Maranatha International Gospel Outreach Ministry Bible School

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • Maranatha International Gospel Outreach Ministry Bible School

Maranatha International Gospel Outreach Ministry Bible School በስልክ ለማግኘት +2519664499

በቴሌግራም ለመማር +251941629673

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000346050512 My name is missionary dawit bonga wogasso from ethiopian

30/05/2026

ለመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ!!

ሰላም ለእናንተ ይሁን እያልን ጌታ ኢየሱስ በዚህች ምድር በአካል ወደ ሰዎች ወርደው በሚያስተምርበት ጊዜ አይሁዳውያን አለማመናቸውንና ቃሉን አለመቀበላቸውን አይተውና ተረድተው እንዲህ አላቸው፤ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ። ዮሐ 8፥31 አላቸው።

እኛም ደግሞ በዘመናችን በኢየሱስና ሕይወትም መንፈስም በሆነው በቃሉ ከኖረንና መኖር ከቻልን ለእኛም በሕይወት ላለን የእግዚአብሔር ቃል ሕይወትም፤ ደስታና ሰላምም፤ መታዘዝምና የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችን የሚገልጽ እውነታችን ነው።

በአገልግሎቱ የረዥም እድሜ ባለቤትና ለብዙ አገልጋዮች ከጌታ በታች ለአገልግሎታቸው በር የሆነው፥ በአገራችን በኢትዮጵያና ከኢትዮጵያም ውጭ በደቡብ አፍሪካ፥ በአሜሪካን፥ በእስያና በአውሮፓ አገራት ላይ የመዳን ወንጌልን በማሰራጨት፥ ደቀመዛሙርትን በማፍራት፥ ቤተክርስቲያንን በመትከል፥ ድሆችን በመረዳትና ከአገር ውስጥ ሚሶናውያን ጀምሮ እስከ ድንበር ዘለል ሚሶናውያን በማሰልጠንና በመላክ፥ ከመሠረታዊ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት እስከ ዶክትሬት ድግሪን በማስተማር የሚታወቀው Maranatha International Gospel Outreach Ministry Bible School ዛሬም የተመሠረተበትን ዓላማ ሳይረሳ ሥራውን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ከወትሮው ይልቅ በጽናት እየሰራ ይገኛል።

እናንተም ደግሞ መሠረታችሁ የእግዚአብሔር ቃልና የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሙላትና ምሪት የሆነበትን እውነተኛ የአማኝ ሕይወትን ለመኖርና በእግዚአብሔር ቃል የተመሠረተውን አገልግሎት ለማገልገል ከፈለጋችሁ በጸሎት ወደ Maranatha International Gospel Outreach Ministry School Of Christ Bible College ብቻ ኑ እንላለን።

በዚህ መግለጫ መሠረት በትምህርት ቤታችን ለመማር የሚትፈልጉ አዳዲስና ነባር ተማሪዎች የተሻሻለውንና አዲሱን አለም አቀፍ የሥነ መለኮት ሕጌ ደንብ መሠረት ከዚህ በታች ያለውን መስፈርት አሟልታችሁ ዛሬውኑ ትምህርቱን መጀመር ትችላላችሁ።

1. ሙሉ ስም ከእነ አያት፥ ጾታ እና እድሜ።

2. አንድ ጉርድ ፎቶ ለሰርተፍኬት የሚሆንና በአግባብ ለሰዎች የሚታይ።

3. ከ8ኛ ጀምሮ ያለውን የትምህርት ማስረጃ በሙሉ ኮፍ መላኪ ሲሆን መረጃውን ወደ እኛ ስትልኩ፥ ለድፕሎሚ ከ10,12 መረጃ እና በላይ፥ ለድግሪ ከድፕሎሚ መረጃ እና በላይ፥ ለማስተርስ የአንደኛ ድግሪ መረጃ እና በላይ፥ ለዶክትሬት የማስተርስ መረጃ እና በላይ ያለው መረጃ መላኪ አለባችሁ።

4. ለመማር የሚፈልጉትን ትምህርት ከሰርተፊኬት ጀምሮ እስከ ዶክትሬት ያለውን ትምህርት ኮርስ መምረጥ አለባችሁ ።

ይህንን ከጨረሳችሁ፦

4.1 የሚዝገባ ብር በኢትዮጵያ ለድፕሎሚና ለድግሪ (350) ለማስተርስና ለዶክትሬት (500) ገቢ በኢትዮጵያ ወኪል አስተባባሪው አካውንት ገቢ ማድረግ አለባችሁ።

