብቆ እንዲሠራ በትኩረት እንደሚሠራ ገልጸዋል።

ግንቦት ፲፫/፳፻፲፰ ዓ.ም ወልቂጤ

ለፈጣን መረጃ ሳሌም የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሚዲያ። ቤተሰብ ይሁኑ። የማኅበራዊ ሚዲያዎቻችን።
Facebook; https://www.fb.com/GurageDiocese
Telegram; https://t.me/GurageDiocese
Tiktok; tiktok.com/
Instagram; instagram.com/gurage_diocese
YouTube; https://youtube.com/

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ለ106 ዕጩ አገልጋዮች ሥልጣነ ክህነት ሰጡ።ግንቦት ፲፫/፳፻፲፰ ዓ.ም ኤነር ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ...
21/05/2026

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ለ106 ዕጩ አገልጋዮች ሥልጣነ ክህነት ሰጡ።

ግንቦት ፲፫/፳፻፲፰ ዓ.ም ኤነር

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ መሥራችና የበላይ ኃላፊ በኤነር ደብረ መንክራት ቅዱስ አማኑኤል ገዳም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የዕርገት በዓል በማስመልከት ለ103 የአብነት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለቆዩ ደቀ መዛሙርት የዲቁና፣ እንዲሁም ለ3 ዲያቆናት የማዕረገ ቅስና ሰጡ።

የጉራጌ ሀገረ ስብከት ጥራትና ብቃት ያለው የቤተክርስቲያን አገልጋይ ለማፍራት በብፁዕነታቸው መመሪያ ሰጪነት ሰፊ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ሥልጣነ ክህነት በሚሰጥበት ጊዜ ለዲያቆናትም ሆነ ለቀሳውስት የሚሆን ወጥ መመዘኛ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ ነው። በዚህ መሠረት ዕጩ አገልጋዮች መጀመሪያ ከየደብራቸው ተነስተው እስከ ወረዳ ቤተ ክህነት ድረስ ባለው መዋቅር ጥብቅ የብቃት መመዘኛዎችን እንዲያልፉ የሚደረግ ሲሆን በእነዚህ ደረጃዎች ያለፉት ብቻ ለሀገረ ስብከቱ የካህናት አስተዳደር ዋና ክፍል የሚተላለፉ ሲሆን፣ ሀገረ ስብከቱም በበዓሉ ዋዜማ የመጨረሻውን የብቃት ማረጋገጫ ፈተና በመስጠት ሙሉ በሙሉ ያለፉትንና ብቁ የሆኑትን ብቻ ለሥልጣነ ክህነት እንዲበቁ ያደርጋል።

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ማዕረገ ክህነት ለተቀበሉት አገልጋዮች በሰጡት አባታዊ ምክርና መመሪያ፦ "አርአያ ክህነታችሁን በጥንቃቄ ልትጠብቁ፣ በቅድስና ሕይወት ልትመላለሱ፣ እንዲሁም ለተሰጣችሁ ቅዱስ አገልግሎትና ለቤተክርስቲያን ሥርዓት ዘወትር ታማኞች ልትሆኑ ይገባል" ብለዋል።

ሀገረ ስብከቱ አገልጋዮች ሥልጣነ ክህነት ለመቀበል የሚገጥማቸውን እንግልትና የጉዞ ድካም ለመቀነስ በማሰብ፣ በአሁኑ ወቅት በዓመት አራት ጊዜ ወረዳዎችን ባማከለ ሁኔታ በተለያዩ ማዕከላት ሥልጣነ ክህነት የሚሰጥበትን ምቹ አሠራር ዘርግቶ እየተገበረበት ይገኛል።

ለፈጣን መረጃ ሳሌም የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሚዲያ። ቤተሰብ ይሁኑ። የማኅበራዊ ሚዲያዎቻችን።
Facebook; https://www.fb.com/GurageDiocese
Telegram; https://t.me/GurageDiocese
Tiktok; tiktok.com/
Instagram; instagram.com/gurage_diocese
YouTube; https://youtube.com/

ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ሣልሳይ የጻድቁ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ፍልሰተ ዓፅም ዓመታዊ በዓልን  በእምድብር ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው አከበሩግንቦት 12/20...
20/05/2026

ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ሣልሳይ የጻድቁ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ፍልሰተ ዓፅም ዓመታዊ በዓልን በእምድብር ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው አከበሩ

ግንቦት 12/2018 ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ሣልሳይ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ መሥራች እና የበላይ ኃላፊ፤የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት የሥራ ሂደት ቦርድ ሰብሳቢ ሊቀ ጳጳስ የጻድቁ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ፍልሰተ ዓፅም ዓመታዊ ክብረ በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በጉራጌ ሀገረ ስብከት በቸሃ ወረዳ ቤተ ክህነት በእምድብር ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው አከበሩ።

ብፁዕነታቸው ከሌሊቱ ክፍለ ጊዜ ጀምረው በቦታው በመገኘት ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን ያከናወኑ ሲሆን የቅዳሴው ሥርዓት ከተጠናቀቀ በኋላ ታቦታቱ ወደዓውደ ምህረት ወጥተው በሊቃውንቱ ያሬዳዊ ወረብ ቀርቦ በመቀጠል በብፁዕ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ መልካም ፈቃድ የዕለቱን ትምህርተ ወንጌል መዝሙር 33፦19 " ብዙኅ ሕማሞሙ ለጻድቃን ወእምኩሉ ያድኅኖሙ እግዚአብሔር/የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል"" በሚል ርዕስ መጋቤ ሃይማኖት ብሥራት ገ/ሥላሴ የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ ዋና ክፍል ኃላፊ አስተምረዋል።

በመቀጠል ብፁዕነታቸው በበዓሉ ለተሰበሰቡት የመንፈስ ቅዱስ ልጇቻቸው አባታዊ ቃለ ምዕዳን፤ቡራኬ እና መመሪያ ሰጥተዋል።

ብፁዕነታቸው በቃለ ምዕዳናቸው የጻድቁ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን በዓል የምናከብረው አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ለመምሰል ነው።

ቅዱሳን አባቶቻችን በሥጋቸው መከራን የተቀበሉ ክርስቶስን መስለው የዘለዓለም ሕይወትን ለመውረስ ስለሆነ እኛም ንስሐ ገብተን ቅዱስ ሥጋውን በልተን ክቡር ደሙን ጠጥተን ክርስቶስን በመምሰል የዘለዓለም ሕይወትን መውረስ አለብን በማለት አባታዊ ቃለ ምዕዳን ሰጥተው በበዓሉ ለአገልግሎት ከየድባራቱ ለተሰበሰቡ መምህራን፤ካህናት እና ዲያቆናት መንፈሳዊ አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ አባታዊ መመሪያ ካስተላለፉ በኋላ በቅርብ ጊዜ ተጀምሮ ግንባታው የተጠናቀቀውን የደብሩን አፀደ ሕዓናት ጎብኝተው ተጨማሪ መመሪያዎችን ለወረዳ ቤተ ክህነቱ፤ ለደብሩ አስተዳዳሪ እና የሰበካ ጉባኤ አባላት በማስተላለፍ በቦታው የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት አጠናቀዋል።

19/05/2026

ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጉራጌ ሀገረ ስብከት የዩቲዩብ ቻናል ነው።

18/05/2026

ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጉራጌ ሀገረ ስብከት የዩቲዩብ ቻናል ነው።

"ከሕንፃ ቤተክርስቲያኑ በላይ የሥላሴ ሕንፃ የሆናችሁትን ምዕመናን ስናይ እንደሰታለን" — ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅየጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ...
17/05/2026

"ከሕንፃ ቤተክርስቲያኑ በላይ የሥላሴ ሕንፃ የሆናችሁትን ምዕመናን ስናይ እንደሰታለን" — ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ

የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ በቸሀ ወረዳ ቤተ ክህነት በሚገኘው በሞጨ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን በይፋ ጎበኙ። ብፁዕነታቸው በዕለቱ ከማኅሌትና ከቅዳሴ ጸሎት በኋላ ለተሰበሰበው ምዕመን ሰፊ አባታዊ ትምህርትና መመሪያ አስተላልፈዋል።

ብፁዕነታቸው በአሁኑ ወቅት ዐዲስ እየተገነባ ያለውን የሕንፃ ቤተክርስቲያን የሥራ ሂደት ያደነቁ ሲሆን፣ የአካባቢው ምዕመናን ከሀገረ ስብከቱ የሚሰጡ መመሪያዎችን በአግባቡ በመተግበር፣ ግንባታው ከመጠናቀቁ በፊት "ሂደቱን አይታችሁ መመሪያ ስጡን" በማለት መጋበዛቸው ሥርዓትንና መመሪያን ስለማክበር ትልቅ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።

የጉብኝታቸው ዋና ዓላማ የሕንፃውን ቁሳዊ አወቃቀር መመልከት ብቻ እንዳለሆነና የምዕመናኑ መንፈሳዊ ሕይወት መጎብኘት የላቀ ደስታ እንደፈጠረባቸው ብፁዕነታቸው ሲያስረዱ እንዲህ ብለዋል፦ "ዛሬ ለማየት የመጣነው የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑን የግንባታ ሁኔታ ቢሆንም፤ ከሕንፃው በላይ ግን የሥላሴ ሕንፃ የሆናችሁ እናንተ ምዕመናን ስታስቀድሱ፣ ስትጸልዩ፣ ስትዘምሩና ስትቆርቡ ስናይ ደስታችን እጥፍ ሆኗል፤ ሕንፃው የሚሠራው ለሰው እንጂ ሰው ለሕንፃ አልተፈጠረም። ስለዚህ ንስሐ ገብታችሁ እንድትቆርቡበትና ሕይወት እንድታገኙበት ነው አባታዊ ምኞታችን።" ብለዋል

በተጨማሪም ምዕመናን የሚከተሉትን የክርስትና የሰላም መርሆች አጽንተው እንዲይዙ አባታዊ ምክራቸውን ለግሰዋል፦
የራስን ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ እምነትና ሥርዓት ጠብቆ መኖር፣ የሌሎችን እምነት ማክበር፣ ከሌሎች ጋር በሰላምና በመከባበር መኖር እንዲሁም ከአላስፈላጊ ጭቅጭቆች በመራቅ ሁልጊዜም ሰላማዊ መሆን እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የቤተክርስቲያን መሬት በከንቱ ክፍት መሆን የለበትም፤ በልማት ሥራዎች ላይ መዋል አለበት በማለት በተደጋጋሚ በሚሰጡት መመሪያ መሠረት በደብሩ እየተከናወኑ ያሉትን ዘርፈ-ብዙ እንቅስቃሴዎች በስፍራው ተገኝተው ተመልክተዋል። በዚህም መሠረት፦ ዐዲስ እየተገነባ ያለውን ዘመናዊ ሕንፃ ቤተክርስቲያን፣ ቤተልሔም እና የደብሩን ሁለገብ አዳራሽ፣ እንዲሁም በቤተክርስቲያኑ ሰፊ ይዞታ ላይ ለምቶ የሚገኘውን የድንች ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የተሠሩትን የልማት ሥራዎች ካደነቁ በኋላም ለቀጣይ ሥራዎች የሚረዱ መመሪያዎችን ሰጥተዋል።

በዕለቱ የጉራጌ ሀገረ ስብከት የስብከተ ወንጌል ዋና ክፍል ኃላፊ መምህር መላኩ ጸዳሉ "ትወደኛለህን?" በሚል ርዕስ ሰፊ ትምህርተ ወንጌል ለምዕመናኑ ሰጥተዋል።

