የወላይታ ቀጣና ቃ/ሕ/ቤ/ክ ጽ/ቤት

የወላይታ  ቀጣና ቃ/ሕ/ቤ/ክ ጽ/ቤት ኢየሱስ የሞተው ለእርስዎ ነው።

Jesus died for you.

ሰላም ቅዱሳን!ትውልድን ማገልገል የነገ ቤተ ክርስቲያንን ማዘጋጀት ነው። በወላይታ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ትኩረት ከተሰጣቸው አገልግሎች አንዱ የወጣቶች አገልግሎት ሲሆን በወጣቶች ...
25/05/2026

ሰላም ቅዱሳን!
ትውልድን ማገልገል የነገ ቤተ ክርስቲያንን ማዘጋጀት ነው።
በወላይታ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ትኩረት ከተሰጣቸው አገልግሎች አንዱ የወጣቶች አገልግሎት ሲሆን በወጣቶች ዘርፍ ከሚከናወኑ ተግባራት ቀዳሚው የተማሪዎች እና ምሩቃን አገልግሎት በመሆኑ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን አባል ተማሪዎች ኀብረት በቀን 14/09/2018 ዓ.ም ዓመታዊ የአንድነት ጊዜአቸውን በሶዶ ስታዲየም አጥቢያ በማካሄድ ተመራቂ ክርስቲያን ተማሪዎች ሽኝትም በማድረግ ፕሮግራሙ በስኬት የተጠናቀቀ ስለሆነ የተማሪዎች ኅብረት መሪዎችና አስተባባሪን እንዲሁም የሶዶ ስታዲየም አጥቢያ ቃለ ሕይወት ቤ/ክ መሪዎችን ከልብ እናመሰግናለን።
"...ማናቸውን ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት።" 1ቆሮ 10:31
ጠረጴዛ ወላይታ ሶዶ ኢትዮጵያ

20/05/2026

ዶክተር አበራ አየለ

ሰላም ቅዱሳን!በወላይታ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የጠረጴዛ ልማት ማህበር የሰው ልጆች ሁለንተና በማገልገል የሚታወቅ ሲሆን ከጊዜ ወደ ጊዜ በማደግ በአሁኑጊዜ በአምስት ክልሎች ማለትም...
12/05/2026

ሰላም ቅዱሳን!
በወላይታ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የጠረጴዛ ልማት ማህበር የሰው ልጆች ሁለንተና በማገልገል የሚታወቅ ሲሆን ከጊዜ ወደ ጊዜ በማደግ በአሁኑጊዜ በአምስት ክልሎች ማለትም በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ በሲዳማ እና በኦሮሚያ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን በመስጠት አኩሪ ተግባር በማስመዝገብ የሚገኝ በመሆኑ ዛሬ በሶዶ ከተማ ዳልቦ ወጋኔ አካባቢ የሚገኙ 11,000 በላይ ሰዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ንጹህ መጠጥ ውኃ በመገንባት ለመንግሥትና ለአካባቢው ማህበረሰብ በማስረከቡ ለዚህ ተግባር የተጉ ወገኖችን እያመሰገንን በጎ ሥራዎች እንዲቀጥሉ እናበረታታለን ።
ግንቦት 04/2018 ዓ.ም
ጠረጴዛ ወላይታ ሶዶ ኢትዮጵያ

ሰላም ቅዱሳን !የቤተ ክርስቲያን ተሐድሶ ሁለንተናዊ ልሆን ይገባል ። እንዲሁም የቤተ ክርስቲያን መሪዎችና አገልጋዮች አገልግሎታቸው ሁለንተናዊ ልሆንና በሁሉም አቅጣጫ ምሳሌ ሆኖ መገኘት መጽሐ...
11/05/2026

ሰላም ቅዱሳን !
የቤተ ክርስቲያን ተሐድሶ ሁለንተናዊ ልሆን ይገባል ። እንዲሁም የቤተ ክርስቲያን መሪዎችና አገልጋዮች አገልግሎታቸው ሁለንተናዊ ልሆንና በሁሉም አቅጣጫ ምሳሌ ሆኖ መገኘት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው። በሌላ በኩል በሁሉም አካባቢ የሚገኙ የቤተ ክርስቲያን ግቢዎችና የእርሻ መሬቶች ልለሙና ዘርፈ ብዙ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ማድረግ የሁሉም አማኝ ተግባር መሆን አለበት ።

