ጉኑኖ ከተማ ስታዲየም KHC ቤቴል መዘመራን/Gununo stadium khc Bethel singers/

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • ጉኑኖ ከተማ ስታዲየም KHC ቤቴል መዘመራን/Gununo stadium khc Bethel singers/

ጉኑኖ ከተማ ስታዲየም KHC ቤቴል መዘመራን/Gununo stadium khc Bethel singers/ እርሱ ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፥ ቤዛነቱንም እርሱንም የኃጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን። ቆላስስ 1፥13-14

ወንጌል — ለእውነተኛይቱ ቤተ ክርስቲያን አንገብጋቢ የሆነው ተግባር የምሥራቹን መልዕክት ለዓለም ማዳረስ ነውወንጌል ለእውነተኛይቱ ቤተ ክርስቲያን እጅግ አንገብጋቢ የምሥራች መልዕክት ነው። ም...
29/05/2026

ወንጌል — ለእውነተኛይቱ ቤተ ክርስቲያን አንገብጋቢ የሆነው ተግባር የምሥራቹን መልዕክት ለዓለም ማዳረስ ነው

ወንጌል ለእውነተኛይቱ ቤተ ክርስቲያን እጅግ አንገብጋቢ የምሥራች መልዕክት ነው። ምክንያቱም፦

1. ክርስቶስ አዝዟታል
«ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፦ “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።”»
(ማቴዎስ 28፡18-20)
ይህ ትእዛዝ ለቤተ ክርስቲያን የተሰጠ ታላቅ ተልዕኮ ነው። ስለዚህ ወንጌልን መስበክ አማራጭ ሳይሆን የጌታ ትእዛዝ ነው።

2. ክርስቶስ ለመዳን ብቸኛው መንገድ ነው
መንግሥተ ሰማይን የሚያስገባ ወይም ሰው ከኃጢአቱ ይቅርታ አግኝቶ ከእግዚአብሔር ጋር እርቅ የሚያደርግበት ሌላ መንገድ የለም። በሌላ መንገድ ወደ አብ መድረስ አይቻልም። ድነት በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ይገኛል።
«ኢየሱስም፦ “እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።”» (ዮሐንስ 14፡6)

3. ክርስቶስ ስለ ዓለም ሞቷል
ክርስቶስ የሞተው በኃጢአት ምክንያት ከእግዚአብሔር የተለየው የሰው ልጅ በእርሱ በማመን እንዲድን ነው።
«በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ፥ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።» (ዮሐንስ 3፡16)

4. ለወንጌል ሥራ ቅድሚያ የማትሰጥ ቤተ ክርስቲያን ታላቁን ተልዕኮ እየተላለፈች ነው
ብዙ መሪ አገልጋዮች ስለ ወንጌል መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት ቢያስተምሩም፣ በተግባር ግን የሚቀድሙት ምድራዊና ቁሳዊ ጉዳዮች መሆናቸውን በግልጽ ማየት ይቻላል።
ወንጌል ለእውነተኛይቱና ታዛዥ ቤተ ክርስቲያን ከጌታዋ የተሰጣት “ታላቅ ተልዕኮ” ነው። ስለዚህ በጌታችን ፊት ከመቆማችን በፊት ራሳችንን በጊዜ መመርመርና እየታዘዝን መሆናችንን ማረጋገጥ ይገባናል።

5. ወደ ውጭ ለወንጌል ሥርጭት የማትወጣ ቤተ ክርስቲያን ውስጣዊ ጤናዋን ልትመረምር ይገባታል
በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የተሞሉ ደቀ መዛሙርት ያሏት ቤተ ክርስቲያን ከወንጌል ሥራ የምታስቀድመው ሌላ ነገር አይኖራትም። የጌታቸውን መሥዋዕትነት የተረዱ ቅዱሳን ለነፍሳት መዳን ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣሉ።
በምዕመናኗ ቁጥር ብቻ የረካች እና ወደ ጥፋት የሚሄዱትን ለማየት ያልተጨነቀች ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔርን መንግሥት ሥራ ችላ ትላለች።

«ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ።» (የሐዋርያት ሥራ 1፡8)

«ወንጌልን ብሰብክ እንኳ የምመካበት የለኝም፤ ግድ ደርሶብኝ ነውና፤ ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ።» (1ኛ ቆሮንቶስ 9፡16)

«እንዲህም አላቸው፦ “ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ። ያመነና የተጠመቀ ይድናል፤ ያላመነ ግን ይፈረድበታል።”» (ማርቆስ 16፡15-16)

ታላቁ ተልዕኮ በእውነት ለተረዱት ለኢየሱስ ክርስቶስ ተከታዮች መተኪያ የሌለው ታላቅ መልዕክት ነው!

#ምንጭ፦ አገልጋይ ወርቅነህ አብርሃም ዋንዳሮ

29/05/2026
20/05/2026

ሚስዮናዊ ዶ/ር አበራ አየለ

ለሐሰት አሠራር የተጋለጡ እነማን ናቸው?ከእውነት መሳት አደገኛ ነገር ነው፡፡ እውነትን የሚያስጥሉ እና እንድንሳሳት የሚያደርጉ አሳቾች በምድር ላይ ቁጥራቸው እየጨመረ ይገኛል፡፡ ብዙዎችም ለስ...
19/05/2026

ለሐሰት አሠራር የተጋለጡ እነማን ናቸው?

