Debub Hossana Kale Hiwot Church

Debub Hossana Kale Hiwot Church ደቡብ ሆሳዕና ቃለ-ሕይወት ቤ/ክ

ሰላም አለን“ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም።  — ዮሐንስ 14፥27የእርሱ ሰላም ልብን ያረጋጋል፣ ነፍስን ያበረታል፣ ህይወታችንንም በ...
22/05/2026

ሰላም አለን

“ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም።
— ዮሐንስ 14፥27

የእርሱ ሰላም ልብን ያረጋጋል፣ ነፍስን ያበረታል፣ ህይወታችንንም በማይደበዝዝ ሰላም ይሞላል። 🤍 እርሱ ሰላሙን ሰጥቶናልና በእርሱ ሰላም ተጠብቀንና ተዘልለን ለዘላለም እንኖራለን

የተወደዳችሁ ወንድሞችና እህቶች እንደምን ቆያችሁ በያላችሁበት የጌታ ፀጋና ሰላም ከእናንተ ጋር ይሁን

የፊታችን እሁድ ማለትም ግንቦት 16 ከ9:00 ጀምሮ ልዩ የሆነ የአምልኮ ፕሮግራም ከኬብሮኖች ጋር ሰላም አለን በሚል ርዕሰ ተዘጋጅቷል ስለሆነም በእለቱ በመገኘት ሰለተሰጠን ሰላም ጌታን ከፍ ከፍ አናደርገዋለን ።

ጌታ በአማኞች ህብረት ውስጥ ካስቀመጠው በረከት ተካፋይ እንሁን ።

Join us
Telegram | Facebook
Telegram | Facebook

የትንሣኤ የአዳር ፕሮግራም በፎቶ 📷📷📷Join usTelegram |Facebook
14/04/2026

የትንሣኤ የአዳር ፕሮግራም
በፎቶ 📷📷📷

Join us

Telegram |Facebook

12/04/2026

''ህያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ፤ ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም''ሉቃ 24:5
ውድ የቤተክርስቲያናችን አባላት እንኳን 2018 ዓ.ም. የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ክርስቶስ ተነሰቷል !

ትንሣኤው ዓመታዊ በዓላችን ብቻ ሳይሆን ዕለታዊ ኑሮአችንም ነው ። በዚህ በዓል የትንሣኤውን ምሥጢር ጠብ የተገደለበትን ሁነት በማሰብ ይቅርታና ፍቅር በአገራችንና በምድራችን እንዲመጣ ልንተጋበት ይገባል ። የሞተብን ውድ ነገር ትንሣኤ ያገኛል ። ቡሩክ ፋሲካ ይሁንላችሁ !

✝ ✝






ሚያዝያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም

ዛሬ ማታ ከ 2:30 ጀምሮ የአዳር ፕሮግራም አይቀርም ‼️‼️‼️
10/04/2026

ዛሬ ማታ ከ 2:30 ጀምሮ የአዳር ፕሮግራም አይቀርም ‼️‼️‼️

ቀን 4: አምላክ ሆኖ ሳለ : ተገረፈ ቆሰለም ሆነ“"ነገር ግን እርሱ ስለ መተላለፋችን ቆሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቁስል እኛ ተፈወስ...
09/04/2026

ቀን 4: አምላክ ሆኖ ሳለ : ተገረፈ ቆሰለም ሆነ

“"ነገር ግን እርሱ ስለ መተላለፋችን ቆሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቁስል እኛ ተፈወስን።"”
— ኢሳይያስ 53:5

የክርስቶስ መሥዋዕትነት እርሱ የቆሰለውና የተገረፈው ስለ ገዛ ጥፋቱ ሳይሆን ስለ እኛ ነበር። የታገሰውም መከራ በእርሱ ላይ የተጫነው የእኛ የኃጢአት ሸክም ነበር።

እያንዳንዱ ግርፋት ስለ ፍርድ ይናገር ነበር እርሱ ግን በዝምታ ተሸከመው። እያንዳንዱ ቁስል ለእኛ ፈውስ የተከፈለውን ዋጋ ይዞ ነበር።

እኛ እርሱ ብቻ ሊሰጠን የሚችለውን እንድንቀበል እርሱ በሕግ የእኛ የነበረውን በእርሱ ላይ ወሰደ።

#ፋሲካዬ #ክርስቶስ


join us

Telegram | Facebook

ቀን 3: አምላክ ሆኖ ሳለ : የተናቀ ሆነ“የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።”  —   53፥3ኢየሱ...
08/04/2026

ቀን 3: አምላክ ሆኖ ሳለ : የተናቀ ሆነ

“የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።”
— 53፥3

ኢየሱስ ፍጹም አምላክ ቢሆንም ተናቀ፣ ተገፋም። የክብር ባለቤት የሆነው እርሱ እንደ ዋጋ ቢስ ተቆጠረ ተዘባበቱበት እንዲሁም እንደ ምንም ተቆጠረ።

ሊሰቃይላቸውና ሊሞትላቸው በመካከላቸው በቆመበት በዚያ ቅጽበት እንኳ አምላክነቱ ተሳለቁበት፣ ማንነቱም ለመሳለቂያነት ዋለ።

ቅዱሱ በመካከላቸው ተገኘ… ነገር ግን በንቀት ታየ።

3 #ፋሲካዬ #ክርስቶስ


join us

Telegram | Facebook

ቀን 2: አምላክ ሆኖ ሳለ : ድሀ ሆነ“የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቸር ስጦታ አውቃችኋልና፤ ሀብታም ሲሆን፥ እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ።”  — ...
07/04/2026