"... ምድር የእግዚአብሔርን ክብር በማወቅ ትሞላለችና ።" ዕን 2:14
07/05/2026

"... ምድር የእግዚአብሔርን ክብር በማወቅ ትሞላለችና ።" ዕን 2:14

ሰላም ቅዱሳን !በወላይታ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ቀደምት ወንጌል አገልጋዮች መካከል አንዱ የሆኑት ወንጌል በመስበክና ዝማረን በማቅረብ ለምሳሌ "ኑናራ ዲያጌ ኡባ ጦንያጋ" "ጦሳይ ...
01/05/2026

ሰላም ቅዱሳን !
በወላይታ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ቀደምት ወንጌል አገልጋዮች መካከል አንዱ የሆኑት ወንጌል በመስበክና ዝማረን በማቅረብ ለምሳሌ "ኑናራ ዲያጌ ኡባ ጦንያጋ" "ጦሳይ ታማ ድርሣ ባርናቱስ" በማለት ለእግዚአብሔር ክብር በመዘመር የሚታወቁ የወንጌል አርበኛ አባባ ማርቆስ ሄቫና ወዳገለገሉት ጌታ በክብር ስለተሰበሰቡ እግዚአብሔርን እያመሰገንን ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን እንመኛለን ።
"መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤" 2 ጢሞ 4:7

ሰላም ቅዱሳን!እኚህ አባት አቶ አረአያ ይባላሉ በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤ/ክ የጡረታ ኮሚሽን ሠራተኛ ናቸው ። በወላይታ ቀጣና ጽ/ቤት ከአሥር ዓመት በፊት የአገልጋዮች ጡረታ በማህበራዊ ዋስት...
30/04/2026

ሰላም ቅዱሳን!
እኚህ አባት አቶ አረአያ ይባላሉ በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤ/ክ የጡረታ ኮሚሽን ሠራተኛ ናቸው ። በወላይታ ቀጣና ጽ/ቤት ከአሥር ዓመት በፊት የአገልጋዮች ጡረታ በማህበራዊ ዋስትና እንዲከበር በእንባ ያስተማሩና ዛሬ ፍሬ አፍርቶ 51 አባቶችና እናቶች የጡረታ አቤል ተጠቃሚ እንዲሆኑና 1,000 በላይ አገልጋዮች እንዲታቀፉ ዋጋ በመክፈል ተግቶ ያስተማሩ ጀግና አባት በመሆናቸው የወላይታ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤ/ክ ጽ/ቤት ማስታወሻ ይሆናቸው ዘንድ ጋቢ በማልበስ ፍቅር አጋርተዋል ።
ክብር ለጌታ ይሁን !
ቀን 22/08/2018 ዓ.ም

በአረካ ከተማ ቁ.1 ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን እና ከከተማው አስተዳደር መካከል የተፈጠረው ክፍተት በበሰለ አካሄድ እንዲፈታ በጥበብ የመራውን የወላይታ ዞን የፊት አመራሮችን በወላይታ ቀጣና...
27/04/2026

በአረካ ከተማ ቁ.1 ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን እና ከከተማው አስተዳደር መካከል የተፈጠረው ክፍተት በበሰለ አካሄድ እንዲፈታ በጥበብ የመራውን የወላይታ ዞን የፊት አመራሮችን በወላይታ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ስም ከልብ እናመሰግናለን ።

ቤተ ክርስቲያን ተተኪ አገልጋዮችን በማዘጋጀትና እንደተሰጣቸው ጸጋ የአገልግሎት ሥምሪት መስጠት በተሐድሶ ከሚከናወኑ ተግባራት ቀዳሚ ልሆን ይገባል።መጋቢ በረከት ጸጋ ይብዛልህ!
19/04/2026

ቤተ ክርስቲያን ተተኪ አገልጋዮችን በማዘጋጀትና እንደተሰጣቸው ጸጋ የአገልግሎት ሥምሪት መስጠት በተሐድሶ ከሚከናወኑ ተግባራት ቀዳሚ ልሆን ይገባል።
መጋቢ በረከት ጸጋ ይብዛልህ!