4.2 በመደበኛነት ቴሌግራምን የሚትጠቀሙበት ስልክ እና የቀበሌ ነዋሪነት መታወቂያ ወይም የዲጂታል መታወቂያ ኮፓ መላኪ አለባችሁ።

4.3 የመመዝገቢያውንና የትምህርቱን የኮርስ ክፍያ (500) እና የምዝገባ (350) ከዚህ በታች ባለው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት 1000346050512 ወይም በደቡብ ግሎባል ባንክ አካውንት ቁጥር 2311106080691 ወይም ብርሃን ባንክ 1031545963629 በአስተባባሪው አካውንት ማስገባት አለባችሁ።

ማሳሰቢያ ፦ ከዚህ በላይ በተቀመጠው መመሪያ መስፈርትን የሚያሟሉ ተማሪዎችን ሁልጊዜ እንቀበላለን፥ ሁልጊዜ እናስተምራለን!!

✔ለምዝገባ በመደወል ☞+251925664499 ይደውሉ።

✔ለምዝገባ በቴሌግራም ☞251941629673 ይጻፉ።

✔እኛ የሚንሰጣቸው ማንኛውም አይነት ትምህርቶች በቴሌግራም ቻናል ብቻ መሆኑን ለአዳዲስ ተማሪዎች እንገልጻለን።

✔ልዮ ልዩ ትምህርቶችንና አጫጭር ኮርሶችን በማዘጋጀት ከ8ኛ-10ኛ ክፍል ጀምሮ ተማሪዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ በድምጽና ለመረዳት በሚችሉበት ቀለል ባለ አገላለጽ ያዘጋጀናቸውን ጹሑፎችን በማድረስ በደረሱበት ደረጃቸው መሠረት እናስተምራለን፥ ዓላማችን እውነተኛ ደቀመዛሙርትን በእግዚአብሔር ቃል መቅረጽ ነው። ማቴ 28:16-20

የክፍያ ሁነታ ለትምህርት ቤት

1. ለሰርተፊኬት ተማሪዎች 12 ኮርስ ከክፍያ ነጻ ነ።

2. ለድፕሎሚ ተማሪዎች በአንድ በኮርስ 500 ብር ነው፤ ለድፕሎሚ ተማሪዎች የሚሰጡ ኮርሶች 38 ናቸው።

3. ለመጀመሪያ ድግሪ ተማሪዎች በአንድ በኮርስ 600 ብር ነው፤ የኮርስ ብዛት 36 ነው።

4. ለሁለተኛ ድግሪ ተማሪዎች በአንድ በኮርስ 800 ብር ነው፤ የኮርስ ብዛት 36 ነው።

5. ለዶክትሬት ተማሪዎች በአንድ በኮርስ 800 ብር ነው፤ የኮርስ ብዛት 36 ነው።

ማሳሰቢያ ለሁሉም ተማሪዎች የምዝገባ ብር 350 መሆኑን እንዳትረሱ።

አድራሻ፦ ዋና ቢሮ ሚኖሰታ ዩኤስ ኤ፤ አዲስ አበባ, ወላይታ ሶዶ, አረካ፤ አዋሳ እና አርባምንጭ።

ለመመዝገብና ለመማር ዘውትር 0941629673

የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ። በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ። በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ በጸጋው በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ። ቆላ 3:16 አሜን። እናመሰግናለን!!

0941629673

https://t.me/maranathaministrybibleschool

[email protected]

30/05/2026

Welcome to Maranatha international Bible School.

Student Name= Yohannes Urmale Kalisho

Class Level= Higher Certificate In Christian Education

Student Id= migombs 2070/2026

Area/ Country = Southern Ethiopia/Konso

ተመዝግባችሁ ትምህርቱን በOnline ለመጀመሪያ 0941629673 በቴሌግራም ያናግሩን።

30/05/2026

Welcome to Maranatha international Bible School.

