Hawassa Alamura Full Gospel Church

Hawassa Alamura Full Gospel Church “ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።” ዕብራውያን 13፥8

ቀን :-16/09/18 ዓ.ምእሁድ አምልኮፀሎት :- በወንጌላዊት ለወግነሽ አርጋውአምልኮ :- በቤተክርስቲያናችን የአምልኮ መሪዎችዝማሬ :- በቤቴል መዘምራንየእግዚአብሔር ቃል :- በፓስተር ማቲ...
24/05/2026

ቀን :-16/09/18 ዓ.ም
እሁድ አምልኮ
ፀሎት :- በወንጌላዊት ለወግነሽ አርጋው
አምልኮ :- በቤተክርስቲያናችን የአምልኮ መሪዎች
ዝማሬ :- በቤቴል መዘምራን
የእግዚአብሔር ቃል :- በፓስተር ማቲው ሄነሪ
ርዕስ :- የእግዚአብሔር ንጉስ
“አሕዛብ ለምን ያጕረመርማሉ? ወገኖችስ ለምን ከንቱን ይናገራሉ?”
— መዝሙር 2፥1-12
🔸የንጉስ ዝማሬ በመባል የሚታወቅ ክፍል ሲሆን ለእስራኤል ንጉስ ለዳዊት የተፃፈ ቢሆንም ከዚህም በላይ ስለ ንጉሡ ጌታ እየሱስ ይናገራል።
⭕️ከዚህ በመቀጠል አራት ዋና ዋና ነጥቦች እንመለከታለን
1.በእግዚአብሔር ላይ የተነሱ ያላመኑ የምድር ነገስታት (ቁ1-3)
▪️በእግዚአብሔር እና በተቀባው በመሲሑ ላይ በቁጣ እና በከንቱ ክፉ ንግግር ተናገሩ
2.በሰማይ ያለው ሉዐላዊ አምላክ (ቁ4-6)
▪️እርሱ ያህዌህ የሆነ ሉዐላዊ አምላክ እንደነገስታቱ በቁጣ አልተናገረም ነገር ግን በዙፋኑ ላይ ተቀምጦ ይስቅባቸዋል
▪️ምክኒያቱም የሚናገርበት ጊዜ ገና ወደፊት የሚመጣ ስለሆነ
3.የሰማያዊው ሉዐላዊው አምላክ የመጨረሻ አዋጅ እና ድንጋጌ (ቁ7-9)
▪️ህዝቡን እና መሪዎችን አይቶ ሊል የሚፈልገውን ሁሉ ተናገረ
▪️የተቀባውን መረጠው ልጄ ብሎ ጠራው(ዘፍ 3÷)
🔸ድል ማድረጉን ያኔ የጀመረ ሲሆን ድንግል ፀንሳ ስትወልድ እውን ሆነ ሞትም ክርስቶስ ወደ መስቀል በሄደ ጊዜ ተወገደ የሞትም ሀይል ከሙታን በተነሳ ጊዜ ተሻረ።ዳግም በሚመጣበት ጊዜ በብዙ ክብር እናየዋለን የጠሉትም ሁሉ ይሰግዱለታል
🔻ልጄ አለው - ይህ የክብር ቦታን የሚገልፅ ነው
(ማት 17 ፣ ማት 3)
4.እውነተኛውን ንጉስ ለማምለክ የተደረገው ጥሪ
▪️እግዚአብሔር እራሱ ለህዝቡ የተናገረው በጣም ወሳኝ የሆነ ማስጠንቀቂያ እንዲህ ሲል ሰጠ
🔻"በአመፃቹ አትቀጥሉ ኑ እና ጌታን በፍርሃት በመንቀጥበጥ አምልኩት አለ።
⭕️ማጠቃለያ
🔸በምድር ላይ ያለው የትኛውም ክፉ እቅድ እና አመፅ ሁሉ እግዚአብሔር ያውቃል
🔸እንድናመልክ የተጠራውን ክርስቶስን የመቃወም እና የመቀበል ምርጫ ተሰጥቶናል
🔻ባንቀበል ነፃ የሆንን ይመስለናል ግን በእስራት ስር ነን
🔻ብንቀበል ጌታም ይቀበለናል የዘላለም ህይወት ይኖረናል
✅ይህንን ጌታ ሁልጊዜ ልንቀበል ልንከተል ልናመልከው እና ልናከብረው ይገባናል

Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61567498017093&mibextid=ZbWKwL
Telegram
https://t.me/+AqjPGNRFvlEyMmFk
Youtube
https://youtube.com/?si=fwcZPawNrwOD_thg
Tiktok
https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1&sender_device=pc
Instagram
https://www.instagram.com/hawassaalamurafullgospelchurch/
Follow, Like, Share በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ፡፡

ቀን 09/09/18አመታዊ የልጆች ኮንፈረንስ 👉🏿ፀሎት:- በወንድም ተቋም ደምሴ👉🏿አምልኮ:- በልጆች አምልኮ መሪዎች👉🏿መዝሙር :-በናዝራዊያን ኳ👉🏿የእግዚያብሄር ቃል ትምህርት :-በእህት ቡሩክ...
17/05/2026

ቀን 09/09/18
አመታዊ የልጆች ኮንፈረንስ
👉🏿ፀሎት:- በወንድም ተቋም ደምሴ
👉🏿አምልኮ:- በልጆች አምልኮ መሪዎች
👉🏿መዝሙር :-በናዝራዊያን ኳ
👉🏿የእግዚያብሄር ቃል ትምህርት :-በእህት ቡሩክታዊት ጎዳና
👉🏿ርዕስ:- ለወላጆች ስለ ልጆች አስተዳደግ ከእግዚአብሔር ቃል አንፃር አስተምራለች
ዘዳግም 6:6-7
6 እኔም ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል በልብህ ያዝ።
7 ለልጆችህም አስተምረው፥ በቤትህም ስትቀመጥ፥ በመንገድም ስትሄድ፥ ስትተኛም፥ ስትነሣም ተጫወተው።