የዕለቱ አጠቃላይ መርሐ-ግብር በብፁዕነታቸው ቃለ-ምዕዳን፣ ቀጣይ የሥራ መመሪያና በጸሎተ ፍጻሜውን አግኝቷል።
ለፈጣን መረጃ ሳሌም የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሚዲያ። ቤተሰብ ይሁኑ። የማኅበራዊ ሚዲያዎቻችን።
Facebook; https://www.fb.com/GurageDiocese
Telegram; https://t.me/GurageDiocese
Tiktok; tiktok.com/
YouTube; https://youtube.com/

ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በአዲስ መልክ እየተገነባ ያለውን የወንጪ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ጎበኙሚያዝያ ፯/፳፻፲፰ ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና፤ ብ...
15/05/2026

ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በአዲስ መልክ እየተገነባ ያለውን የወንጪ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ጎበኙ

ሚያዝያ ፯/፳፻፲፰ ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በወንጪ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም በመገኘት፣ በአዲስ መልክ እየተከናወነ ያለውን የገዳሙን የግንባታና የልማት ሥራ ተመልክተዋል።
በጉብኝቱ ወቅት ሙሀዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ለብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳቱ ገዳሙን በተመለከተ እየተከናወኑ ስላሉት ሥራዎች ሰፊ ገለጻ አድርገውላቸዋል።

ገዳሙ ጥንታዊ ማንነቱን ሳይለቅ፣ ለገዳማዊ ሕይወትና ለጸሎት አመቺ በሆነ መልኩ በድጋሚ እየተገነባ ሲሆን ግንባታው ገዳሙን ለገዳማዊ ሥርዓት ብቻ ሳይሆን፣ ለከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት ማዕከልነትና የቅርስ መጠበቂያ ሙዚየም ሆኖ እንዲያገለግል ታስቦ እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል።
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳቱ በቦታው ተገኝተው ባዩት የሥራ እንቅስቃሴ መደሰታቸውን ገልጸው፣ ገዳሙ የቤተክርስቲያንን ክብርና የታሪክ ቅርስን ጠብቆ ለትውልድ በሚሻገር መልኩ መገንባቱ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን አመልክተዋል።

በወንጪ ሐይቅ ላይ የሚገኘው ይህ ታሪካዊ ገዳም፣ ግንባታው ሲጠናቀቅ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ቱሪስቶች መንፈሳዊ መዳረሻ ከመሆኑም ባለፈ፣ በርካታ መነኮሳትና የሃይማኖት ተማሪዎች በስፋት የሚሰለጥኑበትና መንፈሳዊ ግዳጃቸውን የሚወጡበት ታላቅ ተቋም ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።

ለፈጣን መረጃ ሳሌም የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሚዲያ። ቤተሰብ ይሁኑ። የማኅበራዊ ሚዲያዎቻችን።
Facebook; https://www.fb.com/GurageDiocese
Telegram; https://t.me/GurageDiocese
Tiktok; tiktok.com/
Instagram; instagram.com/gurage_diocese
YouTube; https://youtube.com/

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫየእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክ...
14/05/2026

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ሲኖዶሳዊ በመሆኗ አበው ቅዱሳን በፍትሕ መንፈሳዊና በጉባኤ አድያም ዘአንጾኪያ “ወይኩን ሲኖዶስ ዘጳጳሳት ፪ተ ጊዜያተ በበዓመት - የጳጳሳት ጉባኤም በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን” ብለው በደነገጉት ቀኖና መሠረት፤ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመራው፣ የሐዋርያት መንበር ወራሽ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤውን በኅብረተ መንፈስ ቅዱስ ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ አካሄዷል፡፡

ምልዓተ ጉባኤው ስለ ሀገር ሰላም፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አንድነት፤ ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነትና ክብር፣ በአጠቃላይ ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ሰፊ ውይይቶችን በማድረግ ዘመኑን የዋጁ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ ከውሳኔዎቹም መካከል፡-