Student Name= Sagoya Arkale Ayele

Class Level= Bachelor Degree In Theology

Student Id= migombs 2071/2026

Area/ Country = Southern Ethiopia/Konso

ተመዝግባችሁ ትምህርቱን በOnline ለመጀመሪያ 0941629673 በቴሌግራም ያናግሩን።

26/05/2026

ዛሬ እለተ ማክሰኞ ታላቅ የጸጋ ወንጌል ስርጭት በአረካ ከተማና አከባቢዎች ላይ እየተደረገ ነው።

ጸሎታችሁ አይለየን።

26/05/2026

የቀደምት እውነተኛ ነቢያቶችና መልእክታቸው።

የእግዚአብሔር ሰላምና ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን ቅዱሳን የእግዚአብሔር ቤተሰቦች። ዛሬ በዚህ ትምህርት የቀደምት ነቢያቶች ያስተላለፉት መልእክት በዚያን ጊዜ ለነበረው ሕዝብ ምን የሚመልስ ነበር፤ አጠቃላይ የአገልግሎታቸው ይዘት እንደት ነበር፤ የነቢያት ሕይወት በዘመናቸው በሚያገለግሉበት ማሕበር ዘንድ እንደት ነበር፤ የነቢያት ሹመት ከሰው ነበር፤ ራሱን በራሱ ነበር ወይስ ከእግዚአብሔር ነበር፤ ከመጽሐፍቶቹ የሚናገኘው እውነት ለእኛ ምን ይሁን የሚለውን ጭምር በየዘመናቱ ያገለገሉ ነቢያትን ማየት በዚህ ትምህርት እንጀምራለን።

ማራናታ አለም አቀፍ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት፥ 0941629673 ወይም 0916832587። በቴሌግራም መማርን ጀምሩ።

አሁን ባለንበት በአዲስ ኪዳን ዘመን ነቢያትንና የትንቢት መጻሕፍትን አንዳዳ ሰዎች በተሳሳተ መንገድ ይተረጐማሉ። ለዚህ ዋናው ምክንያት በነቢዩ ማንነትና በሚሠራው ሥራ ረገድ የተምታታ ነገር ስላለ ነው። ስለ ነቢዩና ስለሚናገረው ትንቢት በምናስብበት ጊዜ በሁላችን አእምሮ የሚቀረጹ የተለያዩ ምስሎች አሉ። ብዙውን ጊዜ ነቢይ ወደፊት ስለሚሆነው ነገር የማመልከት ችሎታ ያለው ሰው የሆነ ይመስለናል፤ የብሉይና የአዲስ ኪዳን ነቢያት ዋና ተግባር ይህ የሆነ ይመስለናል። ይህም ነገር ሰዎችን ዛሬ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነቢያት አሉን? የሚል ጥያቄ አሳድሮባቸዋል፤ ብዙዎችንም እንዲደነቁ አድርጓቸዋል። በአዲስ ኪዳን ውስጥ መንፈስ ቅዱስ ለሰዎች የትንቢትን ስጦታ እንደሚሰጥ እናነባለን (1ኛ ቆሮ. 12፡28፤ ኤፌሶን 4፡11 ተመልከት)።

ይህ ስጦታ ለቤተ ክርስቲያን ከተሰጡ እጅግ አስፈላጊ ስጦታዎች አንዱ ሲሆን፥ ቤተ ክርስቲያን ከተመሠረተችባቸው መሠረቶች አንዱ ክፍል ነው። በአሁኑ ዘመን ነቢይ የሚመስሉ ሰዎች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቢኖሩም፥ ነቢይ ማን እንደሆነና ምን እንደሚሠራ ስላለን ግንዛቤ ከፍተኛ ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል። በተጨማሪ በዚህ ዘመን ያሉትን ነቢያት ሥልጣን በብሉይ ኪዳን ዘመን የእግዚአብሔርን ቃል ያለ ምንም ስሕተት ይናገሩ ከነበሩ ሰዎች ጋር እንዳናስተካክል ልንጠነቀቅ ይገባል። እንዲያውም አንዳንዶች የአዲስ ኪዳን ዘመን ነቢያት በብሉይ ኪዳን ዘመን እንደነበሩ ነቢያት መለኮታዊ የመንፈስ ቅዱስ ምሪት እንደነበራቸው ተደርገው እንዳልታዩ ይናገራሉ።

