Hawassa Yehiwot Birhan Church

Hawassa Yehiwot Birhan Church This page is about the spiritual and physical movement of hawassa yehiwot birhan church.

        (18–08–2018 ዓ.ም)በእግዚአብሔር ቃል፦ ፓስተር እንዳልካቸው ተፈራርዕስ፦ ለእግዚአብሔር ስልጣን መገዛትመነሻ ክፍል፦ ሮሜ 13፥1–4መገቢያ፦ ሶስት በእግዚአብሔር የተመሰረቱ ...
27/04/2026


(18–08–2018 ዓ.ም)
በእግዚአብሔር ቃል፦ ፓስተር እንዳልካቸው ተፈራ
ርዕስ፦ ለእግዚአብሔር ስልጣን መገዛት
መነሻ ክፍል፦ ሮሜ 13፥1–4
መገቢያ፦ ሶስት በእግዚአብሔር የተመሰረቱ ስልጣናት አሉ፤ እነርሱም
#1, የቤተሰብ ስልጣን
#2, የቤተክርስቲያን ስልጣን
#3, የቤተመንግስት ስልጣን
#1, የቤተሰብ ስልጣን
* ይህ የቤተሰብ ስልጣን አስፈላጊ መሆኑን ጳውሎስ ለቆላስይስ ሰዎች በፃፈው መልእክት ይናገራል። ይህም በቤተሰብ መካከል መቀባበል እና መከባበር እንዲኖር አንዱ ለአንዱ በፍቅር እንዲገዛ ያዝዛል።
ቆላ 3፥18–21
"ሚስቶች ሆይ፥ በጌታ እንደሚገባ ለባሎቻችሁ ተገዙ። ባሎች ሆይ፥ ሚስቶቻችሁን ውደዱ መራራም አትሁኑባቸው። ልጆች ሆይ፥ ይህ ለጌታ ደስ የሚያሰኝ ነውና በሁሉ ለወላጆቻችሁ ታዘዙ። አባቶች ሆይ፥ ልባቸው እንዳይዝል ልጆቻችሁን አታበሳጩአቸው።"
* በዚህ ክፍል የምንመለከተው እያንዳንዱ የቤተሰብ አካል የራሱ የኃላፊነት ድርሻ እንዳላቸው ያስረዳል።
* በዚህ ዘመን ያለው የቤተሰብ ተግዳሮት ከፍተኛ ነው፣
#1,የትዳር መፍረስ(ፍቺ)
* ይህ የእግዚአብሔርን ህያው ቃል ችላ በማለት ሁለቱ አንድ ስጋ ይሆናሉ ወደፊት ሁለት ስጋ አይሆንም የሚለው ቀላል ሆኖ የፍቺ መጠን በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል።
#2, ግብረ ሰዶማዊነት
* ይህም ድህረ ዘመናዊነትን ተከትሎ ሰይጣን በቤተሰብ ውስጥ የሚያካሂደው ታላቅ ውጊያ ነው።
#3, ፌሚኒዝም
* ይህም የሴት እኩልነት በሚል ሰበብ ብዙ ያልተገቡ ነገሮች ውርጃ እና ሌሎች ተያያዥ ችግሮችን ሲያስከትል እናያለን።
#2, የቤተክርስቲያን ስልጣን
1ኛ ጴጥ 5፥5
"እንዲሁም፥ ጐበዞች ሆይ፥ ለሽማግሌዎች ተገዙ፤ ሁላችሁም እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ፥ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል።"
* እግዚአብሔር ለቤ/ክ የሰጣቸውን መሪዎችና ሽማግሌዎች መታዘዝና መገዛት የአማኞች ሁሉ ግዴታ ነው።
* መሪዎችና ሽማግሌዎች የምትመሩትን ህዝብ ደግሞ በትህትና እና በፍፁም ቅንነት ታገለግሉ ዘንድ እለምናችኋለሁ።
ዕብ 13፥17
"ለዋኖቻችሁ ታዘዙና ተገዙ፤ እነርሱ ስሌትን እንደሚሰጡ አድርገው፥ ይህንኑ በደስታ እንጂ በኃዘን እንዳያደርጉት፥ ይህ የማይጠቅማችሁ ነበርና፥ ስለ ነፍሳችሁ ይተጋሉ።"
* አማኞችም ለዋኖቻችሁ፣ ማለትም ለሚያገለግሉ
የቤ/ክ መሪዎች ስልጣን ተግዳሮት
#1, የመሪዎች የሞራል ዝቅጠት
* መሪዎች በዚህ ዘመን ያሉበት
"ሆኖም በየዘመናቱ እግዚአብሔር ያስቀመጣቸው ቅሬታዎች አሏት ብዬ አምናለሁ።"
#3, የቤተመንግስት ስልጣን
1ኛ ጴጥ 2፥13—14
"ስለ ጌታ ብላችሁ ለሰው ሥርዓት ሁሉ ተገዙ፤ ለንጉሥም ቢሆን፥ ከሁሉ በላይ ነውና፤ ለመኳንንትም ቢሆን፥ ክፉ የሚያደርጉትን ለመቅጣት በጎም የሚያደርጉትን ለማመስገን ከእርሱ ተልከዋልና ተገዙ።"
ስለ መንግስት ማወቅ ያሉብን ነገሮች
#1, መንግስታት በእግዚአብሔር የተሾሙ መሆናቸው፤
ሮሜ 13፥1
"ነፍስ ሁሉ በበላይ ላሉት ባለ ሥልጣኖች ይገዛ። ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ሥልጣን የለምና፤ ያሉትም ባለ ሥልጣኖች በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው።"
* አሁን ያሉት ባለስልጣናት በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው።
#2, መንግስታት የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸው።
ሮሜ 13፥4
"ለመልካም ነገር ለአንተ የእግዚአብሔር አገልጋይ ነውና። በከንቱ ግን ሰይፍ አይታጠቅምና ክፉ ብታደርግ ፍራ፤ ቍጣውን ለማሳየት ክፉ አድራጊውን የሚበቀል የእግዚአብሔር አገልጋይ ነውና።"
ሮሜ 13፥6
"ስለዚህ ደግሞ ትገብራላችሁና፤ በዚህ ነገር የሚተጉ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸውና።"
ማድረግ የሚገቡን ነገሮች
#1, ልመና እና ፀሎት
1ኛ ጢሞ 2፥1–2
"እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ።"
"የምንፀልየው እኛ ነን፣ የምንፀልየው አሁን ነው፣ የምንፀልየውም እዚሁ ነው።"?
#2, ለባለስልጣናት መገዛት ያስፈልጋል፤
የቤተመንግስት ተግዳሮት
1, ዘረኝነት
ጥያቄ
ለመንግስት የማንታዘዘው መቼ ነው?
* የእግዚአብሔርን መንግስት ትዕዛዝ የሚቃረን ትዕዛዝ ሲያዝዘን የዛኔ እምቢ ማለት እንችላለን። ማለትም ወንጌልን የሚቃወም ሆኖ ከተገኘ እምቢ እንላለን፣ በዚህም ዋጋ ልንከፍል እንችላለን ግን ፀንተን እንቆማለን።
ዘጸ 1፥17–18
"እናንተ የዕብራውያንን ሴቶች ስታዋልዱ፥ ለመውለድ እንደደረሱ ባያችሁ ጊዜ፥ ወንድ ቢሆን ግደሉት፤ ሴት ብትሆን ግን በሕይወት ትኑር። የግብፅም ንጉሥ አዋላጆችን ጠርቶ። ለምን እንዲህ አደረጋችሁ? ወንዶቹን ሕፃናትንስ ለምን አዳናችሁ? አላቸው።"
* ዳን 3፥1–30፣ ዳን 6፥1–28፣ ሐ.ሥራ 4፥19

