በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በሻሸመኔ ወረዳ ዳግማዊ ቁልቢ የኩየራ ደ/ሀ/ቅ/ገ/ቤ/ን ህዝብ ግኑኝነት

  • Home
  • Ethiopia
  • Shashemene
  • በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በሻሸመኔ ወረዳ ዳግማዊ ቁልቢ የኩየራ ደ/ሀ/ቅ/ገ/ቤ/ን ህዝብ ግኑኝነት

በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በሻሸመኔ ወረዳ ዳግማዊ ቁልቢ የኩየራ ደ/ሀ/ቅ/ገ/ቤ/ን ህዝብ ግኑኝነት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በሻሸመኔ ወረዳ ዳግማዊ ቁልቢ የኩየራ ደ/ሀ/ቅ/ገ/ቤ/ን ህዝብ ግኑኝነት, Church, Kuyera, Shashemene.

ታላቅ የክብረ በዓል ጥሪ+++++++++++++++++++በኩየራ ደ/ኀ/ቅ/ገብርኤል ቤተክርስትያን   > በፀበሉ ፈዋሽ የሆነው  > ስለት ሰሚ በሆነው  > ብዙ ታምራት በሚደረግበት  > የእድሜ ...
15/12/2025

ታላቅ የክብረ በዓል ጥሪ
+++++++++++++++++++
በኩየራ ደ/ኀ/ቅ/ገብርኤል ቤተክርስትያን
> በፀበሉ ፈዋሽ የሆነው
> ስለት ሰሚ በሆነው
> ብዙ ታምራት በሚደረግበት
> የእድሜ ባለፀጋ አገልጋይ ካህናት ያሉበት እና ታሪካዊ ደብር በሆነው እና በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በሻሸመኔ ወረዳ ስር በሚገኘው ዳግማዊ ቁልቢ የኩየራ ደ/ኀ/ ቅ/ገብርኤል ቤተ ክርስትያን ታህሳስ 19 ቀን ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ ይሆኑ ዘንድ ቤተክርስትያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

ታህሳስ 19 ኩየራ ገብርኤል አይቀርም!!

11/12/2025
ታላቅ የንግስ በዓል  በዳግማዊ ቁልቢ ኩየራ ደ/ኀ/ቅ/ ገብርኤል ቤተክርስትያን******************************  ሐምሌ 19/2016 ዓ.ም የመልዐኩ ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ...
20/07/2024

ታላቅ የንግስ በዓል በዳግማዊ ቁልቢ ኩየራ ደ/ኀ/ቅ/ ገብርኤል ቤተክርስትያን
******************************
ሐምሌ 19/2016 ዓ.ም የመልዐኩ ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ ድምቀት ይከበራል።
ስለሆነም ከዋዜማው ጀምሮ በቦታው ላይ በመገኘት የበዓሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ እና ከመልዐኩ ረድኤት በረከት ተካፋይ እንድትሆኑ በማለት የደብሩ ሰበካ ጉባኤ በአክብሮት ጥሪውን ያስተላልፋል።

28/05/2023
በኩ/ደ/ሀ/ቅ/ገ/ቤ የስቅለት(የስግደት) በአል አከባበር ሁኔታ በአሁኑ ሰአት
14/04/2023

በኩ/ደ/ሀ/ቅ/ገ/ቤ የስቅለት(የስግደት) በአል አከባበር ሁኔታ በአሁኑ ሰአት

14/04/2023

¹ የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል?
² በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል፤ መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም።
³ የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።
⁴ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው።
⁵ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።
⁶ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።
⁷ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።
⁸ በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ?
⁹ ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ፤ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገኘበትም ነበር።
¹⁰ እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈቀደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል።
¹¹ ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል፤ ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል፥ ኃጢአታቸውን ይሸከማል።
¹² ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።

ትንቢተ ኢሳይያስ 53፥1-12

የሆሳዕና በአል በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በሻሸመኔ ወረዳ ዳግማዊ ቁልቢ ኩ/ደ/ኀ/ቅ/ገ/ቤ/ን በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል።በበአሉ ላይ የደብሩ አገልጋይ ካህናት እና ተጋባዥ እንግዶች  እ...
09/04/2023

የሆሳዕና በአል በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በሻሸመኔ ወረዳ ዳግማዊ ቁልቢ ኩ/ደ/ኀ/ቅ/ገ/ቤ/ን በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል።

በበአሉ ላይ የደብሩ አገልጋይ ካህናት እና ተጋባዥ እንግዶች እንዲሁም ብዙ ቁጥር ያላቸው ምዕመናን ተገኝተዋል።

01/04/2023

¹ ከፈሪሳውያንም ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ፦
² መምህር ሆይ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን አለው።
³ ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው።
⁴ ኒቆዲሞስም፦ ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው።
⁵ ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም።
⁶ ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው።
⁷ ዳግመኛ ልትወለዱ ያስፈልጋችኋል ስላልሁህ አታድንቅ።
⁸ ነፋስ ወደሚወደው ይነፍሳል፥ ድምፁንም ትሰማለህ፥ ነገር ግን ከወዴት እንደ መጣ ወዴትም እንዲሄድ አታውቅም፤ ከመንፈስ የተወለደ ሁሉ እንዲሁ ነው።
⁹ ኒቆዲሞስ መልሶ፦ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? አለው።
¹⁰ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ አንተ የእስራኤል መምህር ስትሆን ይህን አታውቅምን?
¹¹ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ የምናውቀውን እንናገራለን ያየነውንም እንመሰክራለን፥ ምስክራችንንም አትቀበሉትም።
¹² ስለ ምድራዊ ነገር በነገርኋችሁ ጊዜ ካላመናችሁ፥ ስለ ሰማያዊ ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ?
¹³ ከሰማይም ከወረደ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው።
¹⁴-¹⁵ ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል።
¹⁶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።
¹⁷ ዓለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ፥ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውምና።
¹⁸ በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም፤ በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል።
¹⁹ ብርሃንም ወደ ዓለም ስለ መጣ ሰዎችም ሥራቸው ክፉ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለ ወደዱ ፍርዱ ይህ ነው።
²⁰ ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና፥ ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም፤

የዮሐንስ ወንጌል 3 ፥ 1-20

01/04/2023

Address

Kuyera
Shashemene

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በሻሸመኔ ወረዳ ዳግማዊ ቁልቢ የኩየራ ደ/ሀ/ቅ/ገ/ቤ/ን ህዝብ ግኑኝነት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category