ቀን 2: አምላክ ሆኖ ሳለ : ድሀ ሆነ

“የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቸር ስጦታ አውቃችኋልና፤ ሀብታም ሲሆን፥ እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ።”
— 2ኛ 8፥9

እርሱ ስለጎደለው ሳይሆን እኛ ስለጎደለን ነው። የእኛ ድህነት መንፈሳዊ ነበር ኃጢአት ከእግዚአብሔር መለየት ነበረ ድህነታችን ስለዚህ እርሱ ወደ እኛ ሁኔታ ውስጥ ገባ በእርሱም ላይ አደረገው።

የእርሱ ድሃ መሆን ማለት የእርሱን ስፍራ በእኛ ስፍራ በፈቃደኝነት ለወጠ ማለት ነው። እኛ የእርሱን ጸጋን ጽድቅንና ሕይወትን እንድንቀበል፣ እርሱ የእኛ የሆነውን ሁሉ ወሰደ።

#ፋሲካዬ #ክርስቶስ


join us

Telegram | Facebook

ቀን 1: አምላክ ሆኖ ሳለ : የተረገመ ሆነ“በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን፤”  — ገላትያ 3፥13ኢየሱስ አምላ...
06/04/2026

ቀን 1: አምላክ ሆኖ ሳለ : የተረገመ ሆነ

“በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን፤”
— ገላትያ 3፥13

ኢየሱስ አምላክ ቢሆንም ቅዱስ ንጹሕ እና ፈጽሞ ኃጢአት የሌለበት ሆኖ ሳለ ሊታሰብ ወደማይችል ዝቅተኛው ስፍራ ለመውረድ እና ለእኛ እርግማን ለመሆን መረጠ። እርሱ ለዘላለም የተባረከ ሲሆን ስላደረገው አንዳች ነገር ሳይሆን እኛ ስላደረግነው ነገር ሁሉ እንደ ተናቀ እና እንደ ተፈረደበት እንዲቆጠር ፈቀደ።

የፍቅሩ ጥልቀት ይህ ነው ቅድስናውን ከእኛ ስብራት ለመጠበቅ አልሞከረም ይልቁንም እኛ መሸከም እንዳይኖርብን የእኛን እርግማን በራሱ ላይ ወሰደ የኃጢአትን እና የውርደትን ሸክም ተሸከመ። እኛ ፈጽሞ መሆን የማንችለውን እንድንሆን፣ ቅዱሱ እርሱ ያልነበረውን ሆነ በዚያም ቅጽበት የሰማይ ንጽሕና ከሰው ልጅ ብልሽት ጋር ተገናኘ ፍቅርም ሁሉንም ለመሸከም መረጠ በዚህም የእርግማኑን ኃይል ለዘላለም ሰባበረው።

#ፋሲካዬ #ክርስቶስ


join us

Telegram | Facebook

ልዩ የትንሣኤ በዓል የአዳር ፕሮግራም“በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ።”  — ፊልጵስዩስ 2፥8ያለፈው አልፏል፣ ነገም ታድሷል፤ ክ...
05/04/2026

ልዩ የትንሣኤ በዓል የአዳር ፕሮግራም

“በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ።”
— ፊልጵስዩስ 2፥8

ያለፈው አልፏል፣ ነገም ታድሷል፤ ክርስቶስ ተነስቶ ሞት ተሸንፏል። የትንሳኤውን የምስራች ይዘን፣ በታላቅ ዝማሬና አምልኮ ጌታን ልናከብር ተዘጋጅተናል። ኑ፣ አብረን የክርስቶስን ትንሳኤ እናክብር!

የተወደዳችሁ ወንድሞችና እህቶች እንደምን ቆያችሁ በያላችሁበት የጌታ ፀጋና ሰላም ከእናንተ ጋር ይሁን

የጌታንን ትንሣኤ መታሰቢያ በዓል ልናስብ እንዲሁም ህይወት ያለውን ህይወት ለሰጠን ለእሱ መልሰን ህይወታችንን ልንሰጠውና በአምልኮ ልናከብረው እንዲሁም ልናመሰግነው የፊታችን አርብ ማለትም ሚያዝያ 2 ከምሽቱ 2:30 ጀምሮ ቀጠሮ ይዘናል ስለዚህ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል

join us

Telegram | Facebook
Telegram | Facebook

የአምልኮ ኘሮግራምየተወደዳችሁ ወንድሞችና እህቶች እንደምን ቆያችሁ በያላችሁበት የጌታ ፀጋና ሰላም ከእናንተ ጋር ይሁንየፊታችን እሁድ ማለትም መጋቢት 20 ከ9:00 ጀምሮ ልዩ የሆነ የአምልኮ ...
26/03/2026

የአምልኮ ኘሮግራም

የተወደዳችሁ ወንድሞችና እህቶች እንደምን ቆያችሁ በያላችሁበት የጌታ ፀጋና ሰላም ከእናንተ ጋር ይሁን

የፊታችን እሁድ ማለትም መጋቢት 20 ከ9:00 ጀምሮ ልዩ የሆነ የአምልኮ ጊዜ ከሆሳዕና ዘፀአት ቤተክርስቲያን ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ስለሆነ በእለቱ በመገኘት በአምልኮ ከሚገኝ በረከት ተካፋይ ይሁኑ።

Join us
Telegram | Facebook
Telegram | Facebook

Address

Hossana

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debub Hossana Kale Hiwot Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share