BEREA Believers የቤሪያ አማኞች

BEREA Believers የቤሪያ አማኞች Evan Bekele Dubago
Belessa No 1 KHC

03/10/2023

የእዉነተኛ ተሐድሶና የእግዚአብሔር ቤት ቅናት እሳት ድምጽ! (ዮሐ 2፡17)
ክፍል 3
በእነዚህ ከላይ በተጠቀሱትና በሌሎችም በእዉነተኛ ቤተክርስቲያን እንቅፋቶች ላይ የመስራትና የመከላከል ኃላፊነት የማነዉ? እኔ እንደሚመስለኝ፤
1) የቤተክርስቲያን መሪዎች፤
2) የመጋቢያንና ወንጌላዊያን፤
3) እግዚአብሔር እድሉን ሰጥቷቸዉ በከፍተኛ ሥነመለኮት ጥናትና ምርምር ያጠኑ፤ የመጽሐፍ ቅዱስ ት/ቤት የቲኦሎጂ መምህራን፤
4) ሌሎችም ለክርስቶስ ቤ/ክ እዉነተኛ ቅናት ያለን ቤቱ የሁላችን ናት የምንል፤
ከላይ በተራ ቁጥር አንድ ላይ የተቀመጣችሁ የቤተክርስቲያን የመጀመሪያ ባለድርሻ አካላት፤ መሪዎች ይህንን በትዉልድ ላይ የተጋረጠዉን ፈተና ለመጋፈጥ እናንተ በር ከፋቾች ናችሁ፤ ቁሳቁስ ማሳመርና ስሜትን ማርካት ብቻ ሳይሆን፤ ያሉንን ለሃዲያ ቀርቶ ለአፍሪካና ለዓለምም የሚሆኑ የሥነ መለኮት ምሁራን እንጠቀማቸዉ።
ሌሎች ሰባኪዎችን ለስብከትና ለማነቃቃት፣ ለአስተዳደር ኃላፊነት፣ ለማስተባበር ብንጠቀማቸዉ፤ ምክንያቱም ማስተማር፣ ማሰልጠንና ማስታጠቅ ለሁሉ አገልጋይ የሚሆን አይደለም።
ያዕ 3፡1 ስለሚል።
ፀጋዉ ይብዛልን፤ አሜን!

ይህን Page follow በማድረግ የወ/ዊ በቀለ ዱባጎን ሌሎችንም መንፈሳዊ ትምህርቶች ይከታተሉ።

25/09/2023

የእዉነተኛ ተሐድሶና የእግዚአብሔር ቤት ቅናት እሳት ድምጽ! (ዮሐ 2፡17)
ክፍል 2
እኛም መሪዎች፣ መጋቢያን፣ ወንጌላዊያን፣ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተማሪዎችና ሌሎችም አገልጋዮች ለእዉነተኛ ተሐድሶና ለዉጥ እንስራ!
የአዲሱ ትዉልድ ጩኸት ለምንድነዉ? ከአባቶቻችን የተረከበዉን ንጹህ ወንጌል ክርስቶስ እስኪመለስ ወይም ሞት እስኪለየን ለሚቀጥለዉ ትዉልድ ጤናማ ቤተክርስቲያን ለማስተላለፍ አይደለምን? ትዉልዱ አሁን እየተጋፈጠ ያለዉ ምንድተዉ?
ነፃነት፣ እድገትና ለዉጥ ያለ ሲመስል ስልጣኔና የተክኖሎጂ ሽግግር ያለ ሲመስል ነገር ግን ትከሻችንን ያጎበጠ ቀንበር፤ ጨለማ የወረረበት ጊዜ ላይ ነዉ ያለነዉ!
ምን ጨለማ አለ? ምን ቀንበር አለ? ለሚለዉ በኔ አመለካከት፤
1) ክፍፍልና ዘረኝነት አደባባይ የወጣበት ጊዜ፤
2) ቤተክርስቲያንን የሚያተራምሱ፣ ጥቅም ዝናና ክብር ማግኛ የግለሰብ አገልግሎቶችና ንግዶች የሐሰት አሰራሮች የበዙበት ጊዜ፤
3) ሙስናና ጉቦ፤ ብልሹ አሰራሮች መስፋፋት፤
4) ድህረ-ዘመናዊነት /Post-modernism
5) የጋብቻ ዉስጥ ትርምሶች፣ ፍቺ፣ ግብረ-ሰዶማዊነት፣ ሴት ከሴት ጋር ጋብቻ፣ ዝሙት...
6) ከሌሎች አካባቢዎችም ይልቅ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ የቢራና የአልኮል መጠጦች መናኻሪያ መሆንና ሌሎችም ደባል ሱሶች፤
7) የበራልን /ኢሉሚናቲዎች ሴራ ማነጣጠር፤
8) እንደሚታወቀዉ ከሌሎች አህጉራት ይልቅ አፍሪካ በባህላዊ ኃይማኖቶች የታጨቀች ናት፤
ከዚህ ባሕላዊ ኃይማኖት ለማላቀቅ ብዙ ዋጋ የተከፈለበት መሆኑን ጥናታዊ ጽሑፎች ያሳያሉ፤ ይህ ማመቻመች አሁንም በኢትዮጵያ በተለይም በወንጌል አማኞችን በብዙ እየጎዳን ነዉ።
የእግዚአብሔር ቃል በዉሸት ሲቀየጥ ዝም አንበል! (2ቆሮ 4፡2)..
ክፍል 3 ይቀጥላል፤ በዚህ Page follow በማድረግ የወ/ዊ በቀለ ዱባጎ ሌሎችንም መንፈሳዊ ትምህርቶች ይከታተሉ።