ከእውነት መሳት አደገኛ ነገር ነው፡፡ እውነትን የሚያስጥሉ እና እንድንሳሳት የሚያደርጉ አሳቾች በምድር ላይ ቁጥራቸው እየጨመረ ይገኛል፡፡ ብዙዎችም ለስህተት መጋለጣቸውን በግልጥ እያየን እንገኛለን፡፡ ሰዎች እንዲስቱ ምክንያት የሆኑ ነገሮችን በጥቂቱ ላወጋችሁ እና እንዴት ከዚህ አደገኛ የሰይጣን ስትራቴጂ ማምለጥ እንደሚቻል ከእግዚአብሔር ቃል እውነት ላሳያችሁ ወድጃለሁ፡፡ ለስህተት የተጋለጡ ሰዎች፡-

1. በግል ምኞት የተወሰዱ/የተገዙ ሰዎች (Obsessed with Personal Desires) ለሐሰተኛው አሠራር የተጋለጡ ናቸው፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰዎች ከእግዚአብሔር ፈቃድ ይልቅ የራሳቸውን ፍላጎትና ደስታ የሚያስቀድሙ ናቸው። የሕይወታቸው መሪ መርህ መለኮታዊ እውነት ሳይሆን ግላዊ ምኞት ነው። ስለዚህ የሚፈልጉትን ለማሳካት ሲሉ ማንኛውንም መንገድ ለመጠቀም ዝግጁ ይሆናሉ። በዚህ ሁኔታ ተድላ በሕይወታቸው ውስጥ ከእግዚአብሔር ፈቃድ በላይ ቦታ ይይዛል።
- በራስ ፈቃድና በኃጢአተኛ ምኞት መመራት መጨረሻው መንፈሳዊ ጥፋት ነው። “ነገር ግን እያንዳንዱ በገዛ ምኞቱ ሲሳብና ሲታለል ይፈተናል፤ ከዚያም ምኞት ፀንሶ ኃጢአትን ይወልዳል፥ ኃጢአትም በበሰለ ጊዜ ሞትን ይወልዳል።” (ያዕ. 1:14-15)
- ስለዚህ ክርስቲያኖች ከኃጢአተኛ ምኞቶች ራሳቸውን በመጠበቅ ከጌታ በሆነላቸው በአዲሱ ሰውነት/ማንነት እንዲመላለሱ ተጠርተዋል። “20 እናንተ ግን ክርስቶስን እንደዚህ አልተማራችሁም፤ 21 በእርግጥ ሰምታችሁታልና፥ እውነትም በኢየሱስ እንዳለ በእርሱ ተምራችኋል፤ 22 ከቀድሞ ኑሯችሁ የተነሣ በሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፤ 23 በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፤ 24 በእውነተኛ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ።” (ኤፌ. 4:20-24)

2. እውነተኛ አስተምህሮን የማይታገሡ ሰዎች ለሐሰተኛው የስህተት አሠራር የተጋለጡ ናቸው፡፡

- በዘመኑ ውስጥ የሚታየው አንዱ መንፈሳዊ ችግር ሰዎች ጤናማ ትምህርትን ከመቀበል ይልቅ ለራሳቸው ምኞት የሚስማማ መልእክትን መፈለጋቸው ነው። ይህም ከእውነት መራቅንና ወደ ሐሰተኛ አስተምህሮ መዘንበልን ያሳያል። “3 ጤናማውን ትምህርት የማይታገሡበት ዘመን ይመጣልና፤ ነገር ግን ጆሮአቸውን የሚያሳክክ ነገር ስለሚፈልጉ፥ እንደ ገዛ ምኞታቸው ለራሳቸው አስተማሪዎችን ያከማቻሉ። 4 ከእውነትም ጆሮአቸውን ይመልሳሉ፥ ወደ ተረትም ፈቀቅ ይላሉ።” (2 ጢሞ. 4:3-4)

- በታሪክ ውስጥ እውነተኛ ነቢያትና የእግዚአብሔር አገልጋዮች ተቃውሞና ስደት ያጋጠማቸው መሆኑ ይታወቃል። ነቢዩ ኤርምያስ ከዚህ ግልጽ ምሳሌ አንዱ ነው። (ኤር. 18:1-11፣ 18፤ ኤር. 36:1-3፣ 20-26

3. በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ በተገለጠው እውነት ላይ መደራደር/ማመቻመች ሰዎች ለስህተት የተጋለጡ እንዲሆኑ ያደርጋል፡፡
- ሐሰትን ማመን እውነትን ሊለውጥ አይችልም። እውነት ከሰው አመለካከት ወይም ከስሜት ጋር ተያይዞ የሚለዋወጥ ሳይሆን በእግዚአብሔር ባሕርይ ላይ የተመሠረተ ፍጹም እውነት ነው። 12 “ይህን ቃል አቃልላችኋልና፥ በግፍና በጠማማነትም ታምናችኋልና፥ በእርሱም ተደግፋችኋልና፤ 13 ስለዚህ ይህ ኃጢአት እንደ ሊወድቅ የቀረበ ከፍ ያለ ቅጥር ይሆንባችኋል፤ ውድቀቱም ድንገት ይመጣል። 14 የሸክላ ማድጋ እንደሚሰበር ይሰብረዋል።” (ኢሳ. 30:12-14)

- እውነት ሁልጊዜ ለሰው ምቹ ላይሆን ይችላል፤ ሆኖም ግን ለመንፈሳዊ እድገትና ለድነት አስፈላጊ ነው። ‹‹27 ንጉሡ ክርታሱን ካቃጠለ በኋላ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ መጣ፤ 28 “ዳግመኛ ሌላ ክርታስ ውሰድ፤ በፊተኛውም ክርታስ ላይ የነበረውን ቃል ሁሉ ጻፍበት።” 29 “ይህን ክርታስ ለምን አቃጠልህ?” በማለት ንጉሡን ገሠጸው። (ኤር. 36:27-29)

