Beto Uba Debre Tsehay District Islamic Affairs

ሰበር ዜና!!!   እንኳን ደስ አላችሁ።አዲሱ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ፀደቀ::"""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""ላ...
25/06/2026

ሰበር ዜና!!! እንኳን ደስ አላችሁ።
አዲሱ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ፀደቀ::
"""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ላለፉት 25 አመታት አገልግሎት ላይ የነበረው ​ የፌደራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 188/1992 ሙሉ በሙሉ የሚተካው አዲሱ ረቂቅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው እለት ፀድቋል::

የዚህ የሕግ ማርቀቅ ሥራው የተከናወነው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ባቀረበው ጥያቄ መሠረት በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት በተዋቀረ ባለ 7 አባላት ያሉት የዳኞችና የባለሙያዎች ኮሚቴ ነው።

​ኮሚቴው የውጭ ሀገራት ተሞክሮዎችንና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተገኙ ጠቃሚ ግብዓቶችን በማካተት የተዘጋጀ ሲሆን ረቂቁ ለፓርላማው ለህግ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመርቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል::

​ሰባት ክፍሎችን ይዞ በአዲስ መልክ የተዘጋጀው ይህ ረቂቅ አዋጅ የፍርድ ቤቶቹን የዳኝነት ሥልጣን፣ አደረጃጀትና አሠራር፣ የዳኞች አሿሿምና በጀት፣ እንዲሁም የፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባኤን በአዲስ መልክ ማቋቋምን ጨምሮ ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችን በዝርዝር አካቷል።

የህዝበ ሙስሊሙ የመልካም አስተዳደር የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበረው የዚህ ተቋም በአዲስ መልኩ መደራጀት ምላሽ የሚሰጥ ነው::

ይህ አዋጅ እንዲፀቅ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ጀምሮ የፌደራል ጠቅይላይ ፍርድ ቤት አመረሮች፣ ረቂቁን ያዘጋጁ የኮሚቴ አባላት ፣ የፓርላማው የህግ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ በማበርከታቸው ላቅ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል::

የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ቁመናቸው ተስተካክሎ ለህዝበ ሙስሊሙ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ የተጀመረው የለውጥ ጉዞ ከአዋጁ በተጨማሪ የሁሉንም ህዝበ ሙስሊም ድጋፍ እና እገዛ ያሻዋል::

ይህ ረቂቅ አዋጅ እንዲፀድቅ ኃላፊነታቸውን ለተወጡ ሁሉ በድጋሚ ላቅ ያለ ምስጋናዮን ማቅረብ እወዳለሁ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የኡሉማ ምስረታ አካህዷልምስረታው ዮተካሄደው በ2017 በተካሄደው ምርጫ አልፈው የክልሉ ም/ቤት አባል ከሆኑ ዑለማዎች ሲሆን በምስረ...
23/05/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የኡሉማ ምስረታ አካህዷል
ምስረታው ዮተካሄደው በ2017 በተካሄደው ምርጫ አልፈው የክልሉ ም/ቤት አባል ከሆኑ ዑለማዎች ሲሆን በምስረታው ወቅት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማዕ ጉባኤ ስራ አስፈፃሚ አባላት ሽህ አብዱሰላም አንዋር እና ሸህ ጀማል ሙሳ የተገኙ ሲሆን ዑለማው የተገኘውን አጋጣሚ ተጠቅሞ ለኡማው አንድነት በርትቶ መሥራት እንዳለበት አሳስበዋል በምስረታው ወቅት በክልሉ የእስልምና ተቋማትን አንድነት፣ ሰላምና የሃይማኖት እሴቶችን ለማጠናከር በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውይይቶች የተደረጉ ሲሆን

ሐጅ ያሲን ከድር አንበሴ በየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የኡሉማ ምስረታ ጉባኤ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት መልእክት፣ በእስልምና እሴቶች ላይ የተመሠረተ አንድነት፣ ሰላምና መቻቻል እንዲጠናከር ጥሪ አቀረበዋል።

እንዲሁም ኡሉማዎች በማህበረሰቡ ውስጥ ያላቸውን ከፍተኛ ሚና በመጠቀም የወጣቶችን ስነ-ምግባር በመገንባት፣ ሰላምን በማስፈንና ህብረተሰቡን ወደ ልማት በማቀራረብ ረገድ የበለጠ እንዲሰሩ አሳሰቡ።

በእያካሄደ በሚገኘው የኡሉማ መሠረት ጉባኤ ላይ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የዘንድሮው የኡሉማ መሠረት ጉባኤ ከወትሮ የተለየ አደረጃጀትና አመሠራረት ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

