ማህበረ ፂዮን ወበ ስንዳፋ Mahiber Tsiyon Web Sendafa

ማህበረ ፂዮን ወበ ስንዳፋ Mahiber Tsiyon Web Sendafa ከልደቱ እስከ አለተ እርገቱ
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 16:13..ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ።...

የአእላፋት ዝማሬ መርሐ ግብር በምስል፡-
06/01/2026

የአእላፋት ዝማሬ መርሐ ግብር በምስል፡-

"ነፍሴን ሀገሯን አሳየኋት።"ነፍስ ሄዳ የምትመጣበት-ደብረ ሮሐ***(ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም - ለድሬ ቲዩብ)የዛሬው የቤተ አማኑኤል ማህሌት ያስቀናል። እንኳን በዚህ ሰሞን ዓመቱን በሙሉ ስ...
06/01/2026

"ነፍሴን ሀገሯን አሳየኋት።"
ነፍስ ሄዳ የምትመጣበት-ደብረ ሮሐ
***
(ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም - ለድሬ ቲዩብ)

የዛሬው የቤተ አማኑኤል ማህሌት ያስቀናል። እንኳን በዚህ ሰሞን ዓመቱን በሙሉ ስለ ላሊበላ ቢወራ መች ይጠገባል? የእናቶች ዜማ ጆሮዬ ላይ ቀርቷል ብዬ የምገልፀው አይደለም። ከሰማሁበት ቀን ጀምሮ ደብረ ሮሐን ሳስብ ጆሮዬ ውስጥ የኖረ ድምፅ ነው።
"ነፍሴን ሀገሯን አሳየኋት
ነፍሴን ሀገሯን አሳየኋት
ሀገሬ ስገባ ካላበላሸኋት" እንዲህ የሚሉ ሰዎች ከየስጋቸው ሀገር ወደ ነፍሳቸው ሀገር መጡ። ላሊበላማ የነፍስ ሀገር ነው። ለነፍስ ያለ ላስታ ደርሷል። ሰብአ ሰገል በኮኮብ ተመርተው ስለ መወለዱ እጅ ሊነሱ ጎል ግርግሙ ጋር እንደ ደረሱ ሁሉ ወንጌል የመራቸው የሀገሬ ሰዎች እነሆ መድኃኒት ተወልዶልናል ሲሉ ስለ ልደቱ ብሥራት ላስታ ገቡ።

የሀገሬ ሰው ዛሬ እንደ ንጉሥ አይሹር ነው። በልቡ የምስጋና ወርቅ ይዞ፣ "ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት" ሊል በምድር ወደአለ ሰማዮ ይጓዛል። ያ ላስታ ላሊበላ ነው። እዚያ ስጋ በነፍስ የሰማይ ቤት የምትጎመዥበት። ለዚህም ነው "ነፍሴን ሀገሯን አሳየኋት" የሚሉት።

በነፍስስ ሀገር ለፈጣሪ ክብር ምስጋና ብቻ ነው። የላሊበላ ተጓዦች በዚያ "ነፍሴን ሀገሯን አሳየኋት" የሚሉትም ለዚህ ነው። ሰብአ ሰገል ከምሥራቅ ወደ እርሱ እንደመጡት ሁሉ የሀገሬ ሰው ከየአለበት ለልደት በዓል ወደ ላሊበላ ይመጣል።

ላሊበላ ህይወት ያለው ቅርስ ነው። ያ ህይወት ደግሞ ምድራዊ ብቻ አይደለም። ወገኔ "አይቴ ሀሎ" ብሎ ለዘመናት እርሱ መድኃኒት መወለዱን የምናስብበት የታላቁ ንጉሥ እና ቅዱስ ደጃፍን ፍለጋ ይመጣል። እየዘመረ
"አያወላውልም ይምረናል
አያወላውልም ይምረናል
ያንን ሁሉ መንገድ ስንመጣው አይቶናል" እያለ።