- ስለዚህ ለእውነት ያለን መሰጠት ጽኑና የማይናወጥ ሊሆን ይገባል። ቤተ ክርስቲያን እንደ ክርስቶስ አካል በንጽሕና፣ በቅድስናና በትጋት እንድትመላለስ እግዚአብሔር ጥበቡን፣ ማስተዋሉንና ጸጋውን ያብዛልን።

እንግዲህ ከእኛ ምን ይጠበቃል?
1. መዘጋጀት (ሉቃ12፡35-40)
2. ራሳችንን መመርመር (2ቆሮ 13፡5) ‹‹5 በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ ወይስ ምናልባት የማትበቁ ባትሆኑ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ እንዳለ ስለ እናንተ አታውቁምን?››
3. መንቃት (ሮሜ 13፡11-14) ‹‹11 ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና።12 ሌሊቱ አልፎአል፥ ቀኑም ቀርቦአል። እንግዲህ የጨለማውን ሥራ አውጥተን የብርሃንን ጋሻ ጦር እንልበስ።13 በቀን እንደምንሆን በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን፤14 ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም ለሥጋ አታስቡ።››
4. በመጠን መኖር (1ጴጥ5፡8) “8-9 እርሱንም ሳታዩት ትወዱታላችሁ፤ አሁንም ምንም ባታዩት በእርሱ አምናችሁ፥ የእምነታችሁን ፍፃሜ እርሱም የነፍሳችሁን መዳን እየተቀበላችሁ፥ በማይነገርና ክብር በሞላበት ሐሤት ደስ ይላችኋል።” (1ተስ5፡9) “8 እኛ ግን ከቀን ስለ ሆንን፥ የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር የመዳንንም ተስፋ እንደ ራስ ቁር እየለበስን በመጠን እንኑር፤”
5. ዘመኑን መመርመር/መከታተል(ማቴ16፡1-4፣ ቆላ4፡5፣ ኤፌ5፡15-17)
6. የትንቢት ፍጻሜዎችን መከታተል (ሉቃ13፡28-31)
7. ሳያቋርጡ መጸለይ( ሉቃ 21፡37፡)
8. የእግዚአብሔርን ቃል በትጋት ማጥናት(ኤፌ6፡17፣ሮሜ15፡4፣ማቴ4፡1-10)
ከአሳቹ ተጠብቀን ተስፋችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በታላቅ ንቃትና ዝግጅት እንቀበለው ዘንድ ጌታ በጸጋው ይደግፈን!
አገልጋይ ወርቅነህ አብርሃም ዋንዳሮ

-------የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፥ እኛም ባሪያዎቹ ተነሥተን እንሠራለን፤ (መጽሐፈ ነሀምያ 2:20) **************ውድ በሀገርና ከሀገር ውጭ ለሚገኙ ክርስቲያኖች እና የቤቴል ...
18/05/2026

-------የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፥ እኛም ባሪያዎቹ ተነሥተን እንሠራለን፤
(መጽሐፈ ነሀምያ 2:20)
**************
ውድ በሀገርና ከሀገር ውጭ ለሚገኙ ክርስቲያኖች እና የቤቴል ቤተሰብ አባላትና የእግዚአብሔር ብሩካኖች በሙሉ !!

በኢትዮጵያ ቃለ ህይወት በደቡብ ኦሞ ቀጠና በማሌ ዋርጋታ አጥቢያት ህብረት እነሆ "ቤቴል" የእግዚአብሔር ቤትን በጋራ እንስራ በሚል በመንፈሳዊ መነሳሳት ቁጭት ቤቱን ጀምሮ በማገባደድ ላይ ይገኛል ።
ይህን የእግዚአብሔር ቤት ሥራ በርካቶች እግዚአብሔር በጉልበት ፤ በገንዘብ እንዲሁም በእውቀት ባርኳቸው በድጋፍና በፀሎት ከጎናቸዉ ሆኖ እያገዙ ይገኛል ።

አሁንም ቤቱ ሙሉ በሙሉ ተሰርቶ እንዲያልቅ የብዙሃኑን ተሳትፎ በብርቱ ያሻልና በአቅማችሁ ልክ ጌታን በመስጠት እንዲታገሉት በጌታ ፍቅር እናሳስባለን!!

በማንኛዉም ጊዜ የድጋፍ ገንዘብን ወደ አካዉንታቸዉ ገብ ለማድረግ የምትፈልጉ አካላት " 1000 41 79 68 915" የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ይጠቅሙ ፤

በተጨማሪም ያስገባችሁትን Reciet ፎቶ በታች በተጠቀሰዉ መስመር ማድረስ የሚትችሉ መሆኑን እናሳዉቃለን!!