የቤተ ክርስቲያናችንን አንድነት መጠበቅና ማስጠበቅ የቅዱስ ሲኖዶስ ተግባር በመሆኑ ጥንታዊትና ሐዋርያዊት የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን በአንድነቷና በሉዓላዊነቷ እንደተረከብናት ለወደፊቱም ሉዓላዊ ክብሯ ተጠብቆ እንድትቀጥል በምልዓተ ጉባኤው የተሠየመው በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራው “የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት” ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ በተረጋጋ መንገድ እንዲካሄድ፣ ለሀገር ሰላምና ለሕዝብ አንድነት በሚጠቅም ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምትጸልይ ሲሆን ምርጫው በሁሉም ወገን ለኢትዮጵውያን ዘላቂ ሰላምንና መረጋጋትን የሚያስገኝ ሆኖ እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ያሳስባል፡፡

ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የአርሲ ሀገረ ስብከትን በሊቀ ጵጵስና በቋሚነት እንዲመሩ፣ ሕዝቡን እንዲያጽናኑ እየደረሰ ያለውን ችግር ከቋሚ ሲኖዶስና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ከሚመራው የሰላም ኮሚቴ ጋር በመሆን የሚመለከተውን የመንግሥት አካል በማነጋገር ዘላቂ መፍትሔ እንዲያፈላልጉ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡

ከጥንት ጀምሮ “ቅዱስ ሲኖዶስ” በሚል ርእስ እየተዘጋጀ ይታተም የነበረው ታሪካዊ መጽሔት የቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖናዊ ውሳኔዎችን በማካተት በቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስፈጻሚነት ሕትመቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

የቤተ ክርስቲያናችንን ደንቦች መመሪያዎች መርምሮ ማጽደቅ የቅዱስ ሲኖዶስ ሉዓላዊ ሥልጣን በመሆኑ፡-

የስብከተ ወንጌል ሐዋርያዊ ተልእኮ ማስፈጸሚያ ደንብ በብፁዕ አቡነ ማርቆስ ሰብሳቢነት

የአንድነት ገዳማት ኅብረት መተዳደሪያ ደንብ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስና ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ባሉበት በድጋሚ እንዲታይና ሌሎቹም ለውሳኔ የቀረቡ ደንቦች በሊቃውንትና በሕግ ባለሙያዎች ታርመው ለጥቅምት 2019 ዓ/ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርቡ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል

የቀድሞው የሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ “የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድረክ”ና “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ” በሚሉ አርእስት አዘጋጅተው ያሳተሟቸው መጻሕፍትን የማሳተምና የማሰራጨት የባለቤትነት መብት ከሚያዝያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም እንዲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

ከተለያዩ አህጉረ ስብከት በቀረቡ ጥናቶችና የማጣራት ውጤቶች መሠረት፡-

የደቡብ ሱዳን ሀገረ ስብከት ከምሥራቅ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ጋር ተደርቦ በብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ሊቀ ጳጳስ እንዲመራ፤
ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል ሊቀ ጳጳስ የጋምቤላንና የቤንሻንጉል ጉምዝ አህጉረ ስብከትን ብቻ እንዲመሩ፤
ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ የጅማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጰስ የሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከትን እንደያዙ እንዲቀጥሉ፤
ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የቡኖ በደሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከትን ደርበው በአባትነት እንዲመሩ፣
የኮንታ ዞን ሀገረ ስብከት እንዲሆን የቀረበው ጥያቄ የጸደቀ በመሆኑ ሀገረ ስብከቱ ራሱን ችሎ እንዲደራጅና በብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ ሊቀ ጳጳስ እንዲመራ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የልማት ተግባራትን ምልዓተ ጉባኤው በከፍተኛ ደረጃ በማድነቅ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ/ ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ሲቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ በአባታዊ አመራር የፈጸሙት አስደናቂ የሥራ አፈጻጸም በጉልህ የሚታይ ለውጥ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን የሚጠቅም፣ ሉዓላዊ ክብሯን የሚያስጠበቅ፣ ለሁሉም አበው ምሳሌነት ያለው በመሆኑ ምልዓተ ጉባኤው እጅግ ከፍ ባለ ክብር አመስግኗል፡፡

በዚህም መሠረት በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጁ አባታዊ መሪነት እየተከናወኑ ያሉት ተግባራት ማለትም፡-