ብዙ ጊዜ የነቢያት ሥራ ስለ ወደፊቱ ጉዳይ መናገር የሆነ ይመስለናል፤ ስለዚህ የትንቢት መጻሕፍት በምናጠናበት ጊዜ፥ ስለ ወደፊቱ የተነገረ ሰፊና ጥልቅ አሳብ እንፈልጋለን። በአመዛኙ ክርስቲያኖች የትንቢትን መጻሕፍት በሚመለከቱበት ጊዜ፥ የሚያነቡትን ነገር የኢየሱስን ምጽአት ወይም የዘመናት መጨረሻን በሚያመለክት መልኩ የሚተረጉሙባቸውን መንገዶች ይፈልጋሉ። እነዚህን ጉዳዮች የሚያመለክቱ ትንቢቶች ቢኖሩም እንኳ የብሉይ ኪዳን ትንቢቶች በአብዛኛው የሚናገሩት ስለ ኢየሱስ ወይም ስለ እኛ የወደፊት ሁኔታ አይደለም። አንዳንድ ምሁራን እንደሚገምቱት፥ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚናገሩ የብሉይ ኪዳን ትንቢቶች ከ2 በመቶ አይበልጡም። ኢየሱስ ከተወለደ በኋላ ስላሉት ጊዜያት የሚናገሩት ትንቢቶች ከ5 በመቶ በታች ናቸው። ከ1 በመቶ ያነሱት ደግሞ ዛሬ እኛም ብንሆን ገና ወደፊት ይፈጸማሉ የምንላቸው ናቸው። የብሉይ ኪዳን ነቢያት ስለ ወደፊቱ ሁኔታ አስታውቀዋል፤ ነገር ግን ይህ ብዙ ጊዜ ለእስራኤል ልጆችና በአካባቢያቸው ለነበሩት መንግሥታት የቅርብ ጊዜ አመልካች መልእክት ነበር፤ ስለዚህ ከእነዚህ የትንቢት መጻሕፍት የምናገኛቸው አብዛኛዎቹ ትንቢቶች በብሉይ ኪዳን ዘመን ከነበረችው እስራኤል ጋር የሚዛመዱ እንጂ ስለ እኛ ወደፊት ሁኔታ የሚናገሩ አይደሉም።

ነቢይ ምንድን ነው? በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፥ ነቢይ የእግዚአብሔርን መልእክት ለሰዎች የሚያስተላልፍ ሰው ነው። አብዛኛውን ጊዜ መልእክቱ ያተኩረው በሕዝቡ ወቅታዊ ፍላጎት ላይ ነበር። ነቢያት የእግዚአብሔር መልእክተኞች ሆነው እስራኤል ከእግዚአብሔር ጋር የገቡትን ቃል ኪዳን መታዘዝ እንዳለባቸው፥ ካልታዘዙ ግን ያለመታዘዛቸውን ውጤቶች የሚቀበሉ መሆናቸውን የሚያሳስቡ ነበሩ። ነቢያት ሕዝቡ ንስሐ እንዲገቡና ለቃል ኪዳኑ እንዲታዘዙ ለማድረግ የሚጥሩ የእግዚአብሔር አፈ-ቀላጤዎች ነበሩ። በቃል ኪዳኑ የተመለከተው ፍርድ እንደሚመጣባቸው የሚያስጠነቅቁ ነበሩ፤ ወይም ደግሞ የእግዚአብሔር ልጆች ለቃል ኪዳኑ ታዛዥ ሆነው በሚኖሩበት ጊዜ ስለሚቀበሉት በረከት ይናገሩ ነበር። የነቢያት አገልግሎት ከእግዚአብሔር ርቆ የሄደው ሕዝብ ወደ እግዚአብሔር እንዲመለስ ማነቃቃትን አጥብቆ የሚሻ ነበር። ነቢያት ወደዚህ አገልግሎታቸው የመጡት በገዛ ፈቃዳቸው ሳይሆን፥ ጥሪውን ከእግዚአብሔር ተቀብለው ነበር (ለምሳሌ፡- ኢሳይያስ 6፤ ሕዝቅኤል 1-3)። ስለዚህ ነቢያት ብዙ ጊዜ የሚናገሩት እግዚአብሔር እንደሚናገር ሆነው የእግዚአብሔርን ድምፅ በመጠቀም ነበር። (እግዚአብሔር ራሱ እንደተናገራቸው እንጂ ነቢዩ እንዳልተናገራቸው የሚመስሉ ትንቢቶች ምን ያህሉ እንደሆኑ አስተውል።)

ማራናታ አለም አቀፍ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት፥ 0941629673 ወይም 0916832587። በቴሌግራም መማርን ጀምሩ።

ነቢያት ስለ ወደፊት ሁኔታዎች የሚናገሩት አልፎ አልፎ ብቻ ነበር። አብዛኛዎቹ ትንቢተቻቸው በእስራኤላውያን ላይ በቅርብ ጊዜ ስለሚሆኑ ነገሮች የሚያመለክቱ ነበሩ፤ ለምሳሌ አብዛኛዎቹ የብሉይ ኪዳን ትንቢቶች እስራኤል በአሦር፥ ይሁዳ ደግሞ በባቢሎን ስለ መደምሰሳቸው ወይም ደግሞ ስለ ሕዝቡ ከምርኮ መመለስ የተነገሩ ነበር። ስለ ኢየሱስ መምጣትና ስለ ዘመኑ ፍጻሜ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የሚናገሩ ጥቂት ትንቢቶች ነበሩ። እነዚህን በረዥም የጊዜ ሂደት ውስጥ የሚፈጸሙ ትንቢቶች በመስጠት ረገድ የእግዚአብሔርና የነቢያቱ መሠረታዊ ፍላጎት የእስራኤልን ሕዝብ ማስተማር ነበር። እግዚአብሔር በታሪክና በእነርሱ ሕይወት ውስጥ ያለውን የበላይ ተቈጣጣሪነት እንዲመለከቱ ይፈልግ ነበር። ስለሚመጣው ፍርድ ተረድተው እንዲጠነቀቁና በመጨረሻም ስለሚያገኙት በረከት በማሰብ እንዲነቃቁ ይፈልግ ነበር።