የቴሌግራም መስመር -:
1. 09-19-64-86-77
2. 099-16-05-66-70
3. 09-12-76-09-15

‎የፀሎት ትርጉም በጥቂቱ ‎‎ፀሎት ማለት:-‎‎1) ከአባታችን እግዚአብሔር ጋር መነጋገር ማለት ነው‎‎✅ለእግዚአብሔር መነገርና ከእግዚአብሔር መስማትም ነው፡።‎✅ይህ በቀላሉ የማይገኝ በልጁ በ...
14/05/2026

‎የፀሎት ትርጉም በጥቂቱ

‎ፀሎት ማለት:-

‎1) ከአባታችን እግዚአብሔር ጋር መነጋገር ማለት ነው

‎✅ለእግዚአብሔር መነገርና ከእግዚአብሔር መስማትም ነው፡።
‎✅ይህ በቀላሉ የማይገኝ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የተገኘ የልጅነት ስልጣን ነው፡
‎✅ይህ በኢየሱስ ሞት የቅድስታ ቅዱሳን መጋረጃ ስለተቀደደ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ዘልቀን የመግባት ትልቅ እድል ነው፡

‎2) መለኮታዊ አየር መተንፈስ ማለት ነው።

‎✅ትንፋሽ ተነፍጎ አንዲትን ደቂቃ እንኳን መቆያት አይቻልም፣
‎✅ስለዚህ በመንፈሳዊ ዓለም ውጤታማ ለመሆን የፀሎት ትጋት ቁልፍ ሚና አለው፣
‎✅ይህም ባለማቋረጥ ዘወትር መጸለይ ለአማኞች ሁሉ የተሰጠ ግዴታ እንጂ ውዴታ አለመሆኑን የሚያመለክት ነው፣
‎=>ፀሎት ጀምሮ ማቋረጥ ሳይጣንን ለሥራ ቀስቅሰው እንደመተኛት ያለ ሞኝነት ነውና እንንቃ!! እንትጋ!!

‎3) የእግዚአብሔርን እጅ ሳይሆን ፊቱን መፈለግ ነው።

‎Ⓐ እጁ ይሰጠናል ፊቱ ግን ይለውጠናልና የሚለውጠን ፊቱ ይበልጥብናል፤ተቀብለን ካልተለወጠን ትርጉም የለውምና!!!
‎Ⓑ ፊቱን መፈለግ ማለት ደግሞ በህልውና ውስጥ መቆያት ማለት ሲሆን በህልውና ውስጥ ስንሆን የሚጎድለን ነገር አይኖርም።

‎4) በእግዚአብሔር መደገፍ ማለት ነው።

‎✅ይህ ማለት ደግሞ በራስ ጥበብና ችሎታ አለመመካት ነው፤
‎✅ይህም ለሚንወስዳቸው እርምጃዎች ሁሉ በእግዚአብሔር ኀይልና ምሪት መደገፍ ተገቢ መሆኑን ያመለክታል(1ቆሮ1፥28)
‎✅በተቃራኒ አለመፀለይ ማለት እግዚአብሔርን አታስፈልገኝም በራሴ ልወጠው እንደማለትም ነው፤ ይህም ዋጋ ያስከፍላል። ዶ/ር ደሰታ ላንገና ሲናገሩ "ሲንፀልይ እግዚአብሔር ይሠራል፤ ካልፀለይን እኛ ደግሞ እንሠራለን "ብሎዋሉ፤

‎ማጠቃለያ

‎=>ፀሎት ለሁሉም አማኞች የተሰጠ መለኮታዊ ትዕዛዝ እንጂ የጸጋ ስጦታ አይደለም!!!!
‎=>ፀሎት ሁሉንም በር የሚከፍት ዋና ቁልፍ ነው።
‎=>ስለዚህ የጠልነውን ይህንን ቁልፍ አንስተን በፀሎት እንድንተጋ እግዚአብሔር ይርደን!! አሜን!!

‎Please share for Others!!!👍👍👍👍

ሰላም ቅዱሳን!በወላይታ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የጠረጴዛ ልማት ማህበር የሰው ልጆች ሁለንተና በማገልገል የሚታወቅ ሲሆን ከጊዜ ወደ ጊዜ በማደግ በአሁኑጊዜ በአምስት ክልሎች ማለትም...
12/05/2026

ሰላም ቅዱሳን!
በወላይታ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የጠረጴዛ ልማት ማህበር የሰው ልጆች ሁለንተና በማገልገል የሚታወቅ ሲሆን ከጊዜ ወደ ጊዜ በማደግ በአሁኑጊዜ በአምስት ክልሎች ማለትም በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ በሲዳማ እና በኦሮሚያ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን በመስጠት አኩሪ ተግባር በማስመዝገብ የሚገኝ በመሆኑ ዛሬ በሶዶ ከተማ ዳልቦ ወጋኔ አካባቢ የሚገኙ 11,000 በላይ ሰዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ንጹህ መጠጥ ውኃ በመገንባት ለመንግሥትና ለአካባቢው ማህበረሰብ በማስረከቡ ለዚህ ተግባር የተጉ ወገኖችን እያመሰገንን በጎ ሥራዎች እንቀጥሉ እናበረታታለን ።
ግንቦት 04/2018 ዓ.ም
ጠረጴዛ ወላይታ ሶዶ ኢትዮጵያ

ክፍል ሁለት ወ/ዊ ማሙሻ (ፒኤችዲ)e.g. የሥዕል አድናቂዎች አሉ። ከሥዕሉ መደነቅ በኋላ የሰዓሊውን ፊርማ ያያሉ። ሰዓሊወማ ታዋቂ እንትና ነው ይላሉ። ሰዓሊው ኢየሱስ ስዕሉ እኛ ነን። ሰዎች...
10/05/2026

ክፍል ሁለት ወ/ዊ ማሙሻ (ፒኤችዲ)

e.g. የሥዕል አድናቂዎች አሉ። ከሥዕሉ መደነቅ በኋላ የሰዓሊውን ፊርማ ያያሉ። ሰዓሊወማ ታዋቂ እንትና ነው ይላሉ። ሰዓሊው ኢየሱስ ስዕሉ እኛ ነን። ሰዎች ኢየሱስን በእኛ ተመልክተው ለአርሱ ክብር መስጠት አለባቸው።