  /Coram Deo/
25/04/2026

/Coram Deo/

 /Coram Deo/ከሚያዚያ 16-18/2018 ዓ/ም በሀዋሳ የሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያንአርብ እና ቅዳሜ ከ11፡30-2፡00 እሁድ ከ3፡00-6፡00 ልዩ የትምህርት ጊዜ ሁላችሁም በጌታ ፍቅ...
20/04/2026

/Coram Deo/
ከሚያዚያ 16-18/2018 ዓ/ም በሀዋሳ የሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን
አርብ እና ቅዳሜ ከ11፡30-2፡00 እሁድ ከ3፡00-6፡00 ልዩ የትምህርት ጊዜ ሁላችሁም በጌታ ፍቅር ተጋብዛችኅል፡ ፡

  (11–08–2018 ዓ.ም)በእግዚአብሔር ቃል፦ ፓስተር Marcusመግቢያ፦ በዚህ ሳምንት እያከበርን ያለነው የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሳኤ መታሰቢያ በዓል እንደሆነ እናውቃለን። * በዚህ ወቅ...
20/04/2026


(11–08–2018 ዓ.ም)
በእግዚአብሔር ቃል፦ ፓስተር Marcus
መግቢያ፦ በዚህ ሳምንት እያከበርን ያለነው የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሳኤ መታሰቢያ በዓል እንደሆነ እናውቃለን።
* በዚህ ወቅት ዓለም ያለችበትን ሁኔታ ስንመለከት በሁሉም አቅጣጫ ችግር፣ ጦርነት እና ምስቅልቅል እንዲሁም የዓለም ኢኮኖሚ በመናጋቱ ሀገራት ሁሉ በጭንቅ ውስጥ ሆነዋል።
* ዓለም በድቅድቅ ጨለማ፣ በታላቅ ጭንቀት ውስጥ ትገኛለች፣ ነገር ግን ሞትን ድል አድርጎ የተነሳው ኢየሱስ ክርስቶስ ይሄን ሁሉ ምስቅልቅል ሊያስተካክለው የሚችል ታላቅ እና ኃይል ያለው አምላክ ነው። አሜን!!!
* ትንሳኤን ስናከብር የኢየሱስ ክርስቶስን ሞት በስቅለት ቀን አስበን እንውላለን፣ ነገር ግን ሁላችን ለትንሳኤው ማለዳ ዝግጁዎች ነን ወይ የሚለውን ልጠይቃችሁ እፈልጋለሁ።
* ድንገት ዛሬ ብንሞት ኢየሱስን አገኘዋለሁ ብላችሁ ታስባላችሁ? አዎ ይሄን ወሳኝ ጥያቄ ልንመልስ ይገባናል። በመስቀል ላይ ስለእኛ በተሰቀለው በኢየሱስ ክርስቶስ ካመንን በርግጥም ከኢየሱስ ጋር በመንግስተ ሰማይ እንገናኛለን።
ዮሐ 17፥3
"እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።"
* ካሉን ሜጋ ቤተክርስቲያናት በላይ እጅግ ወሳኙ እና አስፈላጊው ነገር በኢየሱስ ክርስቶስ አምነን የዘላለም ህይወትን ማግኘታችን ነው።
* ይህንን ወንጌል ያመንን ሰዎች ሁላችን ይህንን ወንጌል ለሌሎች መስጠት እንችላለን።
* ከህግ ሁሉ ፊተኛዋ ትዕዛዝ የትኛዋ ናት?
ማር 12፥30
"አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም አሳብህ በፍጹምም ኃይልህ ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት። ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።"
* ሐዋርያው ጴጥሮስ ኢየሱስን ሶስት ጊዜ የካደ ሰው ነበር፣ በኋላም የቤ/ክ መሰረት የተመሰረተችበት ሰው ነበር።
* ኢየሱስ ከትንሳኤ በኋላ አግኝቶት ሶስት ጊዜ የጠየቀው ጥያቄ አንድ ነበር እርሱም ትወደኛለህ? የሚል ነበር።
ዮሐ 21፥15
"ምሳ ከበሉ በኋላም ኢየሱስ ስምዖን ጴጥሮስን፦ የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ከእነዚህ ይልቅ ትወደኛለህን? አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ግልገሎቼን አሰማራ አለው።"
