06/07/2026
እምነት ተራሮችን ብቻ አይደለም የሚያንቀሳቅሰው... እምነት ጊዜውንም ያቆማል!
ኢያሱ በጦርነት መካከል ቆሞ ወደ ሰማይ እጁን ባነሳ ጊዜ፣ የጠየቀው ነገር ተራ አልነበረም። ፀሐይ እንድትቆም ጠየቀ። ጊዜ እራሱ እንዲታዘዝለት ጠየቀ። እና እግዚአብሔር መለሰለት። ፀሐይ ቆመች፥ ወርኅም ቆመ፥ እስራኤልም ድል ነሱ።
ይህ ታሪክ የሚያስተምረን አንድ ትልቅ እውነት አለ፦ ደፋር ጸሎት፣ ደፋር እምነትን ይፈልጋል። ኢያሱ ትንሽ ነገር አልጠየቀም። ትልቅ ነገር ጠየቀ፥ ምክንያቱም እግዚአብሔር ትልቅ አምላክ እንደሆነ ያውቅ ነበር።
ዛሬ በሕይወትህ ውስጥ ጊዜ የቆመ የሚመስልህ፣ ወይም በተቃራኒው ጊዜ በጣም ፈጣን ሆኖብህ የምትታገልበት ሁኔታ ካለ... እወቅ፣ ያ ፀሐይን ያቆመው አምላክ ዛሬም ተመሳሳይ አምላክ ነው። ለአንተም ጸሎትህን ይሰማል። ለአንተም ይታገልልሃል።
እግዚአብሔር ትናንት፣ ዛሬም፣ እስከ ዘላለምም ያው ነው።አሜን!!!