27/04/2026
(18–08–2018 ዓ.ም)
በእግዚአብሔር ቃል፦ ፓስተር እንዳልካቸው ተፈራ
ርዕስ፦ ለእግዚአብሔር ስልጣን መገዛት
መነሻ ክፍል፦ ሮሜ 13፥1–4
መገቢያ፦ ሶስት በእግዚአብሔር የተመሰረቱ ስልጣናት አሉ፤ እነርሱም
#1, የቤተሰብ ስልጣን
#2, የቤተክርስቲያን ስልጣን
#3, የቤተመንግስት ስልጣን
#1, የቤተሰብ ስልጣን
* ይህ የቤተሰብ ስልጣን አስፈላጊ መሆኑን ጳውሎስ ለቆላስይስ ሰዎች በፃፈው መልእክት ይናገራል። ይህም በቤተሰብ መካከል መቀባበል እና መከባበር እንዲኖር አንዱ ለአንዱ በፍቅር እንዲገዛ ያዝዛል።
ቆላ 3፥18–21
"ሚስቶች ሆይ፥ በጌታ እንደሚገባ ለባሎቻችሁ ተገዙ። ባሎች ሆይ፥ ሚስቶቻችሁን ውደዱ መራራም አትሁኑባቸው። ልጆች ሆይ፥ ይህ ለጌታ ደስ የሚያሰኝ ነውና በሁሉ ለወላጆቻችሁ ታዘዙ። አባቶች ሆይ፥ ልባቸው እንዳይዝል ልጆቻችሁን አታበሳጩአቸው።"
* በዚህ ክፍል የምንመለከተው እያንዳንዱ የቤተሰብ አካል የራሱ የኃላፊነት ድርሻ እንዳላቸው ያስረዳል።
* በዚህ ዘመን ያለው የቤተሰብ ተግዳሮት ከፍተኛ ነው፣
#1,የትዳር መፍረስ(ፍቺ)
* ይህ የእግዚአብሔርን ህያው ቃል ችላ በማለት ሁለቱ አንድ ስጋ ይሆናሉ ወደፊት ሁለት ስጋ አይሆንም የሚለው ቀላል ሆኖ የፍቺ መጠን በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል።
#2, ግብረ ሰዶማዊነት
* ይህም ድህረ ዘመናዊነትን ተከትሎ ሰይጣን በቤተሰብ ውስጥ የሚያካሂደው ታላቅ ውጊያ ነው።
#3, ፌሚኒዝም
* ይህም የሴት እኩልነት በሚል ሰበብ ብዙ ያልተገቡ ነገሮች ውርጃ እና ሌሎች ተያያዥ ችግሮችን ሲያስከትል እናያለን።
#2, የቤተክርስቲያን ስልጣን
1ኛ ጴጥ 5፥5
"እንዲሁም፥ ጐበዞች ሆይ፥ ለሽማግሌዎች ተገዙ፤ ሁላችሁም እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ፥ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል።"
* እግዚአብሔር ለቤ/ክ የሰጣቸውን መሪዎችና ሽማግሌዎች መታዘዝና መገዛት የአማኞች ሁሉ ግዴታ ነው።
* መሪዎችና ሽማግሌዎች የምትመሩትን ህዝብ ደግሞ በትህትና እና በፍፁም ቅንነት ታገለግሉ ዘንድ እለምናችኋለሁ።
ዕብ 13፥17
"ለዋኖቻችሁ ታዘዙና ተገዙ፤ እነርሱ ስሌትን እንደሚሰጡ አድርገው፥ ይህንኑ በደስታ እንጂ በኃዘን እንዳያደርጉት፥ ይህ የማይጠቅማችሁ ነበርና፥ ስለ ነፍሳችሁ ይተጋሉ።"
* አማኞችም ለዋኖቻችሁ፣ ማለትም ለሚያገለግሉ
የቤ/ክ መሪዎች ስልጣን ተግዳሮት
#1, የመሪዎች የሞራል ዝቅጠት
* መሪዎች በዚህ ዘመን ያሉበት
"ሆኖም በየዘመናቱ እግዚአብሔር ያስቀመጣቸው ቅሬታዎች አሏት ብዬ አምናለሁ።"
#3, የቤተመንግስት ስልጣን
1ኛ ጴጥ 2፥13—14
"ስለ ጌታ ብላችሁ ለሰው ሥርዓት ሁሉ ተገዙ፤ ለንጉሥም ቢሆን፥ ከሁሉ በላይ ነውና፤ ለመኳንንትም ቢሆን፥ ክፉ የሚያደርጉትን ለመቅጣት በጎም የሚያደርጉትን ለማመስገን ከእርሱ ተልከዋልና ተገዙ።"
ስለ መንግስት ማወቅ ያሉብን ነገሮች
#1, መንግስታት በእግዚአብሔር የተሾሙ መሆናቸው፤
ሮሜ 13፥1
"ነፍስ ሁሉ በበላይ ላሉት ባለ ሥልጣኖች ይገዛ። ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ሥልጣን የለምና፤ ያሉትም ባለ ሥልጣኖች በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው።"
* አሁን ያሉት ባለስልጣናት በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው።
#2, መንግስታት የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸው።
ሮሜ 13፥4
"ለመልካም ነገር ለአንተ የእግዚአብሔር አገልጋይ ነውና። በከንቱ ግን ሰይፍ አይታጠቅምና ክፉ ብታደርግ ፍራ፤ ቍጣውን ለማሳየት ክፉ አድራጊውን የሚበቀል የእግዚአብሔር አገልጋይ ነውና።"
ሮሜ 13፥6
"ስለዚህ ደግሞ ትገብራላችሁና፤ በዚህ ነገር የሚተጉ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸውና።"
ማድረግ የሚገቡን ነገሮች
#1, ልመና እና ፀሎት
1ኛ ጢሞ 2፥1–2
"እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ።"
"የምንፀልየው እኛ ነን፣ የምንፀልየው አሁን ነው፣ የምንፀልየውም እዚሁ ነው።"?
#2, ለባለስልጣናት መገዛት ያስፈልጋል፤
የቤተመንግስት ተግዳሮት
1, ዘረኝነት
ጥያቄ
ለመንግስት የማንታዘዘው መቼ ነው?
* የእግዚአብሔርን መንግስት ትዕዛዝ የሚቃረን ትዕዛዝ ሲያዝዘን የዛኔ እምቢ ማለት እንችላለን። ማለትም ወንጌልን የሚቃወም ሆኖ ከተገኘ እምቢ እንላለን፣ በዚህም ዋጋ ልንከፍል እንችላለን ግን ፀንተን እንቆማለን።
ዘጸ 1፥17–18
"እናንተ የዕብራውያንን ሴቶች ስታዋልዱ፥ ለመውለድ እንደደረሱ ባያችሁ ጊዜ፥ ወንድ ቢሆን ግደሉት፤ ሴት ብትሆን ግን በሕይወት ትኑር። የግብፅም ንጉሥ አዋላጆችን ጠርቶ። ለምን እንዲህ አደረጋችሁ? ወንዶቹን ሕፃናትንስ ለምን አዳናችሁ? አላቸው።"
* ዳን 3፥1–30፣ ዳን 6፥1–28፣ ሐ.ሥራ 4፥19