* በክርስትና ህይወት አንዳንዴ እንደመጀመሪያው ጊዜ ፍቅራችን ላይሆን ይችላል፣ በህይወታችን ልንደክም እንችላለን።
ራዕ 2፥2–4
"ሥራህንና ድካምህን ትዕግሥትህንም አውቃለሁ፤ ክፉዎችንም ልትታገሥ እንዳትችል፥ እንዲሁም ሳይሆኑ፥ ሐዋርያት ነን የሚሉቱን መርምረህ ሐሰተኞች ሆነው እንዳገኘሃቸው አውቃለሁ፤ ታግሠህማል፥ ስለ ስሜም ብለህ ጸንተህ አልደከምህም። ዳሩ ግን የምነቅፍብህ ነገር አለኝ የቀደመውን ፍቅርህን ትተሃልና።"
* በተለያየ አይነት የህይወት ድካም ውስጥ ላለን ለሁላችን ዛሬ አንድ እውነት እንናገራለን፣ የኢየሱስ ፍቅር ዛሬ በውስጣችን እንደገና ይቀጣጠላል።
* የቀድሞ ፍቅርችንን እናድሳለን በዚህም ኢየሱስን በተጠጋንና በቀረብነው ቁጥር እርሱን እየመሰልን እንሄዳለን።
* ኢየሱስ እኛን እናንተ የዓለም ብርሃንና የምድር ጨው ናችሁ ብሎናል። በምድር ላይ የክርስቶስ አምባሳደሮች ነን።
* የእግዚአብሔር በረከት እርሱም የእግዚአብሔር ልጆች እንሆን ዘንድ በክርስቶስ ኢየሱስ ታላቅ በረከትን አግኝተናል። በዚህም የክርስቶስ አካል ሆነናል።
1ኛ ዮሐ 4፥17
"በፍርድ ቀን ድፍረት ይሆንልን ዘንድ ፍቅር በዚህ ከእኛ ጋር ተፈጽሞአል፤ እርሱ እንዳለ እኛ ደግሞ እንዲሁ በዚህ ዓለም ነንና።"
ኢሳ 9፥2
"በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃን አየ፤ በሞት ጥላ አገርም ለኖሩ ብርሃን ወጣላቸው።"
ኢሳ 9፥6
"ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።"
* የእርሱ አካል እንደሆንን እና እርሱን እንደምንመስል በምድራችን ለምናየው የሰላም እጦት በተለያየ የዓለም ክፍል እየተካሄደ ላለው ጦርነት የሰላም አለቃ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ለምድሪቱ ሰላም መፍትሄው እርሱ ነው። እኛም የክርስቶስ አምባሳደሮች ነንና በምድሪቱ ሰላም እንዲመጣ ልንፀልይ እና ልንቃትት ይገባናል።
* ሰላም ማለት ሻሎም ማለታችን ነው። ይህም ሙሉነትን የሚያሳይ ቃል ነው፣ የተበላሸ ግንኙነት፣ የፈረሰ ትዳር እንደገና ሲታደስ የዛኔ ሻሎም ሆነ እንላለን።
* ሻሎም ማለት ተስማምቶ በሰላም አብሮ መኖር ማለታችን ነው።
* የዚህ አለም ችግር እና የሰላም እጦት መፍትሄ የሚያገኘው የሰላም አለቃ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ብቻ ነው። አሜን!!!
1ኛ ቆሮ 13፥1–2
"በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ሆኜአለሁ። ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ።"
* ይህ ክፍል ክርስቲያኖች እንዴት በፍቅር ከሰዎች ጋር መኖር እንዳለብን የሚናገር ነው።
* ኢየሱስን እንወደዋለን የምንል ከሆነ የኢየሱስ ፍቅር በእኛ ላይ ሊታይ እና ሊገለጥ ይገባል።
* በየትኛውም የምድር ክፍል ብንሄድ ከሁሉም ጋር የሚያግባባን አንድ ቋንቋ አለ፣ እርሱም የፍቅር ቋንቋ ይባላል።
ማቴ 5፥9
"የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው፥ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና።"
* በሰዎች መካከል ሰላምን የሚያመጡ የሚያስተራርቁ እነርሱ የተባረኩ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው። የሚያስተራርቁ ሰዎች ውስጣቸው በደስታ የተሞላ ይሆናል።