እሥራኤላውያን የተጠሩት ለእግዚአብሔር ክብር ነው። ማቴዎሰ "ኑሮአቸውን አይተው የሰማዩን አባት እንዲያከብሩ ነው.." ይላል። ጸጋው በእምነት ቢያድንም፥ እምነት ውጤት አለው፤ የጽድቅ ሥራ።

የሚሻገሩ ማን ናቸው? (የኤፌሶን ጸሎት አሻጋሪ ጸሎት ብለናል።
1)እርሱን የሚያውቁ።👍

ከምዕራፍ አንድ እስከ ሦስት የሆኑትን የሚያውቁ ነው የሚኖሩት። የበለጠ እንዲያዎቁ ደግሞ የጥበብ እና የመገለጥ መንፈስ እንዲሰጣቸው እግዚአብሔርን ይለምናል። ሰጭውን ማወቅ የበለጠ ለመኖር ያገዛል፤ ለእርሱ እንድንኖርለት ይረዳናል። ሰው እግዚአብሔርን የበለጠ ሲያውቅ እግዚአብሔር የሚወደውን ይወድዳል፤ የሚጠላውንም ደግሞ ይጠላል። ዳንኤል 11፥31 ላይ ...አምላካቸውን የሚያውቁ ህዝብ ይበረታሉ ይላል።

ጌታን ማወቅና ስለ ጌታ ማወቅ ይለያል። ዮሐንስ 8 መጽሐፍን ስለሚያውቁ አይሁድ "ኀጢአት የሚያደርጉ ሁሉ የኀጢአት ባሪያ ናቸው።... አብርሃም አባታችሁ አይደለም" አላቸው። "አብርሃም ቀኔን አይቷል። አብርሃም ጨዋ ነው። እንደ እናንተ አይደለም። እነርሱ ግን አንተ አብርሃምን አይተሃል? አሉ። ኢየሱስ አብርሃምን ልጅ አደረገው። አብርሃም ሳይወለድ እኔ እኔ ነኝ አለ። በሲና ተራራ "አኔ አኔ ነኝ" ብሎ ራሱን የገለጠወ አምላክ ኢየሱስ ከርስቶስ ነው። ፈርሳውያን "እኛ የእግዚአብሔር ልጆች ነን" ሲሉ እናንተ የዲያብሎስ ልጆች ናችሁ አለ ኢየሱስ። ወገኖቼ! አየሰበክን፥ አየመሰከረን፥ እየዘመርን፥ እያመለክን የዲያብሎስ ልጆች ልንሆን እንችላለን። የአግዚአብሔር ልጅ መሆን በኑሮ ይገለጣልና።

እግዚአብሔርን ማወቅ መጽሐፍ ቅዱስ በወንድና በሴት መካከል ካለው ግንኙነት ጋር ያስመስለዋል። "አዳም ሔዋንን አወቃት" ከሚለው ማወቅ ጋር አንድ ቃል ነው።

e.g. አስቲ ስለ ዶክተር ዐቢይ የምታውቁ? ሐዝቡን ጠየቀ። ሁሉም አው አለ። እርሱ ያውቃችኋል? ተነካክታችኋል? አብራችሁ በልታችኋል? እነዚህ ይለያያሉ። እግዚአብሔርን የምታውቁ እና እግዚአብሔር የሚያውቋቸው ይለያያሉ።

ከኢየሱስ ጋር ቀረቤታ ካላቸው ደቀመዛሙርት ሦስቱ መካከል ዮሐንስ፥ ጴጥሮስ ያዕቆብ መካከል ዮሐንስ ቀዳሚው ነው። የቅርብ ሆኖ ቢቆይም ኢየሱስን እንደማያውቅ ራዕይ መጽሐፍ ምስክር ነው። " 1:12 ላይ "እኔም የሚናገረኝን ድምፅ ለማየት ዞር አልሁ፤ ዞር ባልሁም ጊዜ ሰባት የወርቅ መቅረዞችን አየሁ፤" ይላል። ድምፅ ለማየት አለ ዮሐንስ። ድምፅ ይሰማል እንጂ አይታይም። ደረቱ፥ ጠጉሩ፥ ዓይኖቹ፥ እጁ፥ ፊቱ፥ ከአፉ የሚወጣው ቃል ... ብሎ በፊት ከሚያውቀው ኢየሱስ የለየውነ አየ። ቁ17 ባየሁህም ጊዜ እንደሞተ ሰው ሆንኩ አለ። እግዚአብሔር ማወቅ የየዕለት መገለጥ ነው። ጌታ ቸር መሆኑን የቀመሰ ያውቃል።

e.g. አንድ ሕጻን አባቱን ጠየቀ። "አባዬ እግዚአብሔር ሁሉም ቦታ አለ? አው። በጊቢያችን አለ? አው አለ። በቤታችንስ? አው። በመኝታ ክፍላችን? አዎ አለ። አባዬ በብርጭቆ ውስጥ አለ? አው ሲል ቶሎ ብሎ ጨበጥ አድርጎ ያዝኩት አለ። ትንሽ ነገር አግኝተን እግዚአብሔርን የያዝን ይመስለናል። በሆነ ልምምድ ውስጥ ገብተን እርሱን የያዝን ይመስለናል። ሁሉን ይዘን ምንም የያዝን መሆን አለብን። ሐዋርያ ጳውሎስ ፊልጵስዩስ 3 የፊቱን ለመያዝ እዘረጋለሁ አለ። የዛሬ አማኞች ጥቅስ እናውቃለን። መጽሐፍ ቅዱስ እናውቃለን። በሕይወት ግን እግዚአብሔርን እናውቅ ይሆን?