ሐጅ ያሲን በመልእክታቸው እንደገለጹት፣ የመድረኩ አደረጃጀት ከቀደሙት ጊዜያት በተሻለ ሁኔታ በስፋትና በተዋቀረ መልኩ የተካሄደ ሲሆን፣ ይህም በክልሉ የእስልምና ተቋማት መካከል የተሻለ ቅንጅትና መግባባት እየተፈጠረ መሆኑን ያሳያል ብለዋል።

ባጠቃላይ ምስረታው የዑለማዕ ጉባኤ
ሽህ አብዱረህማን አብዱኮ ዋና ሰብሳቢ
ሸህ አህምድ ሙሀመድ ሀሰን ም/ሰብሳቢ
ኡ/ሱልጣን ሱለይማን ከድር ዋና ፃሃፊ እና
በፈትዋው ዘርፍ
ሸ/ሽረፈዲን ማህሙድን ሰብሳቢ
ሸ/አህመድ ሙሀመድ ም/ ሰብሳቢ
ኡ/አብዱረዛቅ አህመድ ፃሀፊ
ሸ/ሰይድ ሙሐመድን አባል
አድርጎ ተጠናቋል

በቴሌግራም ለመከታተል
👇👇👇
https://t.me/southet1

በ Facebook ለመከታተል
👇👇👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=61587554553111

Smm: -በአርባ ምንጭ ከተማ 'ጃሚዕ' የተሰኘ መስጂድ እና ኢስላማዊ ኮሌጅን ያካተተ ሁለገብ የገበያ ማዕከል ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ በኢትዮጵያ እ/ጉ/ጠ/ም/ ቤት ፕሬዚዳንት ሼይኽ ሀጂ ...
03/05/2026

Smm: -በአርባ ምንጭ ከተማ 'ጃሚዕ' የተሰኘ መስጂድ እና ኢስላማዊ ኮሌጅን ያካተተ ሁለገብ የገበያ ማዕከል ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ በኢትዮጵያ እ/ጉ/ጠ/ም/ ቤት ፕሬዚዳንት ሼይኽ ሀጂ እብራሂም ቱፋ ተቀመጠ!
"""""""""""'"""""""""""'"""""""""""""""""""''''"""'''"""""""""""""""
​የአርባ ምንጭ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የሚያስገነባው የ'ጃሚዕ' ሁለገብ የገበያ ማዕከል ህንፃ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ፣ በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ ተቀምጧል።

​የግንባታ መሰረት ድንጋዩን ያስቀመጡት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሐጂ ያሲን ከድር፣ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምስ አድማሱ እና የአርባ ምንጭ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር መስፍን መንዛ ናቸው።

በመርሃ-ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ከፍተኛ አመራሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም ተገኝተዋል።

​በዕለቱ ንግግር ያደረጉት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፤ የመሰረት ድንጋይ ከማስቀመጥ ባለፈ ግንባታውን በአጭር ጊዜ ወደ ተግባር ቀይሮ ለማጠናቀቅ የሁላችሁም እርብርብ እና ትብብር ያስፈልጋል ብለዋል።

የአርባ ምንጭ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር መስፍን መንዛ በበኩላቸው ጃሚዕ የገበያ ማዕከል አርባ ምንጭ ከተማ ከጀመረቻቸው የልማት ስራዎች አንዱና የከተማዋን ልማት ወደፊት ከሚያራምዱ ፕሮጀክቶች መካከል መሆኑን ጠቅሰው ግንባታው በቅርቡ ተጠናቆ ወደስራ ይገባል ብለዋል።

​ይህ ግዙፍ የ'ጃሚዕ' ሁለገብ የገበያ ማዕከል በውስጡ ከያዛቸው በርካታ የንግድ ማዕከላት በተጨማሪ፣ ዘመናዊ መስጂድ እና ኢስላማዊ ኮሌጅን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል። ይህም ለከተማዋ ሙስሊም ማህበረሰብ ሁለንተናዊ እድገት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ይጠበቃል።

የበቶ ኡባ ደብረ ፀሀይ ወረዳ እስልምና ጉዳይ ምክር ቤት ከበቶ ኻሊድ መስጅድ ህዝበ ሙስሊም ጋር የሹራ  ምክክር አደረጉ።25/08/2018 አ.ልምክር ቤቱ የሠላምንና የአንድነት ዋጋ በመረዳት ...
03/05/2026