ያ ሁሉ መንገድ እንደምን ያለ ነው ቢሉ የሀገሬ ሰው ከጥንት እስከ ዛሬ ከመስቀል ክብራ እስከ ለብቃ ኢየሱስ ከደብረ ዳሞ እስከ ዲማ ከጎንደር እስከ ሸዋ ከትግራይ ጫፍ እስከ ጎጃም ከኢትዮጵያ የተመጣው። መጥቶ ለምን መጣሁ የሌለበት። ይልቁንም
"ከእንግዲህ አልቀርም ላሊበላ
ከእንግዲህ አልቀርም ላሊበላ
እሱ ያዘዘውን ያለኝን ልበላ....." እያስባለ ዳግም ለመምጣት የሚያስናፍቅ።

ዋዜማ ነው። ልደቱን ለማክበር ሰው ላስታ ገብቷል። አደፋ ደምቃለች። የደብረ ሮሐ የቀድሞ መጠሪያ አንዱ አደፋ ይባላል። እንደ ማር የሚጣፍጥ የምስጋና መስዋዕት የሚቀርብባት ታላቅ ስፍራ። ኢትዮጵያዊያን የኢየሱስ ክርስቶስን መወለድ እንዲህ ያከብራሉ ያስባለች መካነ ቅርስ። ዛሬ ምሽት የሚሆነውን አስቡት....ቤተ ማርያም
በድጋሚ ለምጠቀማቸው ፎቶዎች Lalibela የተባለውን የፌስ ቡክ ገፅ አመሰግናለሁ።

06/01/2026

23/06/2024
☞ወር በገባ በ29 ታስባ የምትውለው እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስያደረገችው ታዕምር ይህ ነው፡፡☞እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶሰ የተወለደችው በጎንደር ክፍለ ሀገር በደራፎገራ አንበሳ ...
14/09/2022