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ መታሰቢያ ፕሮግራም     (04–08–2018 ዓ.ም)በእግዚአብሔር ቃል፦ ፓስተር ጌቱ አያሌውርዕስ፦ የትንሳኤው ምስክሮች ነንመነሻ ክፍል፦ 1ኛ ቆሮ 15፥1–8     ...
12/04/2026

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ መታሰቢያ ፕሮግራም
(04–08–2018 ዓ.ም)
በእግዚአብሔር ቃል፦ ፓስተር ጌቱ አያሌው
ርዕስ፦ የትንሳኤው ምስክሮች ነን
መነሻ ክፍል፦ 1ኛ ቆሮ 15፥1–8
1ኛ ቆሮ 15፥3–4
"እኔ ደግሞ የተቀበልሁትን ከሁሉ በፊት አሳልፌ ሰጠኋችሁ እንዲህ ብዬ፦ መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፥"

መግቢያ፦ ቆሮንቶስ በግሪክ ሀገር የምትገኝ ከተማ ናት። የግሪክ ሰዎች ደግሞ በሙታን ትንሳኤ የማያምኑ ህዝቦች ነበሩ። ከዚህ በፊት ሐዋርያው ጳውሎስ ስለ ሙታን ትንሳኤ ሰብኮላቸው ነበር።
ሐ.ሥራ 17፥32
"የሙታንንም ትንሣኤ በሰሙ ጊዜ እኵሌቶቹ አፌዙበት፥ እኵሌቶቹ ግን። ስለዚህ ነገር ሁለተኛ እንሰማሃለን አሉት።"
* ወንጌላችን የትንሳኤ ወንጌል ነው! የትንሳኤ ወንጌል የኃይል ወንጌል ነው።
2ኛ ቆሮ 5፥21
"እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።"
*ፃድቅ የሆነውና ኃጢአት ያላወቀው ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሲል በመስቀል ላይ ሞተልን። እኛም ይህን እውነት መቀበልና እና መመስከር አለብን!
* ሐዋርያው ጳውሎስ መፅሐፍ እንደሚል ሲል የብሉይ ኪዳን መፅሐፍ የሆነውን የኢሳይያስን ትንቢት ነው።(ኢሳ 53፥1–12)
* ባለጠጋ የሆነው የአርማትያሱ ዮሴፍ የኢየሱስን አስከሬን ለመቅበር ጲላጦስን ለመነው። ይህ ሰው እጅግ ባለጠጋ ነው፣ ሆኖኝ የኢየሱስን ስጋ ለመቅበር ከዓለት በተወቀረ በአዲስ መቃብር አኖረው።
ማቴ 27፥57–60
"በመሸም ጊዜ ዮሴፍ የተባለው ባለ ጠጋ ሰው ከአርማትያስ መጣ፥ እርሱም ደግሞ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ነበረ፤ ይኸውም ወደ ጲላጦስ ቀርቦ የኢየሱስን ሥጋ ለመነው። ጲላጦስም እንዲሰጡት አዘዘ። ዮሴፍም ሥጋውን ይዞ በንጹሕ በፍታ ከፈነው፥ ከዓለት በወቀረው በአዲሱ መቃብርም አኖረው፥ በመቃብሩም ደጃፍ ታላቅ ድንጋይ አንከባሎ ሄደ።"
* ዛሬስ እኛ ለኢየሱስ ምን እናደርግለታለን? ይህ ባለጠጋ ባለው ነገር አለተመካም ነገር ግን ለኢየሱስ እጅግ የከበረውን ነገር አደረገለት።
ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች ስለኢየሱስ ሞትና ትንሳኤ የሚላቸው ሶስት ነገሮች፦
#1, ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ
#2, ተቀበረም፤
#3, በሦስተኛው ቀን ተነሳ የሚል ነው።
* የኢየሱስን ከሞት መነሳት ያዩ የዓይን ምስክሮች ነበሩ።
1ኛ ቆሮ 15፥5–8
"ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ፤ ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፤ ከእነርሱም የሚበዙቱ እስከ አሁን አሉ አንዳንዶች ግን አንቀላፍተዋል፤ ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ፤ ከሁሉም በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ደግሞ ታየኝ።"
#1, ለኬፋ(ጴጥሮስ) ታየ
#2, ለአስራ ሁለቱ ደቀመዛሙርት ታየ
#3, ከ500 ለሚበዙ ወንድሞች ታየ
#4, ለያዕቆብ ታየ
#5, ለሐዋርያት ታየ
#6, ለጳውሎስ ታየ
* ዛሬ በትንሳኤው እለት የሁላችን ፀሎት እንዲሆን የምፈልገው ኢየሱስን ማየት እንዲሆንልን ነው።
ሐ.ሥራ 1፥3
"ደግሞ አርባ ቀን እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው።"

11/04/2026

መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ
የሀዋሳ የሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን ዋና መጋቢ ፓስተር ጌቱ አያሌው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

           (02–08–2018 ዓ.ም)በእግዚአብሔር ቃል፦ መጋቢ ዶ/ር ጌቱ አያሌውርዕስ፦ የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ምንነትመነሻ ክፍል፦ ገላ 6፥11–18መግቢያ፦ ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች...
11/04/2026