የበቶ ኡባ ደብረ ፀሀይ ወረዳ እስልምና ጉዳይ ምክር ቤት ከበቶ ኻሊድ መስጅድ ህዝበ ሙስሊም ጋር የሹራ ምክክር አደረጉ።
25/08/2018 አ.ል
ምክር ቤቱ የሠላምንና የአንድነት ዋጋ በመረዳት መስራት እንደሚገባ ህዝበ ሙስሊሙን አጥንኦት በመስጠት ውይይቱ ተቋጭቷል።

በአክሱም ከተማ ሙስሊሞች ላይ የደረሰውን የመብት ጥሰት የሚያጣራው የጠቅላይ ምክር ቤቱ ልዑክ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ ጋር ተወያዬ።•••••••••...
15/04/2026

በአክሱም ከተማ ሙስሊሞች ላይ የደረሰውን የመብት ጥሰት የሚያጣራው የጠቅላይ ምክር ቤቱ ልዑክ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ ጋር ተወያዬ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ሚያዚያ 7/2018 ዓ.ል| ሸዋል 27/1447 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
መቐለ |

ሚያዚያ 2/2018 የአክሱም ከተማ ሙስሊሞች ተከራይተው በሚሰግዱበት ቦታ በሰጋጆች ላይ ድብደባ የተፈጸመ ሲሆን በርካታ የቁርአን ቅጅዎች ተቀደዋል።

በተጨማሪም የመስጂዱ ንብረቶች በፀጥታ ሃይሎች በተወሰደ እርምጃ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ጥቃቱን ተከትሎ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በአክሱም ከተማ ሙስሊሞች ላይ የደረሰውን የመብት ጥሰት የሚያጣራ ልዑክ ወደ ትግራይ ክልል ልኳል።

ልዑኩ በዛሬው ዕለት ከትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ሌትናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደ ጋር ተወያይቷል።

በውይይቱም ልዑኩ የተፈጸመውን ጥቃት ለትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ሌትናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደ በዝርዝር አስረድቷል።

ፕሬዝደንቱ በአክሱም ከተማ ሙስሊሞች ላይ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እና ሃይማኖትን መሰረት ያደረገ ጥቃት ተቀባይነት የሎለውና የሚወገዝ ተግባር መሆኑን ጠቀወሰው የክልሉ መንግስት የተፈጠረውን ችግር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።

በአክሱም ከተማ ሙስሊሞች ላይ ለሚደርሰው ሀይማኖትን መሰረት ያደረገ የመብት ጥሰት ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት የክልሉ መንግስት ከክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጋር በትብብር እንደሚሰራም ፕሬዝደንቱ አስረድተዋል።

በአክሱም ሙስሊሞች ላይ የተፈጠረውን የመብት ጥሰት ለማጣራት ከጠቅላይ ይክር ቤቱ የተላከው አጣሪ ልዑክ በመብት ጥሰቶች ዙሪያ የመፍትሔ ምክረ ሃሳብ ያካተተ ሪፖርት ያቀርባል።

ዛሬ በመቐለ ከተማ በተካሄደው ውይይት ላይ የሰላም፣ የክልልና ዲያስፓራ ዘርፍ ኃላፊ ዑስታዝ አብዱ ሰዒድ፣ የፕሮጀክት ዘርፍ ኃላፊና የትግራይ ክልል ተወካይ ኢጂነር አንዋር ሙስጠፋ፣ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ስራ አስፈፃሚ አባል ዑስታዝ ዚያድ አሊዬና የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ ሀጂ ሙሐመድ ካህሳይ ተገኝተዋል።
••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

06/04/2026

ይጠቀሙበት የተሻሻለው የመጅሊስ ህገ ደንብ።

20/03/2026

በበቶ ሙስሊም ኢድ አል ፊጥር ኘሮግራም ላይ የቀረበ ግጥም ከእህቶች
ማሻዓላህ

20/03/2026

የበቶ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲማ አቶ በኃይሉ በኢድ አል ፈጥር የስግደት ቦታ ተገኝተው ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ይህንን ይመስላል።ስለተከታተላችሁን እናመሰግናለን።

የዛባ ሙስሊም ማህበረሰብ የኢድ ሶላት በፈቶ
20/03/2026

የዛባ ሙስሊም ማህበረሰብ የኢድ ሶላት በፈቶ

የበቶ ከተማ ሙስሊም ማህበረሰብ የኢድ ሶላት በፈቶበድጋሜ መልካም በዓልኢድ ሙባረክ እንዲሁም መልካም ጁምዓ
20/03/2026

የበቶ ከተማ ሙስሊም ማህበረሰብ የኢድ ሶላት በፈቶ
በድጋሜ መልካም በዓል
ኢድ ሙባረክ እንዲሁም መልካም ጁምዓ

Address

Jinka

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Beto Uba Debre Tsehay District Islamic Affairs posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share