ትንቢቶች ወደፊት ስለሚሆኑ ነገሮች ዝርዝር መግለጫዎችን ይሰጣሉ ማለት አይደለም፤ ነገር ግን አሁን እግዚአብሔርን በሚያስከብር መንገድ ስለ መኖር የሚያስተምሩን ናቸው። ስለ ወደፊት ሁኔታዎች ለማወቅ ያለንን ጕጕት ለማርካት የተሰጡ አይደሉም። አንዳንድ ክርስቲያኖች በትንቢቶች አተረጓጐም ረገድ ግምታዊ አስተያየት በመስጠት፥ ኢየሱስ በዚህ ጊዜ መመለስ አለበት፤ ወይም ሐሰተኛው ክርስቶስ ይህ ወይም ያ ሰው ነው ማለታቸው ፍጹም ስሕተት ነው። ይህ ስለ ትንቢት የተዛባ ትርጕም መስጠት ነው።

እግዚአብሔር ለጥንት ነቢያት መልእክቱን ያስተላለፈው እንዴት ነበር? በአንድ የተወሰነ መንገድ ወይም ዘዴ አልተጠቀመም። ለአንዳንዶች መልእክቱን በሕልም ወይም በራእይ ተናግሯል። (ለምሳሌ፣ ለዳንኤል)። ለሌሎች ደግሞ በጥሞና በነበሩበት ጊዜ እግዚአብሔር የተለያዩ ነገሮችን በማሳየት መልእክቱን አስተላልፏል (ለምሳሌ፣ ለሐዋርያው ዮሐንስ በፍጥሞ ደሴት)። ዳሩ ግን እግዚአብሔር በአብዛኛው የተናገረበት መንገድ «እግዚአብሔር እንዲህ ይላል» በማለት መልእክቱን በእርግጠኛነት እንዲያስተላልፉ ለነቢያቱ በቀጥታ በመናገር ነበር ( ለምሳሌ፣ 2ኛ ነገሥት 20፡4-6)።

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የምናያቸው ያተኮሩት የወደፊቱን ሁኔታ በሚቈጣጠርና መልእክቱን ለነቢዩ በሚሰጠው በእግዚአብሔር ላይ እንጂ፥ በነቢዩ ላይ አይደለም። መልእክቱን የሚያዘጋጁት ነቢያት አልነበሩም፤ መልእክቱ የእግዚአብሔር ሲሆን፥ ነቢያት እግዚአብሔር መልእክቱን ለሕዝቡ የሚያስተላልፍባቸው መሣሪያዎች ብቻ ነበሩ። እነዚህ ነቢያት የእግዚአብሔርን አመለካከት፥ ለተለያዩ ጉዳዮች የሚሰጣቸውን ምላሾች አሳቡንና ዕቅዱን ለእነርሱ በገለጠላቸው መንገድ ያቀርቡ ነበር፡፡ ስለዚህ የሚኮሩበትና የሚታበዩበት አንዳችም ምክንያት አልነበራቸውም። በብሉይ ኪዳን ውስጥ፥ የነቢያት ሥራ እግዚአብሔር ከእስራኤላውያን ጋር በሲና ተራራ ካደረገው ቃል ኪዳን ጋር በቅርብ የተሳሰረ ነበር። አብዛኛው ትምህርታቸው (መልእክታቸው) በይዘት አዲስ አልነበረም። ይልቁንም እግዚአብሔር በቃል ኪዳኑ የሰጣቸውን የእርግማንና የበረከት አይቀሬነት በተለየ መንገድ አጠናክረው የሚያውጁ ነበሩ።