(02–08–2018 ዓ.ም)
በእግዚአብሔር ቃል፦ መጋቢ ዶ/ር ጌቱ አያሌው
ርዕስ፦ የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ምንነት
መነሻ ክፍል፦ ገላ 6፥11–18
መግቢያ፦ ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች የሰበከው ወንጌል በገላትያ ላሉ የስህተት አስተማሪዎች አልተመቻቸውም ነበር።
* የሰው ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ማመን ብቻ በቂ አይደለም፣ ይልቁንም ከእምነት በተጨማሪ የአይሁድ ስርዓት እና ህግ(የግዝረት ስርዓት) ለድነት አስፈላጊ ናቸው ብለው ያስተምሩ ነበር።
* ይህን የሚሉበት ዋና ምክንያት ደግሞ መስቀሉ መከራ እና ስደት ስለሚያመጣ ያንን ላለመጋፈጥ ነው።
ገላ 6፥12
"በሥጋ መልካም ሆነው ሊታዩ የሚወዱ ሁሉ እንድትገረዙ ግድ አሉአችሁ፥ ነገር ግን ስለ ክርስቶስ መስቀል እንዳይሰደዱ ብቻ ነው።"
* የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ማንነታችንን ይገልፀዋል።
* የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ለብዙ ዘመናት ያካበትነውን ትምክህት እና ክፉ ባህሪያት ሁሉ ይገርዘዋል።
የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል
#1, ዓለምን ከእኛ ውስጥ ያስወግደዋል፤
ገላ 6፥14
"ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።"
* "ዓለም ለኔ የተሰቀለበት" የሚለው ላይ ዓለም ሲል፦ እግዚአብሔርን፣ መንግስቱን እና ፅድቁን የሚቃወም ድርጊት እና አስተሳሰብ ማለቱ ነው።
* ስለዚህ ይህ ድርጊት በመስቀል ላይ ተሰቅሏል ማለታችን ነው።
1ኛ ዮሐ 2፥15–17
"ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም። ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል።"
#2, አሮጌውን አስተሳሰባችንን ይገርዘዋል፤
ገላ 2፥20
"ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።"
ገላ 5፥24
"የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ።"
ኤፌ 4፥22–24
"ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥ በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፥ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ።"
#3, የሰይጣንን ራስ ይቀጠቅጣል፤
ዘፍ 3፥15
"በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ።"
* ከሴቲቱ የተወለደው ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራንዮ መስቀል ላይ በሰራው ስራ ይሄ ትንቢት ተፈፅሟል።
ገላ 4፥4
"ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤"
ዕብ 10፥19–22
"እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ በመረቀልን በአዲስና በሕያው መንገድ ወደ ቅድስት በኢየሱስ ደም በመጋረጃው ማለት በሥጋው በኩል እንድንገባ ድፍረት ስላለን፥ በእግዚአብሔርም ቤት ላይ የሆነ ታላቅ ካህን ስላለን፥ ከክፉ ሕሊና ለመንጻት ልባችንን ተረጭተን ሰውነታችንንም በጥሩ ውኃ ታጥበን በተረዳንበት እምነት በቅን ልብ እንቅረብ፤"
* ቅን የሆነ ልብ ሊኖረን ይገባል፣ ምክንያቱም ክፋትና ተንኮል የእባቡ ባህሪይ ነው። ስለዚህ ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ በእምነት እና በቅን ልብ ልንቀርብ ይገባናል። ይህ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኛል።
* ኢየሱስ ክርስቶስን አምነው የዳኑ ሰዎች ትምክህታቸውን የኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል ያደርጋሉ።
የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በግል ህይወታችን ምን ያደርጋል?
#1, በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል በሆነው ቤዛነት የኃጢአት ይቅርታ እና ስርየት ያስገኝልናል።
#2, ሰውን ከእግዚአብሔር ጋር፣ ከባልንጀራ ጋር እና ከራስ ጋር የሚያስታርቅ ነው።
ኤፌ 2፥12–13
"በዚያ ዘመን ከእስራኤል መንግሥት ርቃችሁ ለተስፋውም ቃል ኪዳን እንግዶች ሆናችሁ በዚህም ዓለም ተስፋን አጥታችሁ ከእግዚአብሔርም ተለይታችሁ ያለ ክርስቶስ ነበራችሁ። አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል።"
* የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ያቀራርበናል፣ አንድ ያደርገናል።
ኤፌ 2፥14–16
"እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን ያዋሐደ በአዋጅ የተነገሩትንም የትእዛዛትን ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ፤ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ፥ ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው።"
ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሆኖ ምን አለ?
#1,የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አላቸው፤
* መስቀሉ ይቅርታ አስገኝቶልናል!
#2, ኢየሱስ ለእናቱ እነሆ ልጅሽ አላት፣ ቀጥሎም ለዮሐንስ እነሆ እናትህ አለው።
* መስቀሉ በህብረት እንድንሆን እንድንደጋገፍ አዝዞናል።

  ፕሮግራም      (27–07–2018 ዓ.ም)በእግዚአብሔር ቃል፦ ፓስተር ዮሴፍ በቀለርዕስ፦ የሐዋርያው ወርቃማው ፀሎትመነሻ ክፍል፦ ፊልጵ 1፥9–11"ለእግዚአብሔርም ክብርና ምስጋና ከኢየሱስ...
05/04/2026