24/09/2023

የእዉነተኛ ተሐድሶና የእግዚአብሔር ቤት ቅናት እሳት ድምጽ! (ዮሐ 2፡17)
ክፍል 1
በወ/ዊ በቀለ ዱባጎ
Real Reformation and the Zeal of God's House
ወንጌል ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ በ1920ዎቹ በኤስአይኤም ሚሽነሪዎች የተዘራዉ ዘር በመጀመሪያ በቅሎ ፍሬ ያፈራዉ በሃዲያ ምድር ሲሆን፤ ከዚህም በመቀጠል በከምባታ፣ በወላይታ፣ በሲዳማና እንዲሁም በሌሎች የአገራችን ክፍሎች እንደተስፋፋ ቅቡልነት ባላቸዉ መንፈሳዊ ምሁራን የተፃፉ የኢትዮጵያ ቃለሕይት ቤ/ክ ታሪክ መጻህፍት ያረጋግጣሉ፤
1. በወንድዬ ዓሊ የተፃፈዉ "በመከራ ዉስጥ ያበበችቤ/ክ፤ ቅጽ 1" 1990 ዓ/ም
2. በወንድዬ ዓሊ የተፃፈዉ "የእኩለ ሌሊት ወገግታ ቅጽ 2" 1992 ዓ/ም
3. በአቶ ጌታቸዉ በለጠ የተፃፈዉ "ኤሎሄና ሃሌሉያ" 1992 ዓ/ም
4. በሳሙኤል ሀንዳሞና አዲሴ አማዶ አርታዖት፤ በዶ/ር ደስታ ሄሊሶ፣ በዶ/ር ወንድሙ ወንድሙ አበበ፣ በፓ/ር ደገፈ ሰዶሮና በወ/ዊ ተሾመ ተስፋዬ የተፃፈዉ "የወንጌል ታሪክ በሃዲያና አካባቢ፤ 2014 ዓ/ም"
አሁንም ለእዉነተኛ ተሐድሶና የእግዚአብሔር ቤት ቅናት ትግበራ የወንጌል ዘር ተዘርቶ ፍሬዉ ከታየበት የኢትዮጵያ ማዕከል ወይም በአዲሱ መቀመጫ ሆሳዕና የእናት ቃለሕይወት፣የሆሳዕናና አና ሌሞ ሕብረት የተጀመረዉ የእዉነተኛ ተሐድሶና የእግዚአብሔር ቤት ቅናት የመብላት ይቀጥላል፤ (ቤቱ ስል ሕንፃዉና አዳራሹ ወይም ቁሳቁስ እንዳልሆነ ይገባናል።
ወደ ሌሎችም ሕብረቶችና ደቡብ ሸዋ ቀጠና፤ ወደ ሌሎችም ቀጠናዎች፤ ወደ አገር አቀፍም በመዝለቅ ደምብ ሆኖ እንዲቀረጽና እዉነቸኛ ለዉጥ እንዲመጣ ድምጽ መሰማት አለበት!..

ክፍል 2 ይቀጥላል፤ በዚህ Page follow በማድረግ የወ/ዊ በቀለ ዱባጎ ሌሎችንም መንፈሳዊ ትምህርቶች ይከታተሉ።

የተሐድሶና የእግዚአብሔር ቤት ቅንዓት የመብላቱ ጉዳይ (ዮሐ 2፡17)Reformation and the Zeal of God's House(ወ/ዊ በቀለ ዱባጎ፤ የቁ.1 በሌሣ ቃለሕይወት ቤ/ክ አገልጋ...
22/09/2023