እነዚህ ነቢያት መልእክታቸውን የተቀበሉት በቀጥታ ከእግዚአብሔር ነበር። ሆኖም ከተናገሯቸው ነገሮች መካከል አብዛኛዎቹ በሙሴ ሕግ፥ በተለይም ባለመታዘዝ ስለሚመጣው መርገምና በመታዘዝ ስለሚገኝ በረከት በሚናገረው በቃል ኪዳኑ ክፍል ውስጥ የሚገኙ ነበሩ። በሕግ መጻሕፍት ውስጥ በሚገኘው ቃል ኪዳኑ እግዚአብሔር ለሚታዘዙት ሁሉ በረከትን እንደሚሰጥ ቃል ገብቷል። እነዚህ ሰረከቶች ሕይወት፥ ጤንነት፥ ብልጽግና፥ በእርሻ ፍሬያማ መሆን፥ የደኅንነት ዋስትናና በአሕዛብ መካከል የክብር ስፍራ ማግኘትን የሚጨምሩ ነበሩ። እስራኤል እግዚአብሔርን በታዘዘች ቍጥር ይህ ነገር ሲፈጸም እንመለከታለን (ለምሳሌ፣ የዳዊትና የሰሎሞን ዘመነ መንግሥት)። በፍርድ መልክ የተደነገጉት መርገሞች በሕዝቡ ሁሉ ላይ የሚደርሱ ነበሩ። ያለመታዘዝ ምትን፥ በሽታን፥ ድርቅን፥ አደጋን፥ ጥፋትን፥ በጠላቶች ድል መመታትን፥ በምርኮ መጋዝንና ውርደትን ያስከትል ነበር። የነቢያትን መልእክት በጥንቃቄ በምንመረምርበት ወቅት ከመልእክታቸው አብዛኛው ክፍል በእነዚህ በረከቶች ወይም መርገሞች ላይ የሚያተኩር እንደነበር ለማየት እንችላለን። የነቢያት መልእክቶች በሕግ ውስጥ የሚገኙት መርገሞች በእስራኤል ሕዝብ ላይ ሊደርሱ እንደተቃረቡ ያመለክቱ ነበር። በቃል ኪዳኑ ውስጥ የተሰጡት በረከቶች በሙላት የሚፈጸሙበትን የወደፊቱንም ጊዜ አመልክተዋል። በ586 ዓ.ዓ. የሆነው ምርኮ እስከተፈጸመበት ጊዜ ድረስ የአብዛኛዎቹ ነቢያት መልእክቶች ስለ ጥፋት የሚናገሩ ነበሩ። ከምርኮ በኋላ የነበሩት አብዛኛው የነቢያት መልእክቶች ደግሞ በወደፊት በረከቶች ላይ ያተኮሩ የማበረታቻ መልእክቶች ነበሩ።

ማራናታ አለም አቀፍ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት፥ 0941629673 ወይም 0916832587። በቴሌግራም መማርን ጀምሩ።

ብዙ ጊዜ እግዚአብሔር ነቢያትን የሚጠራው ብሔራዊ ችግር በሚኖርበት ጊዜ ይመስላል። አንዳንድ ነቢያት ያገለገሉት የአንበጣ መቅሠፍት ከተፈጸመ በኋላ ነበር (ለምሳሌ፡- ኢዩኤል)። አብዛኛዎቹ ነቢያት ያገለግሉ የነበረው እንደ አሦርና ባቢሎን የመሳሰሉ የአሕዛብ መንግሥታት እስራኤልን ለመደምሰስ ጥቃት በፈጸሙበት ጊዜ ነበር። ነቢያት የእግዚአብሔርን ቃል በግልጽ ሕዝቡን ለማስተማር የተነሡትና ሕዝቡ በዚህ ፍርድ ሥር የወደቀው ለምን እንደሆነ ለማስገንዘብ ያገለገሉት በእስራኤል ሕዝብ ታሪክ ውስጥ የጨለማ ዘመን በመባል በሚታወቀውና መንግሥትዋ ለሁለት በተከፈለበት ወቅት ነበር። በእስራኤል ሕዝብ ታሪክ በአጠቃላይ የተለያዩ ተግባራት ያሉአቸው የተለያዩ ነቢያት ነበሩ። እንዲያውም የነቢያት አገልግሉት በጊዜ ብዛት የተለወጠ ይመስላል።

1. ከነገሥታት ዘመን በፊት የነበሩ ነቢያት፡- ከሳኦልና ከዳዊት ዘመን በፊት የነበሩት አብዛኛዎቹ ነቢያት የእግዚአብሔርን መልእክት ለሕዝቡ የሚያደርሱ፥ ሕዝቡን በችግር ጊዜ የሚመሩና በእግዚአብሔር የተመረጡ መሪዎች ነበሩ። በዚህ ጊዜ ስለ ወደፊት ሁኔታዎች ለተነገሩ መልእክቶች የተሰጠው ትኩረት ዝቅተኛ ነበር። ይልቁንም ትኩረቱ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በመምራት ላይ ነበር። እንደ እነዚህ ያሉ ነቢያት ሙሴ (ዘዳግም 34፡10-11) እና ዲቦራ (መሳፍንት 4፡4) ነበሩ።