ፕሮግራም
(27–07–2018 ዓ.ም)
በእግዚአብሔር ቃል፦ ፓስተር ዮሴፍ በቀለ
ርዕስ፦ የሐዋርያው ወርቃማው ፀሎት
መነሻ ክፍል፦ ፊልጵ 1፥9–11
"ለእግዚአብሔርም ክብርና ምስጋና ከኢየሱስ ክርስቶስ የሚገኝ የጽድቅ ፍሬ ሞልቶባችሁ፥ ለክርስቶስ ቀን ተዘጋጅታችሁ ቅኖችና አለ ነውር እንድትሆኑ የሚሻለውን ነገር ፈትናችሁ ትወዱ ዘንድ፥ ፍቅራችሁ በእውቀትና በማስተዋል ሁሉ ከፊት ይልቅ እያደገ እንዲበዛ ይህን እጸልያለሁ።"
መግቢያ፦ ይህቺ የፊልጵስዩስ ቤተክርስቲያን የተተከለችው በመጀመሪያው በጳውሎስ የወንጌል ጉዞ ወቅት ነበር። ጳውሎስ ይህን መልእክት የፃፈውም ከአስር አመት በኋላ ነው።
* በዚህ አራት ምዕራፎች ውስጥ በእኔ፣ ለእኔ እና የኔ የሚሉ ከመቶ በላይ ቃላትን እንመለከታለን።
* የፊልጵስዩስ ቤተክርስቲያን ለጳውሎስ የእረፍት ወይም ኮንፈርት ዞን ናት። ይህም ይህቺ ቤተክርስቲያን ለጳውሎስ የእረፍት እና የሰላሙ ምክንያት እና ስፍራ ስለሆነች ነው።
ለዚህች ቤ/ክ ጳውሎስ አስደናቂ የሆነ ፀሎት ይፀልይላቸዋል።
1, ከሁሉም የሚሻለውን ለይተው እንዲያውቁ
2, ነቀፋ እና ነውር የሌላቸው ሆነው እንዲኖሩ
3, በክርስቶስ የሚገኝ የፅድቅ ፍሬ እንዲሞላባቸው
4, በእውቀትና በማስተዋል እያደገ የሚሄድ ፍቅር እንዲኖራቸው፤
* ጳውሎስ የፊልጵስዩስ ቤ/ክ በነበራት ፍቅር ሁልጊዜ ይደነቃል።
* ይህ ፍቅር ግን በጥልቅ እውቀት እና በማስተዋል እያደገ የሚሄድ እንዲሆን ይፀልይላቸዋል።
* ይህ ፀሎት እጅግ አስደናቂ ነው፣ በዚህ ዘመን ላለነው አማኞችም ወሳኝ ነው ምክንያቱም የብዙዎች ፍቅር ያለ እውቀት እና ያለ ማስተዋል ነው።
* በቃየን እና በአቤል መካከል የነበረውን ግንኙነት ስንመለከትም በወንድማማች መካከል ተፈጥሮአዊ ወዳጅነት እና ፍቅር ቢኖርም፣ በእግዚአብሔር ፊት መስዋዕት ካቀረቡ በኋላ ግን ያ የወንድምነት ፍቅር እና መዋደድ ተረሳ የገዛ ወንድሙ ላይ እጁን አነሳ፣ ገደለውም፣ ፍቅራችን በጥልቅ እውቀት ላይ የተመሰረተ ካልሆነ አንድ ቀን በጣም እምንወዳቸው ሰዎች ላይ እጃችንን ልናነሳ እንችላለን። ስለዚህ ፍቅራችን በእውቀት እና በማስተዋል ይሁን። አሜን!!!
* በኑኃሚን እና በሩት መካከል የነበረው ፍቅር በእውነተኛ እውቀት እና ማስተዋል የተመሰረተ ነበር፣ ሩት ነገሮች በከፉ ጊዜ ተስፋ በሚያስቆርጥ ሌላኛይቱ ሴት ወደኋላ እንደተመለሰች ሳይሆን፣ በኔና ባንቺ መካከል ያለው ፍቅር እና ግንኙነት ላይ የተመሰረተ ነው፣ ስለዚህ ካንቺ አልለይም እስከሞት ድረስ ካንቺ ጋር እሆናለሁ አለቻት።
* በዚህም ምክንያት እግዚአብሔር ሩትን እውነተኛ በረከት ባረካት፣ የእርሻው ጌታ ቦዔዝም አስደናቂ ምስክርነት ሰጣት።
ሩት 3፥10
"ቦዔዝም አላት፦ ልጄ ሆይ፥ በእግዚአብሔር የተባረክሽ ሁኚ፤ ባለጠጋም ድሀም ብለሽ ጐበዛዝትን አልተከተልሽምና ከፊተኛው ይልቅ በመጨረሻው ጊዜ ቸርነት አድርገሻል።
ይሄ ጥልቅ ፍቅር እንዴት ይገኛል?
#1, በመስቀል ላይ በክርስቶስ በተሰራው ስራ ይሄ እውነተኛና ጥልቅ ፍቅር ይገኛል።
* የሐዋርያው ዮሐንስን ህይወት ስንመለከት ይሄን ፍቅር ከኢየሱስ እንዴት እንደተማረ እንገነዘባለን፣
ሉቃ 9፥54
"ደቀ መዛሙርቱም ያዕቆብና ዮሐንስ አይተው፦ ጌታ ሆይ፥ ኤልያስ ደግሞ እንዳደረገ እሳት ከሰማይ ወርዶ ያጥፋቸው እንል ዘንድ ትወዳለህን? አሉት።"
ማቴ 20፥20–21
"በዚያን ጊዜ የዘብዴዎስ ልጆች እናት ከልጆችዋ ጋር እየሰገደችና አንድ ነገር እየለመነች ወደ እርሱ ቀረበች። እርሱም፦ ምን ትፈልጊያለሽ? አላት። እርስዋም፦ እነዚህ ሁለቱ ልጆቼ አንዱ በቀኝህ አንዱም በግራህ በመንግሥትህ እንዲቀመጡ እዘዝ አለችው።"
* አስቀድሞ ጨካኝ፣ ለሰዎች የማይራራና ራስ ወዳድ ሰው ቢሆንም ኢየሱስን በመስቀል ላይ ሆኖ የሰራውን ስራ ካየ በኋላ ይሄን ጥልቅ ፍቅር ተረዳ ህይወቱም ስብከቱም ትምህርቱም ተቀየረ፣ ፍቅር ፍቅር ፍቅር ማለት ጀመረ።
1ኛ ዮሐ 4፥16
"እኛም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር አውቀናል አምነንማል። እግዚአብሔር ፍቅር ነው፥ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።"
* ይሄ ፍቅር ዛሬም በኛ ህይወት ይገለጥ፣ አሜን!!!