የሰላማችን ምክንያት በሆነው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሁላችንም ሰላም እላችኋለሁ!በወላይታ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ስም እንኳን ለ2018 ዓ.ም ለጌታችንና ለመድሃኒታችን ለኢየሱ...
11/04/2026

የሰላማችን ምክንያት በሆነው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሁላችንም ሰላም እላችኋለሁ!
በወላይታ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ስም እንኳን ለ2018 ዓ.ም ለጌታችንና ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳዔ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
የበዓሉ መታሰቢያነት ከተለመደ የመብልና የመጠጥ ፌሽታ ያለፈ የእምነታችን መሰረት የተጣለበት ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑ በሁላችንም ዘንድ የሚታወቅ ነው።
ይሁን እንጂ ከማወቅ ባለፈ እውነታውን በተግባር ከመግለጥና ከመንፈሳዊ እሴት ይልቅ ልማዳዊ አከባበሩ እየጎላ የበዓሉ መንፈሳዊ እሴት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየደበዘዘ ከይቅርታ ይልቅ ቂም መወጣት፣ ከትህትና ይልቅ የእልከኝነት ስሜት፣ በትዕግስት ከመፅናት ይልቅ ችኩልነት በመጉላቱ ከመንፈሳዊነቱ ይልቅ ዓለማዊነቱ እየጎላ እየሄደ እንደሆነ ማንንም ምስክር መጥራት ሳያስፈልግ የእያንዳንዳችን ሕይወት በራሱ ይመሰክራል።
ከተለመደ የቀድሞ ዓለማዊ ሕይወት ይልቅ የአዲሱን ሰው ሕይወት በተግባር እያሳየን በዓሉን ማክበር እንድንችል የማስተዋልና የጥበብ ሁሉ አባታችን እግዚአብሔር ማስተዋልን ይስጠን እያልኩኝ በዓሉን ስናከብር እስከ መስቀል ሞት የተዘዘውን ኢየሱስን እያየን በመታዘዝ ሕይወት፣ ሲገርፉት፣ ሲተፉበት ሲሳደቡትና ሲያንገላቱት ዝም ብሎ የታገሰውን እያየን በትዕግስት፣ በሰው አዕምሮ ሊገለፅ በማይችል እግልትና ግርፋት ያውም የሚሰቀልበትን መስቀል ተሸክሞ ደም እየፈሰሰው እስከ ጎልጎታ ተጉዞ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ነብሱ ከስጋው ልትለይ በተቃረበችበት ሰዓት የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ያለውን ይቅርታ እያሰብን እርስ በርስ ይቅር እየተባባልን በፍፁም ይቅርታ በዓሉን ትርጉም ያለው መንፈሳዊ ሕይወት በተግባር እያሳየን ማክበር እንድንችል እኔ በጌታ ወንድማችሁ ከልብ ከመነጨ ትህትና ጋር ላሳስባችሁ እወዳለሁ።
በቀጣዩ የእድሜ ዘመናችንም ይህንኑ የአዲሱን ሰው የሕይወት ዘይቤ የሰሞነኛ የበዓል ባህሪይ እና ተግባር ብቻ ሳይሆን የእለት-ተዕለት ማንነታችንን ማሳያና በሌሎች ዘንድ ደቀመዝሙር መሆናችንን እያስመሰከርን እንድንኖር እግዚአብሔር ጸጋውን ያብዛልን እያልኩኝ በበዓል ወቅት እንድንባረክባቸው እግዚአብሔር በመካከላችን ያስቀመጣቸውን በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ወገኖቻችንን እያሰብ ካለን በማካፈል እኛን ብቻ ሳይሆን የበዓሉን ባለቤት የሚያስደስት ተግባርም እየፈጸምን እንድናከብር እያሳሰብኩ በድጋሚ በዓሉ የሰላም፣ የይቅርታ፣ የደስታ እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ በጌታ መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ።
እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካችሁ!
መ/ቢ አብርሃም ቦታ
የወላይታ ቀጣና ዋና ፀሐፊ

Address

S**o

Telephone

+251465516588

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የወላይታ ቀጣና ቃ/ሕ/ቤ/ክ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share