2. በመጀመሪያዎቹ የእስራኤል ነገሥታት ዘመን ማለት የሚጽፉ ነቢያት ከመነሣታቸው በፊት የነበሩ ነቢያት፡- በተባበረችው የእስራኤል ዘመነ መንግሥት ጊዜ ነቢያት የንጉሥ አማካሪዎች ነበሩ። ለነገሥታቱ የእግዚአብሔርን በረከት ወይም ተግሣጽ በመገለጥ የእግዚአብሔር አፍ ሆነው የሚያገለግሉ ነበሩ። አንዳንዶቹ የእስራኤልን ሕዝብ ታሪክ በመመዝገብ ሥራ የተሳተፉ ቢሆንም የራሳቸውን የትንቢት መጽሐፍ አልጻፉም። በአመዛኙ ስለ እነዚህ ነቢያት የምናነብበው ለሕዝብ ከተናገሩት ይልቅ ያደረጉትን ነገር የሚገልጽ ነው። በዳዊት ዘመን የነበረው ነቢዩ ናታን (2ኛ ሳሙኤል 7፡2-5)፥ ኤልያስና ኤልሳዕ ለእንደነዚህ ዓይነት ነቢያት ምሳሌ የሚሆኑ ናቸው።

3. ለሁለት በተከፈለችው የእስራኤል መንግሥት ማብቂያ ላይ የነበሩ ነቢያት፡- በዚያን ጊዜ በርካታ የነበሩ ቢሆንም፥ መጽሐፍ ቅዱስ የትንቢት መልእክቶቻቸውን በጻፉ 16 ነቢያት ላይ አትኩሯል። እነርሱንም በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ እናገኛቸዋለን (ከኢሳይያስ - ሚልክያስ)። እነዚህ ነቢያት አንዳንድ ጊዜ ከነገሥታት ጋር ይሠሩ ነበር። ይሁን እንጂ መልእክታቸው ብዙ ጊዜ ለእስራኤል ወይም ለይሁዳ ሕዝብ የተነገረ ነበር። መልእክታቸው ብዙ ጊዜ በኃጢአት በተበላሸ የእግዚአብሔር ሕዝብ ሕይወት ላይ የቀረበ ተግሣጽ፥ ለጽድቅና ለቅድስና ኑሮ የተደረገ ጥሪ፥ ሊመጣ ስላለው ምርኮ ማስጠንቀቂያና ስለ ወደፊቱ ተሐድሶ የሚናገር ነበር። ትኩረታቸው እግዚአብሔርን ወክለው ለሕዝቡ ባመጡት በእግዚአብሔር ቃል ላይ ስለነበር ስላደረጉት ነገር የምናነበው በጣም ጥቂት ነው።

በዚያን ዘመን ብዙ ነቢያት የነበሩ ቢሆንም፥ ልክ ዛሬ በዘመናችን እንደምናየው በርካታ ሐሰተኛ ነቢያትም ነበሩ። ብዙውን ጊዜ ሐሰተኞች ነቢያትን ከእውነተኞቹ መለየት አስቸጋሪ ነበር። ሁሉም የእግዚአብሔርን መልእክት በሕልምና የእግዚአብሔርን ድምፅ በመስማት እንደተቀበሉ ይናገሩ ነበር። ሁለቱም ወደፊት ስለሚከሠቱ ነገሮች ይናገሩ ነበር፤ ዳሩ ግን ሁሉም ከእግዚአብሔር አልነበሩም (ለምሳሌ፡- ኤርምያስ 14፡14፤ 23፡21)። ነቢያት መልእክታቸውን የሚቀበሉት ከእግዚአብሔር ቢሆንም፥ በጽሑፍ በሚያሰፍሩት ጊዜ የራሳቸውን የአጻጻፍ ስልት እንዲጠቀሙ እግዚአብሔር ፈቅዶላቸዋል፤ ስለዚህ በእያንዳንዱ የነቢያት መጻሕፍት ውስጥ የጸሐፊውን ችሎታና ጥበብ እንመለከታለን። አንዳንዶች እንደተማረ ሰው የሰዋስው አገባብ ጠብቀው ጽፈዋል። ሌሎቹ በሚገባ አለመማራቸውን በሚያሳይ አኳኋን ጥራት በሌለው ሰዋስው ጽፈዋል። እግዚአብሔር ግን መልእክቱን ለማስተላለፍ በሁለቱም ዓይነት ነቢያት ተጠቅሟል።