☞ወር በገባ በ29 ታስባ የምትውለው እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ
ያደረገችው ታዕምር ይህ ነው፡፡
☞እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶሰ የተወለደችው በጎንደር ክፍለ ሀገር በደራ
ፎገራ አንበሳ መዳ ነው፡፡
☞የተወለደችው ክርስቶስ በተወለደበት ቀን ታኅሣሥ 29ቀን በመልአከ
አብሳሪነት ተወለደች፡፡
☞በተወለደችም ጊዜ በእግሯ ቆማ ከጨለማ ወደ ብርሐን ላወጣህኝ ለአብ
ምስጋና ይገባል ለወልድ ምስጋና ለመንፈስ ቅድስ ምስጋና ይገባል ብላ
አመሰግናለች፡፡
☞እርሷ በነበረችበት ዘመን ንጉስ ሱስንዮስ "ሁለት ባሕርይ"የሚለውን የረከሰ
የሮማውያንን ሃይማኖት ሕዝቡ ሁሉ እንዲያምን በማወጁ ምክንያት በሀገራችን
ከፈተኛ የሆነ የሃይማኖት ግጭት ሰለተነሣ ከ8ሺ በላይ ክርስቲያኖች በግፍ
ተጨፍጭፈው ሲየልቁ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ከእነ አቡነ ስምዖን እና
ከሌሎችም ቅድሳን ጋር ተሰልፋ ሰማዕትነት ዐርፋ ሰባት አክሊልን ወርዶላታል፡፡
☞ቅድስት እናታችን አምላኳን እሰከ ጨረሻው በድንግልና መገልገል
ብትፈልግም ዕድሜዋ ለ ከፍ ሲል ቤተሰቦቿ ዘርዓ ክርስቶስ ከሚባል አገረ ገዥ
ጋር አጋባት፡፡ እርሷም ግን በጫጉላ ቤት እያሉ በእኩለ ሌሊት ቧሏን ወንድሜ
ሆይ
እግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ ነገር ድንግልናችንን እጠብቅ አለችው እርሱም እሺ
አላት ይህን ተመካክረው በጸሎት ሲተጉ አደሩ፡፡ በሌሊትም ወደ ባሕር ውስጥ
እየገቡ ጸሎት ያደርጉ ጀመር፡፡
☞በመጨረሻም እርሷ በጳጳሱ በአባ ማርቆስ እጅ ስትመነኩስ ቧሏም
ድንግልናውን እንደጠበቀ በሰማዕትነት አንገቱን ተሰይፎ ዐርፏል፡፡
☞ - - - - መልአኩም ከቅድስት ሀገር
ኢየሩሳሌም መልሶ ወደ ኢትዮጵያ
ካመጣት በኃላ ዛሬ ገዳሟ ካለበት ቦታ ሴትደርስ ከቦታዋ ዓምደ ብርሃን ተተክሎ
በቀሰተ ደመና ተከቦ አይታ ይህቺ ቦታ ምንታምር ብላ ጠራቻት፡፡ በቦታውም ላይ
በመድኃኔ ዓለም ትእዛዝ የቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን በአንዲት ቀን
ብቻ ሠርታለች፡፡
☞እናታችን ቅድስ ፍቅርተ ክርስቶስ የሠራቻት በሰሚዝ(በሰንሰል)እንጨት
በአይጥ ሐረግ፤ በነጠላ ማገር አድርጋ የግድግዳ ቤተ መቅደስ በአንዲት ቀን
ብቻ ሠርታ በታህሳስ 16ቀን በዕለተ እሁድ አሰቀድሳለች፡፡
☞ቅዱስ ሩፉኤልም መሲፋይልም በክንፋቸው አፈር ከእየሩሳሌም አምጥተው
በቦታዋ ላይ ቀላቅለውበታል፡፡
፼ጌታችንም ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ተገልጦላት ቦታዋን ባርኮላታል፡፡
☞ቤተ ክርስቲያኗ አስከ እለተ ምጽአት እንደማትፈርስ ቃል ገብቶላታል፡፡
☞ይቺ ቤተክርስቲያን ጌታችን ለቅድስ ፍቅርተ ክርስቶስ ቃል ኪዳን ሊሰጣት
ሲመጣ ሰግዳለች፡፡ዛሬም በአራቱ አቅጣጫ ሲመለከቱት ዘንበል ብሎ ይታያል፡፡
☞የእናታችን የቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ያደረገችው ታዕምር ይህ ነው፡፡
☞በሀገሯ አቅራቢያ የሚኖሮ አንድ አይነ ስውር ነበር፡፡ ወደ ቤተክርስቲያን እጅ
ይነሣ ዘንድ በዛው በአይኖ መታወር ሁሌ ያዝ ነበር እና እንድታማልደው እናታችን
ቅድስት ፍቅርቶስን ለመለመን ሄደ፡፡
☞በዚየም ቆሞ ሲጸልይ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ እንባዋን እንደ ውሃ
እረጨችው፡፡ በዚያን ጊዜ አይኖቹ በሩለት እና እየ በፊቷም ሰገደ፡፡
☞እስከለተ ሞቴ ድረስ ለሰው አትንገር አለችው ይህን ብላ እናታችን ቅድስት
ፍቅርተ ክርስቶስ ተሰወረች፡፡
☞የእናታችን የቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ የጸሎቷ በረከት አይለየን፡፡
☞የእናታችን የቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ አማላጅነት አይለያችሁ፡፡ የዕረፍቷም
መታሰቢያ የካቲት 29 ቀን ነው፡፡ ወርሐዊ መታሰቢያ ወር በገባ በ 29 ነው፡፡
☞(2015)

አቤቱ ለበረከት አድርግልን
23/03/2022

አቤቱ ለበረከት አድርግልን

03/01/2022

ሼር like comment

Enkuan adersachew
12/12/2021

Enkuan adersachew

   አመታዊ ክብረ በዓል ሁላቹንም አደረሳችሁ
06/07/2021


አመታዊ ክብረ በዓል ሁላቹንም አደረሳችሁ

Address

Sendafa Bake
Sendafa

Telephone

+251946853600

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ማህበረ ፂዮን ወበ ስንዳፋ Mahiber Tsiyon Web Sendafa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share