 #እሁድ 🗓መጋቢት 27 ⏰ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ
02/04/2026

#እሁድ 🗓መጋቢት 27 ⏰ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ

       (20–07–2018 ዓም)በእግዚአብሔር ቃል፦ ፓስተር ኢያሱ ሰለሞንርዕስ፦ እንደገና ለድልመነሻ ክፍል፦ ኢያሱ 7፥1–26፣ 8፥1–2መግቢያ፦ ይህ ከላይ ያነበብነው ክፍል የእስራኤል ህ...
29/03/2026


(20–07–2018 ዓም)
በእግዚአብሔር ቃል፦ ፓስተር ኢያሱ ሰለሞን
ርዕስ፦ እንደገና ለድል
መነሻ ክፍል፦ ኢያሱ 7፥1–26፣ 8፥1–2
መግቢያ፦ ይህ ከላይ ያነበብነው ክፍል የእስራኤል ህዝብ በጠላት ድል የተነሱበት እና የተሸነፉበትን ታሪክ የሚዳስስ ነው። ይህም የሆነበት ምክንያት የእስራኤል ልጆች እርም የሆነን ነገር በማድረግ እግዚአብሔርን በመበደላቸው ነው። የእስራኤል ልጆች ታላቋን ኢያሪኮ አሸንፈው የመጡ ቢሆንም፣ በዚህ ክፍል ግን በትንሿ ጋይ ተሸነፉ።
* በኤልያስም ህይወት ያየነው ይሄ ነው ታላላቅ የሚባሉ የበዓል ነብያትን በእግዚአብሔር ተወራርዶ በማሸነፍ 400 የበዓል ነብያትን በፊቱ ያሳረደ ኤልያስ፣ ጥቂት እልፍ ብሎ ተራ ለሆነችው ለኤልዛቤል ወሬ ተሸንፎ፣ ታላቅ ፍርሃት ውስጥ ሲገባ እንመለከታለን(1ኛ ነገ 18 እና 19)። እንደውም በቃኝ እኔ ከአባቶቼ አልበልጥም እና ውሰደኝ አለ።
* ነገር ግን እግዚአብሔር ኢየሱን እንደገና ትናንት ወዳሸነፏቸው ወደ ጋይ ሰዎች እንዲሄድ አዘዘው(ኢያ 8፥1)፤ ወደ ድል እንዲሄድ አዘዘው።
* እግዚአብሔር ወደ ኤልያስም መጥቶ እንደገና እንዲቆም እና ተመልሶ እንዲሄድ ወደ ድል እንዲጓዝ አደረገው።
* እግዚአብሔር ተስፋ በቆረጥንበት ነገር ላይ ላሸነፈን ነር
እንደገና ለመነሳት ምን እናድርግ?
#1, ከውድቀታችን መነሳት፤ ወይም ውድቀታችንን አምነን አለመቀበል፤
ኢያሱ 7፥7–9
"ኢያሱም አለ፦ ዋይ! ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ በአሞራውያን እጅ አሳልፈህ ትሰጠን ታጠፋንም ዘንድ ይህን ሕዝብ ዮርዳኖስን ለምን አሻገርኸው? በዮርዳኖስ ማዶ መቀመጥን በወደድን ነበር እኮ! ጌታ ሆይ፥ እስራኤል በጠላቶቻቸው ፊት ከሸሹ ምን እላለሁ? ከነዓናውያንም በምድሪቱ የሚኖሩ ሁሉ ሰምተው ይከብቡናል፥ ስማችንንም ከምድር ያጠፋሉ፤ ለታላቁ ስምህም የምታደርገው ምንድር ነው?"
* ውድቀትን መካድ ሳይሆን ውድቀትን አለመቀበል ማለትም ይህንን ውድቀት እግዚአብሔር ይቀይረዋል ብሎ ማመን ነው።
* ውድቀት ውድቀትን ይስባል፣ ለመነሳት ራሳችንን ካላዘጋጀን ሌላ ውድቀት ይጠራብናልና፣ ልክ እንደ ኢያሱ ልብስ መቅደድ፣ ዋይ ማለት እና መጮህ ያስፈልጋል።
* 2ኛ ሳሙ 11 ላይ የምናገኘው ታሪክም ውድቀት ውድቀትን እንዴት እንደሚስብ የመያሳይ ነው። ዳዊት የሰው ሚስት ውስዶ በማስነወር የመጀመሪያውን ውድቀት ወደቀ፣ ሆኖም ከዚህ ውድቀት ከመነሳት ይልቅ ከዚህ ለማምለጥ ሲል፣ እንደገና የሴቲቱን ባል ኦርዮን አስገደለው።
* ዳዊት የመጀመሪያ ውድቀቱን ለመሸሸግ ሲል ወደሌላ ውድቀት ውስጥ ገባ፣ በዚህም እግዚአብሔር ይህን ስላደረገ በቤቱ ላይ ሰይፍ እንደማይጠፋ ነገረው።
#2, መፀለይ አለብን፤
ኢያሱ 7፥6
"ኢያሱም ልብሱን ቀደደ፥ እርሱና የእስራኤልም ሽማግሌዎች በእግዚአብሔር ታቦት ፊት እስከ ማታ ድረስ በግምባራቸው ተደፉ፤ በራሳቸውም ላይ ትቢያ ነሰነሱ።"
* መፀለይ ለውጥ ያመጣል፣ መፀለይ ውጤት አለው። ስንፀልይ ለውጥ ካመጣን፣ ውጤት ካገኘን፣ ካልፀለይን መለወጥ አንችልም፣ ማግኘት ያለብንንም አናገኝም።
* መፀለይ በሰዎች ህይወት ውስጥ አስገራሚ ነገር ያመጣል።