እግዚአብሔርን የሚያውቁ ዶክትሪን በተግባር ይኖራሉ። ለምንድን ነው ኖርማል (የተለመደ/ተራ) የሆንነው? በዩቱብ ሳይ አንድ ኦፕራን የጨበጠው ሰውዬ እንኳ አልቅሶ አላቆም ብሏል። ኢየሱስን ያየና የነካ ኖርማል አይሆንም። ስላልበራልን መሰለኝ በእርሱ የማንደነቀው። እርሱን ስናውቅ እንደነቃለን። በተራ ነገር መደነቅ እናቆማለን።

2)ተስፋን (ርስትን) ማወቅ✍️ የሚያሻግረው ጸሎት ተስፋን እንድናውቅ ይረዳል።

ሰው ዛሬ ለእግዚአብሔር የሚኖረው ወደፊት ስለሚኖረው ተስፋ ያየ ነው። ኤፌሶን 1:18 "እንዲሁም በእርሱ የተጠራችሁለት ተስፋ፣ ይህም በቅዱሳኑ ዘንድ ያለውን ክቡር የሆነውን የርስቱን ባለጠግነት ምን እንደሆነ ታውቁ ዘንድ የልባችሁ ዐይኖች እንዲበሩ" (አመት)።
የልብ ዓይን ሲበራ፦
👉ርስት
👉ክብር
👉ባለጠግነት
የጥበብ እና የመገለጥ መንፈስ ሲመጣ ተዓምር ነው። ተዓምር ሲፈጸም የተትረፈረፈ ርስት ይታወቃል።

ኤፌሶን 1-3 ምን እንደሆንን ብቻ ሳይሆን ወደፊት ምን እንደምንሆንም ይናገራል። እግዚአብሔር እሥራኤልን መረጠ። ባሪያ ሆኑ፤ በበጉ ደም ከለላ በሙሴ አማካኝነት ነጻ አወጣቸው። ርስትን ሰጣቸው። ይኸ ከምን ጋር ይገናኛል? ይኸ የእኛ ታሪክ ነው። ዓለም ሳይፈጠር በፊት መረጠን፥ አጸደቀን።

የሆነልን ነገር ልክ የእሥራኤል ሕዝብ ዓይነት ነው። እኛም እንደ እነርሱ ዓይነት ሰዎች ነን። እነርሱ የተጣበቁት ከምድራዊ ጋር ነው። ስለ ኑሮ መሻሻል፥ ሎተሪ፥ ኑሮ፥ ምግብ፥ ቤት፥ ካሬ መሬት፥ መኪና፥ ጋር ልባችን ተጣብቋል። ነገርግን የተባረክነው በሰማይ ነው፤ በረከቱ ዘላለማዊ ነው። ተስፋችን እግዚአብሔር ነው፤ በሰማይ ነው። መቼም የማላፍረው ዶክትሪን ቢኖር ስለ ሰማይ ርስት ነው። ይህችን መሬት ተስፋዬ እንኳን አንቺ አልሆንሽም እላታለሁ። ገና ስለ ሰማይ እሰብካለሁ።

ስለ ሰማይ ርስት ስሰብክ አብዝቼ የምጠቀመው ተረት አለ። "ላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም የማይ"። ሰላሟን፥ ዕረፍቷን፥ ደስታዋን፥ ርካታዋን፥ ...አይቻለሁ፤ ቀምሻለሁ።

ቁ14 የርስታችን መያዣ? ይላል። መያዣ ቀብድ ነው። የርስታችን ቀብድ ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ ማህም ታተምን። ቀብድ ምን? ዓይነቱ አንድ ሆኖ ብዛቱ ያነሰ ማለት ነው። ወደ ፊት የምናየው መጠን ዓየን ያላየው ጆሮ ያልሰማው ነው...። በሰማይ ሰላም፥ ደስታ፥ በረከት፥ ተዘጋጅቷል። አሁን ግን በምድር እነዚህን ቀምሷል፤ ቀብድ ወስዷል። 100 ሚሊዮን ብር ቦታ የገዛ ሰው ቀብድ ከሰጠ እንደተሸጠ ይቆጠራል።

በትልቅ ከተማ ኖራችሁ ገጠር ስትሄዱ የምትንቁት ካያችሁት ጋር ሲነጻጸር አንሶ ስለተገኘ ነው። በከተማ ያያችሁት የተሻለ ነው። አዲስ አበባ የኖረው ሰው ሶዶ ሲመጣ ትላልቅ ፍቅ አይቶ መጥቶ ሶዶን ይንቃል። መንገዱ ጠበበ፥ ቤቶች አነሱ፥ ...ይላል። ከውጭ አገር የመጣው ዲያስፖራው ደግሞ አዲስ አበባ መጥቶ ይንቃል። የሰማዩን ርስት ያየ ሰው የምድሩን ይንቃል። ርስቱን ያየ ሰው አሁን የሚያየውን ይንቃል። ሙሴ ብድራቱን ትኩር አድርጎ ስለተመለከተ ዙፋኑን፥ ግብጽን፥ ገንዘቡን፥ ክብሩን ናቀው። ትልቅን ይዞ መናቅና ትንሽ ይዞ መናቅ ይለያያል።

ከኢየሱስ ጋር በመገለጥ ተራራ ሙሴ አብሮ መገለጡ ከእርሱ ጋር መከራን ብንቀበል ከእርሱ ጋር አብረን እንከብራለን የሚለውን ቃል ተፈጻሚነት ያመለክታል።