ትንቢትን ለመተርጐም አስቸጋሪ ከሚያደርጉት ነገሮች አንዱ፣ አብዛኛው የተጻፈው በግጥም መልክ መሆኑ ነው፤ ስለዚህ መተርጐም የሚገባቸው በርካታ ተምሳሌቶችን እናገኛለን። እነዚህ ተምሳሌቶች ነቢያቱ በኖሩበት ዘመን ለነበሩ አንባብያን ግልጽ ቢሆኑም፥ ብዙ ጊዜ ለእኛ ግልጽ አይደሉም። ስለ ትንቢቶች የተለያየ ትርጕም ወደ መስጠት የሚያመራው ምክንያት ይህ ነው።

ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ። ማቴ 22፥29

https://t.me/maranathaministrybibleschool

ማራናታ አለም አቀፍ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት፥ 0941629673 ወይም 0916832587። በቴሌግራም መማርን ጀምሩ።

19/05/2026
03/05/2026

በOnline የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ለመማር በ0941629673

29/04/2026

በዚህ ስልክ በቴሌግራም ጀምሩ 0941629673

የምስጋና መልእክትይህም በሐሳብና በጸሎት፥ በገንዘብ በሚጠቅመን ነገር ሁሉ ለረዱን!!የእግዚአብሔር ሰላምና ጸጋ ይብዛላችሁ እያልን ማራናታ የመዳን ወንጌል ስርጭትና የበጎ አድራጎት ሥራ አገልግ...
18/05/2025

የምስጋና መልእክት

ይህም በሐሳብና በጸሎት፥ በገንዘብ በሚጠቅመን ነገር ሁሉ ለረዱን!!

የእግዚአብሔር ሰላምና ጸጋ ይብዛላችሁ እያልን ማራናታ የመዳን ወንጌል ስርጭትና የበጎ አድራጎት ሥራ አገልግሎት ከዚህ በፊት ከተለያዩ አማኝ ወንድሞችና እህቶች ለወንጌል ስርጭት አገልግሎት የሚሆን ሞንተርበው ለመግዛት በደብዳቤ፥ በአካል፥ ስልክ በመደወል እና ወዘተ መንገድ ገንዘብን፥ጸሎትን በቁሳቁስም ቢሆን እንድያግዙን መጠየቃችን የታወቀ ነው።

ስለዚህ በአገር ውስጥና በውጭ አገር ያላችሁ ሁሉ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ቤታችሁን፥ ሥራችሁን፥ ጤንነታችሁን ሁሉ በወንጌል በረከት ይባርካችሁ እያልን ከእናንተ በሰበሰብነው ወይም በተሰበሰበው ገንዘብ በትናንትናው እለት በቀን 09/09/2017 ዓ.ም ከወላይታ ሶዶ በቀድሞው ስም ማርያም ሰፈር ከሚባለው ቦታ በአስተባባሪዎች አማካኝነት ለወንጌል ስርጭት አገልግሎት ብቻ የሚውል ሞንተርበው ብር በኢትዮጵያ (35000 ሺ) ሳላሳ አምስት ሺህ ብር ገዝተን ማምጣታችን በታላቅ ደስታ ለእናንተ በምስጋና በተሞላ መንፈስ ለመናገር እንሞክራለን።

በመጨረሻም ይህንን አገልግሎት በተለያዩ መንገዶች ማለትም የትራንስፖርት ገንዘብን በመክፈል፥፥ ምሳ በመግዛት፥ ትሸርት በማሳተም፥ ቀዝቃዛ ውኃ በመግዛት ጌታ በረዳችሁ መጠን እርዱን እያልን ስላበረከቱልን ለመልካም አስተዋጽኦ ምድርና ሰማዩን በቃሉ በፈጠረው በእግዚአብሔር ፊት በምስጋና ተሞልተን እርሶዎን እናመሰግናለን!!

ማራናታ የመዳን ወንጌል ስርጭት እና የበጎ አድራጎት ሥራ አገልግሎት!!

የእግዚአብሔር ሰላምና ጸጋ ከሁላችሁም ጋር ይሁን፥ አሜን!!

ለበለጠ መረጃ፦

በሕብረቱ ስልክ +251925664499 ይደውሉልን።

በEmail፦ [email protected]

በፌስቡክ ፦ https://www.facebook.com/profile.php?id=100089863696565

ሕብረቱን ለመረዳት ከፈለጋችሁ

የሕብረቱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት 1000693792472 ነው።

Address

Wolaita S**o
S**o
1234

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Maranatha International Gospel Outreach Ministry Bible School posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share