የተሐድሶና የእግዚአብሔር ቤት ቅንዓት የመብላቱ ጉዳይ (ዮሐ 2፡17)
Reformation and the Zeal of God's House
(ወ/ዊ በቀለ ዱባጎ፤ የቁ.1 በሌሣ ቃለሕይወት ቤ/ክ አገልጋይ)
መጽሐፍ ቅዱስን በጥልቀትና በስፋት ያጠኑ ሰዎች የመጽሐፍ ቅዱስን በሦስት ደረጃ ይከፍላሉ፤
Levels of Belief (C.S. Lewis. Our Approach, Convictions, Persuasion and Opinion. Pp 14-21)
1ኛ) ጽኑ እምነት መያዝ ያለበት አቋም |Conviction doctrine
ግትር አቋም መያዝ ያለበት |Dogma or conservative action
ይህም የሕይወት፤ የደህንነት/የድነት፤ የሞትና የሕይወት፤ የመኖርና ያለመኖር፤ የዘላለም ሕይወትን የማጣትና ሽልማትንም የማጣት ጉዳይ ነዉ።
ይህ ብቻ አይደለም የእግዚአብሔር ክብርና ወንድምንም የሚያሰናክል፤ ደግሞም የሥነምግባር ዉድቀትንና ዝቅጠትን የሚያስከትል ጉዳይ ነዉ ይሉታል።
ቤተክርስቲያንን የሚያከፋፍሉ እንዲሁም የሐሰት አስተምህሮዎች፤ ጸሎትንና መጽሐፍ ቅዱስን መቃወም፤ የሥላሴ ትምህርትን መቃወም፣ ዝሙትና የጣኦት አምልኮ ወዘተ ናቸዉ።
2ኛ) ሁለተኛዉ የእምነት ደረጃ ደግሞ የተግባቦት እምነት ነዉ፤ |Persuasion
የመጀመሪያዉን ያህል ጠንካራ አቋም መያዝ የማይፈልጉ፤ ደህንነትን የማያሳጡ፤ ቅድስናን የማያጎድፉ፤ ወይንም ለሥነምግባር ዉድቀት የማያበቁ፤ በመጽሐፍ ቅዱስ እዉነት ላይ የተመሰረቱና መሠረታዊ የአስተምህሮ ልዩነት የማያመጡ ናቸዉ። ተግባብተን መኖር የምንችልበት የእምነት አቋም ነዉ።
3ኛ) ሦስተኛዉ የእምነት አቋም ደግሞ አመለካከት ነዉ። |View or Opinion
ይህንን አቋም ማንም ሰዉ በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ ማሳመን አይችልም፤ ምስጢሩ ለአምላካችን የተባሉ ናቸዉ። (ዘዳ 29፡29)
ስለሆነም ስለማክበር ስናነሳ ከላይ ካየናቸዉ ሦስቱ የመጽሐፍ ቅዱስ እምነት አቋም የትኛዉን ይዘን ነዉ የምንከራከረዉ?
አዲሱ ትዉልድ ባሕላዊ ኃይ ማኖቶችን አመቻምቾ የመሸከም ትከሻ አይኖረዉም። ከጌታ ጋር ሆነን ትግሉ ይቀጥላል!
ባለፈዉ በሚለዉ አጭር ጽሁፌ የሆሳዕና እናት ቃለሕይወት ቤተክርስቲያን የጀመረችዉን ጽፌያለሁ፤ ከእነዚህ መኻል የመስቀል በዓል ጉዳይ ነበር፤ እኛም የበሌሣ ቁ 1 ቃለሕይወት ቤተክርስቲያን በ2014 ዓ/ም መጨረሻ ወደ ኢትዮጵያ ቃለሕይወት ዋና ጽ/ቤት ካቀረብናቸዉ የጥያቄ ሀሳቦች የመስቀል በዓል ጉዳይ ነበር።
በአለማችን አንድ ታዋቂ የሥነመለኮት ምሁር ጄ. ዲ. ዲያግለስ የተባለ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት አዘጋጅ ስለ መስቀልና መሰቀል፤ |Cross -crucification እንዲህ ብሏል፤ የአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች ስለ መስቀል፤ ስለ ክርስቶስ የሚደረግ ጥናት እንጂ ከመሬት በቁፋሮ የተገኘ ታሪካዊ መስቀል አይደለም። ብሏል እናስብበት!
|The new testament writers interest in the cross is neither archeological nor historical but Christological. (J.D. Douglas. New Bible Dictionary. P. 246.)
ከዚህ ቀጥሎ በሚቀርበዉ ፅሑፍ ደግሞ ሰዎች መብሉን እየበሉና መጠጡን እየጠጡ እንዴት አምላካቸዉን እግዚአብሔር እንደሚያመልኩ፤
ወይንም ጣኦታትና አጋንንትን በመጨረሻም ሰይጣንና ዲያቢሎስን እንደሚያመልኩና በመብል እንደሚፈተኑ፤ እንደሚታዘዙ እንዲሁም እንደሚያመነዝሩ፤ ሕያዉና ዘላለማዊ ከሆነዉ ከእግዚአብሔር ቃል በቀጥታ በዝርዝር እንመለከታለን። ተከታተሉ!
ወ/ዊ በቀለ ዱባጎ

Address

Hossana
Shewa

Telephone

+251913465598

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when BEREA Believers የቤሪያ አማኞች posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share