ሮሜ 8፥18 "ለእኛም ይገለጥ ዘንድ ካለው ክብር ጋር ቢመዛዘን የአሁኑ ዘመን ሥቃይ ምንም እንዳይደለ አስባለሁ።" ክፍሉ እኛ ገዢ፥ ሀብታም፥ ባለሥልጣን መሆናችንን የሚናገር አይደለም። እንዲህ የሚተረጉሙትን ጳውሎስ ቢያገኛቸው ይቀጣቸዋል። ክፍሉ ይልቁንስ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጥና መዳናችን ሲፈጸም በትንሣኤ አካል ስንነሳ እግዚአብሔርን የምንወርሰው ጊዜ ፍጥረት ይናፍቃል የሚል ትርጉም አለው።

ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን!❤

ማርቆስ ባሣ ግንቦት 01 2018 ዓ.ም ወላይታ ሶዶ ስቴዲየም አጥቢያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን።

ዶክተር ማሙሻ (09_05_2026 እአአ) ቅዳሜ ከሰዓት ፕሮግራም ። 👉ዋና ስሜ ማሙሻ ነው። በጊዜው 11ኛ ክፍል ጌታን አገኘሁ። ጌታን ስትቀበሉ ስማችሁ በሰማይ ተመዝግቧል የሚል ስለሰማሁ በጌ...
10/05/2026

ዶክተር ማሙሻ (09_05_2026 እአአ) ቅዳሜ ከሰዓት ፕሮግራም ። 👉

ዋና ስሜ ማሙሻ ነው። በጊዜው 11ኛ ክፍል ጌታን አገኘሁ። ጌታን ስትቀበሉ ስማችሁ በሰማይ ተመዝግቧል የሚል ስለሰማሁ በጌታ ስሆን ደግሞ የተመዘገበው ስሜ ከተቀየረ እንዳይጠፋ ሰጋሁና ስሜ ሳይቀየር ቀሬ። ለአገልግሎት ስንለይ ወንጌላዊ ሆንኩ። ኮንፈረንስ ሲዘጋጅ በዳቦ ስሜ እንዲቀየር ተደረገ። ማታ ተጨንቄ አደርኩና የድሮ ስሜ ይመለስልኝ ብዬ አልኩ። በማሙሻ ቀጠለ።

የኮንፈረንሱ ዋና ጥቅስ ቆለ 1፥28 መሆኑ ከትምህርቴ ጋር ተገናኘ። ጳውሎስ ብዙ ሰው ሳይሆን የበሰለ ሰው ለእግዚአብሔር ለማስረከብ ዓላማው ነው። የዛሬዋ ቤተክርስቲያን የቆሮንቶስን ቤተክርስቲያን ትመስላለች። የገባቸው ይመስላሉ ግን አልገባቸውም። የጸጋ ስጦታ አላቸው፥ ስለ መስቀሉ ይረዳሉ። ውስጣቸው ስትገባ ግን መከፋፈል አለ፤ ልዩነት አለ። ርኩሰት በመካከላቸው አለ። ጣዖታትንም ለማምለክ ይፈልጋሉ። ወንድም ወንድሙን ይከስሳል። የችግሩ ሁሉ ምንጭ ግን በጌታ አለመብሰል ነው። ኖሮ ኖሮ ጥሬ ከመሆን ጌታ ያድነን።

አለመብሰል ያሳፍራል፤ ወደ ጌታ ሄዶ ከማፈር ጌታ ያድነን!

ርዕስ፦ 👉አሻጋሪ ጸሎቶች
ኤፌሶን 1፥15-23፤ 3፥14-21

በኤፌሶን መጽሐፍ ላይ የተመሠረተ ጸሎት እንማራለን። ጳውሎስ ይጸልይላቸዋል። የጸሎቱን ዝርዝርም ይናገራል። ጸሎት ወደ ላይ ከሆነ፥ ለምንድን ነው ወደጎን የሚዘረዝረው? ከሚጸልየው ጸሎት ጋር እንዲተባበሩ፤ አብረው እንዲጸልዩ። የኤፌሶን መልዕክት ጸሎቶች አሻጋሪ ናቸው።

ድልድይ መሻገሪያ ነው። መንገድ ሩቅ ያደርሳል። ድልድይ ግን ቅርብ ሆኖ የማይገናኙትን ያገናኛል። ለምንድን ነው ድልድይ ጸሎት የተባለው? አጠገብ ሆነው የማይገናኙ ነገሮችን ያገናኛል። ምን እና ምን አልገናኝ ያሉት?እምነታቸው እና ኑሮአቸው። በሌላ አባባል የሚያምኑት እና የሚኖሩት። የሚናገረው እና የሚሆነው ካልተገናኘ ፈሪሳዊነት ነው፤ ግብዝነት። ኢየሱስ የሌየላቸው ኀጢአተኞች ጋር አብሮ ይበላል ግን ሥራቸውን ይጸየፋል። እርሱ የኮነናቸው የሚናገሩትን እና የሚኖሩት የተለየ የሆነባቸውን እንጂ የለየላቸውን ኀጢአተኞችን አልኮነነም።

e.g.የሰውየው ድምጽና ምስል በቴሌቪዥን በተለያየ ሰዓት ሲገናኙ አይታችኋል? ትንሽ ጊዜ በኋላ ማየት ትተዋላችሁ፤ ያሰለቻል። የሚኖረውን ሲናገር እና የሚናገረውን ሲኖር ...።

የኤፌሶን መጽሐፍ መግቢያ👉

መጽሐፉ በሁለት ይከፈላል። ሦስቱ ምዕራፎች ዶክትሪን ናቸው። በዚያ አድርጉ የሚል የለም። ይህንን እግዚአብሔር አደረገ የሚል። እምነት ወይም ትምህርት ነው። ነገርግን ከምዕራፍ አራት እስከ መጨረሻ በጥሪው መሠረት ነሩ፤ ተመላለሱ የሚል ነው። ተግባራዊ ክርስትና።