የቤተ ክርስቲያንን ቀደምት ሠነዶች በዲጂታል ቴክኖሎጅ እንዲደራጁ የተደረገበት ሥልት ተጠናክሮ እንዲቀጥል፤

ከ1970 ዓ/ም ጀምሮ በመጋዝን ተከማችተው የቆዩ በርካታ ልዩ ልዩ መጻሕፍትን የማሠራጨት ሂደት በተጀመረው መንገድ እንዲጠናቀቅ፤

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የኢንፎርሜሽንና ኮምኒኬሽን ተጠቃሚ እንድትሆን የተጀመረው ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ በሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን መዋቅር በየደረጃው ተጠናክሮ ተግባራዊ እንዲሆን፤

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥር የተጀመሩ የሕንፃ ግንባታዎችና አጠቃላይ የልማት ሥራዎች በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ሁሉም አህጉረ ስብከትና ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋጽኦና ትብብር እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ያሳስባል፡፡

በሰሜን አሜሪካ የሰሜን ካሊፎርኒያ፣ ኔቫዳና አሪዞና ሀገረ ስብከት ኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስና ቅድስት አርሴማ ገዳም የመንፈሳዊ ኮሌጅ፣ የአብነት ት/ቤት ሥርዓተ ትምህርት የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ታሪክና ትውፊት በጠበቀ መልኩ ተጠናክሮ መዋቅራዊ ተጠሪነቱም በአግባቡ ተጠብቆ ሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ያቀረበውን የ2019 ዓ/ም በጀት በማጽደቅ በተገቢው መንገድ ሥራ ላይ እንዲውል ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡

በመጨረሻም ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በተነጋገረባቸው ጉዳዮች በትኩረት የተወያየው የቤተ ክርስቲያናችንን ሁለንተናዊ ዕድገትና ተቋማዊ ሕልውና ስለማስጠበቅ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ሀገራችንን ጨምሮ በመላው ዓለም እየታየ ያለው ግጭትና የሰላም መታጣት በእጅጉ አሳስቦታል፡፡

በመሆኑም ስለ ዓለምና ስለ ሀገራችን ሰላም፣ ስለ ሰው ልጆች ደኅንነት፣ በየቦታው በሃማኖታቸው ምክንያት መከራ የሚደርስባቸውን በየቦታው የሚገኙና ግጭት ባለባቸው ቦታዎች ያሉ ኦርቶዶክሳውያንን በማሰብ በመጪው የ2018 ዓ/ም ጾመ ሐዋርያት በመላው ዓለም ባሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማት፣ አድባራትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ጸሎተ ምሕላ እንዲደርስ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

በመላው ዓለም፣ በደቡብ አፍሪካና በሳውዲ ዐረቢያ የሚኖሩ ዜጎቻችን ሰብዓዊ መብት እንዲከበር፣ የርኅራኄ ምሕረትና ፍትሕ እንዲያገኙ የሚመለከታቸው አካላት ተገቢውን ክትትል እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ ሐዋርያዊ ጥሪውን በማቅረብ ለሰባት ቀናት ሲያካሂድ የሰነበተውን ቀኖናዊ ጉባኤ ዛሬ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም. በጸሎት አጠናቋል፡፡

“እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ”

አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ/ም

14/05/2026

ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጉራጌ ሀገረ ስብከት የዩቲዩብ ቻናል ነው።

የከባሮ ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ምረቃ
14/05/2026

የከባሮ ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ምረቃ

ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጉራጌ ሀገረ ስብከት የዩቲዩብ ቻናል ነው።

ተቋማዊ አሠራርና በዕውቀትና በክህሎት ማዘመን
14/05/2026

ተቋማዊ አሠራርና በዕውቀትና በክህሎት ማዘመን

ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጉራጌ ሀገረ ስብከት የዩቲዩብ ቻናል ነው።

Address

Welk'it'e
366

Telephone

+251909019988

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሳሌም ሚዲያ ጉራጌ ሀገረ ስብከት/Gurage Diocese posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share