"ስንፀልይ እግዚአብሔር ይሰራል፣ ሳንፀልይ እኛ እንሰራለን።" ዶ/ር ደስታ ላንጋና።
* በህይወታችን ለውጥ እንዲመጣ ከፈልግን እግዚአብሔርን በፀሎት እንፈልግ፤ እንፀልይ።
* አለመፀለይ ከእግዚአብሔር መንግስት ባያጎድለንም፣ ከእግዚአብሔር ፀጋ ግን ያጎድለናል።
* በእግዚአብሔር ፊት በህብረት ለመፀለይ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንምጣ፣ ራሳችንን እናዋርድ።
* የሚፀልዩ ሰዎችን እግዚአብሔር እንደገና ያነሳቸዋል።
#3, ንሠሐ መግባት፤
ኢያሱ 7፥10–11
"እግዚአብሔርም ኢያሱን አለው፦ ለምን በግምባርህ ተደፍተሃል? ቁም፤ እስራኤል በድሎአል፤ ያዘዝኋቸውንም ቃል ኪዳኔን አፍርሰዋል፤ እርም የሆነውንም ነገር ወሰዱ፥ ሰረቁም፥ ዋሹም፥ በዕቃቸውም ውስጥ ሸሸጉት።"
* እስራኤል እግዚአብሔርን በድለዋልና ንሰሐ መግባት ነበረባቸው። ምክንያቱም በእግዚአብሔር ፊት ነውር እና እርም የሆነውን ወስደዋልና።
* ኢያሱም ወዲያው እርምጃ ወሰደ፤
ኢያሱ 7፥19–20
"ኢያሱም አካንን፦ ልጄ ሆይ፥ ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ክብር ስጥ፥ ለእርሱም ተናዘዝ፤ ያደረግኸውንም ንገረኝ፤ አትሸሽገኝ አለው። አካንም መልሶ ኢያሱን፦ በእውነት የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን በድያለሁ እንዲህና እንዲህም አድርጌአለሁ።"
* አካን ያደረገውን ሁሉ በኢያሱ ፊት ዘረዘረ፣ ሆኖም ዘግይቶ ነበር፣ ኢያሱም ለምን አስጨነቅኸን ብሎ ንሰሐ ባለመግባቱ እንዲገደል ፈረደበት።
* ዛሬም በዚህ ዘመን በእግዚአብሔር ፊት በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ልንበድል እንችላለንና ንሰሐ እንግባ።
* ንሰሐ የሚገቡ ሰዎች ደካሞች ሆነው ሳይሆን ለእግዚአብሔር ቅርብ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው።
#4, የእግዚአብሔርን ፍቃድ መከተል፤
ኢያሱ 8፥2
"በኢያሪኮና በንጉሥዋም እንዳደረግህ እንዲሁ በጋይና በንጉሥዋ ታደርጋለህ፤ ምርኮዋንና ከብትዋን ግን ለራሳችሁ ትዘርፋላችሁ፤ ከከተማይቱም በስተ ኋላ ድብቅ ጦር አስቀምጥ አለው።"
* እግዚአብሔር ትናንት የተሸነፉበትን ጦርነት እንደገና ለድል ሊያበቃቸው ፍቃዱን ለኢያሱ ሲሰጠው እንዴት እና ወዴት መሄድ እንዳለበት ነገረው። ኢያሱም የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ሰማ፣ ፈቃዱንም አደረገ።
* የዛሬው መልዕክቴ ይሄ ነው እግዚአብሔር እንደገና ለድል ያነሳናል። ለዚህም ከላይ ልናደርጋቸው የሚገቡትን 4 ወሳኝ ነገሮች እናድርግ። አሜን!!!

29/03/2026


🗓ዘውትር እሁድ ከ 3:00-6:00 የቃልና የአምልኮ ጊዜ
🏥ሀዋሳ የሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን የባንክ አካውንቶች
ንግድ ባንክ- 1000013471596
አዋሽ ባንክ- 013521439238200
ብርሃን ባንክ- 2500060008678
ሲዳማ ባንክ- 3424302000034
ዳሽን ባንክ- 0217002922002
መባ፣አስራት እና የፍቅር ስጦታችሁን መላክ ትችላላችሁ ጌታ ይባርካችሁ

 #እሁድ መጋቢት 20 ከ3:00 ጀምሮ በክብር ተጋብዛችኋል::
27/03/2026

#እሁድ መጋቢት 20 ከ3:00 ጀምሮ በክብር ተጋብዛችኋል::

Address

Hawassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hawassa Yehiwot Birhan Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category