ክርስትና አድርግ ብሎ አይጀምርም፤ የተሠራውን በመናገር እንጂ። ጽድቅ በእምነት ይገኛል። የመጀመሪያው ምዕራፍ ከቁጥር 3 ጀምሮ እስከ 14 ድረስ በአንድ ትንፋሽ ተናገረ። እያንዳንዱን ነገር በክርስቶስ ተደረገ ይላል።

እግዚአብሔር መረጠው አብርሃምን። የምርጫ አምላክ የተባረከ ይሁን። ዓለም ሳይፈጠር በፊት። በነገረመለኮት ዘንድ ጉንጭ አልፋ ክርክር አለ፦ "ሰምተን ትራክት አንብበን ነው ወይስ ዓለም ሳይፈጠር በፊት ተመረጥን? ይህ ምላሽ የሌለው የጭንቅላት ጂምናስትክ ነው።

እኔ ወዳጄ ተናግሮ አመንኩ። ወድጄው ወደ ጌታ መጣሁ። ቁ14 እናንተም የመዳናችሁም ወንጌል ሰምታችሁ ... ይላል። ይህ ምርጫ ግን ዓለም ሳይፈጠር ነበር። ይህ የሚያናድድ አይደለም።

አብዛኛው ጊዜ ለዚህ የምርጫ እና ሰው ድርሻ የምጠቀምበት ምሳሌ አለ።✍️

e.g. ልጅቷ ያገባችሁ በኳየር ተዋውቃ ነው። ኳየር ከገቡ ሁለተኛ ዓመት እርሱ ፍቅር ይዞኛል አለ። ከጊዜ በኋላ እርሷም ወደደች። መጥተው ለቤተክርስቲያን አመለከቱ። የሠርጋቸው ቀን ማታ ሲናገሩ "አንቺ መቼ አቀወቅሽኝ?" አላት። ኳየር በገባ ሳምንት። እርሷም "አንተስ?" ስትል "ያኔ ልጅ ሆኘ። ተከትዬ አንችን ፍለጋ ኳየር ገባሁ" ሲል ለምን? ትላለች። ከመገረም ውጭ!

ሳልወድ የወደድከኝ ሳልመርጥ የመረጥከኝ...። እንደ ክርስቲያን የተባረከ አለ ወይ? ጌታ ሲመርጠን ከነቆሻሻችን አልተቀበለም። በደሙ አጠበን። ርስትን ተቀበልን።

ርስታችን ምንድን ነው? እግዚአብሔር ራሱ ነው። ሥፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ ማለት ምን? በ6 ቀናት ዓለምን ሠርቶ ከጨረሰ 2ሺ ዓመት የሚሠራው ቤት ምን ዓይነት ነው?

በኤፌሶን መጀመሪያ ምዕራፍ 11 ቁጥሮች ላይ በእያንዳንዱ ላይ "በክርስቶስ" ይላል፤ ቁጠሩ። ተባርከሃል፥ ርስት ተቀብላሃል፥ ኀጢአትህ ተሰርዮልሃል ይላል። ክርስትና ሕግን በመጠበቅ አይጀመርም። እግዚአብሔር በነፃ ያለ ሥራ አከበረን፤ ባረከን።

ክርስትና እንደ ደመወዝ አይደለም። ሁላችንም ቆሻሾች ነበርን። በረከትን ወይም ርስስን ተንበርክኮ መውሰድ እንጂ መዝናናት የለም። አንዳንድ ሃይማኖት ድርጅቶች ሠርቼ እጸድቃለሁ ሲሉ ሌሎች ደግሞ ሥራ አያስፈልግም ይላሉ።

ሐዋርያው በሁለቱ ክፍሎች ስለ አራት ነገሮች ይጸልያል።
👉እርሱን የበለጠ እንዲያውቁ።
👉ተስፋውን እንዲያውቁ (ርስት)።
👉ኃይሉን እንዲያውቁ
👉እንዲጠነክሩ ምዕራፍ ሦስት፤ ቆለስያስ 1፥28ን እንዲሆኑ።

መኖር እግዚአብሔርን ያስከብራል። መልካሙን ሥራችሁን ሲል ጴጥሮስ በመልዕክቱ እናንተን በሚያሙት ነገር ...ይላል።

✍️Markos Bassa

ክፍል ሁለት ይቀጥላል።

በዳሞት ሶሬ አጥቢያዎች ሕብረት ለግል መዘምራን፤ ለሙዚቀኞች እና ለድምፅ ማጉያ ባለሙያዎች ሥልጠና በቀን 28/8/18 ዓ/ም የተሰጠ ስሆን ለዚህም አገልግሎት አስተባባሪዎችም ተመርጠዋል። እግዚ...
08/05/2026

በዳሞት ሶሬ አጥቢያዎች ሕብረት ለግል መዘምራን፤ ለሙዚቀኞች እና ለድምፅ ማጉያ ባለሙያዎች ሥልጠና በቀን 28/8/18 ዓ/ም የተሰጠ ስሆን ለዚህም አገልግሎት አስተባባሪዎችም ተመርጠዋል። እግዚአብሔር በሥራ ላይ ነውና እናመሰግነዋለን።

Address

Gununo
S**o
OK

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጉኑኖ ከተማ ስታዲየም KHC ቤቴል መዘመራን/Gununo stadium khc Bethel singers/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share