ምሳሌ 22:6
6 ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም።
ኤፌሶን 6:4
4 እናንተም አባቶች ሆይ፥ ልጆቻችሁን በጌታ ምክርና በተግሣጽ አሳድጉአቸው እንጂ አታስቆጡአቸው።
ትምህርቷ ሰፊ ነው ከቃሉ አንፃር ያለውን በነዚህ ጥቅሶች መሰረት ያደረገ ነው።

Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61567498017093&mibextid=ZbWKwL
Telegram
https://t.me/+AqjPGNRFvlEyMmFk
Youtube
https://youtube.com/?si=fwcZPawNrwOD_thg
Tiktok
https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1&sender_device=pc
Instagram
https://www.instagram.com/hawassaalamurafullgospelchurch/
Follow, Like, Share በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ፡፡

ቀን 09/09/18አመታዊ የልጆች ኮንፈረንስ 👉🏿ፀሎት በወንድም ነፃነት ገዛኸኝ👉🏿አምልኮ:- በቤተክርስቲያኒቱ የአምልኮ መሪዎች👉🏿መዝሙር :-በልጆች መዘምራን👉🏿የእግዚአብሄር ቃል :-በፓስተር ...
17/05/2026

ቀን 09/09/18
አመታዊ የልጆች ኮንፈረንስ
👉🏿ፀሎት በወንድም ነፃነት ገዛኸኝ
👉🏿አምልኮ:- በቤተክርስቲያኒቱ የአምልኮ መሪዎች
👉🏿መዝሙር :-በልጆች መዘምራን
👉🏿የእግዚአብሄር ቃል :-በፓስተር ዘሩባቤል ሙሉ ጌታ
▶️ርዕስ:-የአይነተኛ ወላጅ ማንነት
▶️የንባብ ክፍል:
👉ማቲ 18፤6 :-በእኔም ከሚያምኑ ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ሁሉ፥ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ይሻለው ነበር።

👉ቲቶ 2፣7 :-የሚቃወም ሰው ስለ እኛ የሚናገረውን መጥፎ ነገር ሲያጣ እንዲያፍር፥ በነገር ሁሉ መልካምን በማድረግህ ምሳሌ የሚሆን ራስህን አሳይ፤ በትምህርትህም ደኅንነትን፥ ጭምትነትን፥ ጤናማና የማይነቀፍ ንግግርን ግለጥ።

👉በተግባር ምሳሌ መሆንን ለልጆቻችን ማሳየት አለብን ወላጅ መሆን ማለት መናገር ብቻ ሳይሆን የመጀመሪያ ምሳሌ መሆን ነው።
# ወላጅ ለልጅ የሚሰጠው መርዝ ማለት "እኔ የምልህን አድርግ እንጂ እኔ የማደርገውን ነገር አታድርግ "የሚል ከሆነ ነው።

👉 ወላጆች ለልጆቻቸው የሚሰጡት ትዕዛዝ ሳይሆን ተግባር ነው ዋናው ትምህርት።
👉 አርአያነት የንግግር ውጤት ሳይሆን የኑሮ ውጤት ነው።
👉ለትምህርታቸው ስጋት የመንከፍለውን ዋጋ ያህል ለመንፈሳዊ ሂወታቸው የምንከፍለው ዋጋ ሊኖር ይገባል።

❇️በመፅሀፍ ቅዱሳችን ያሉ ወላጆች እንመልከት።

1️⃣ሉቃስ 15 ላይ ያለው ወላጅ :- ይህ ወላጅ የማያቋርጥ ፍቅርና የይቅርታ ልብ ያለው አርአያ ወላጅ ነው። ይሄ አባት ርህራሄን ከክብር ያስቀድማል። ልጁ ካደረገበት ነገር በላይ ርህራሄው ይቀድማል። እናም ዕለት ዕለት ይመጣል ብሎየሚጠብቅ አባትም ነው።

2️⃣እዩብ :-አርአያ በመሆን ለልጆቹ በእግዚያብሄር ፊት የሚቆም መልካም አባት ነው።

3️⃣ዳዊት :- 2ተኛ ሳሙኤል 13 ፍትሀዊነት የጎደለው አባት ነበር የዳዊት ዝምታና ግዴለሽነት የልጆቹን ሂወት ሲያመሰቃቅል እንመለከታለን።
4️⃣ ኤሊ:- ተገቢ ያልሆነ ዝምታና ርህራሄ ነበረበት። ከጥፋት የማይመልስ ፍቅር መጨረሻው ጥፋት ነው።

5️⃣ ርብቃ :- በልጆች መካከል አድሎየምታደረወግ ወላጅ ነበረች።

6️⃣ ሀና :- የፀሎትና የቃልኪዳን ወላጅ ምሳሌ ናት።
7️⃣ የጢሞትዮስ ወላጆች :- የትውልድ ቅብብሎሽ የሚታይበት ቤተሰብ ነው ጢሞቲዎስ ለወላጆቹ የወረሰው የፍቅር ቅብብሎሽ እንዳለው እንመለከታለን።

❇️የወላጅነት ምሰሶ ምንድናቸው።
1️⃣ግልፀኝነት :-ወላጆች ለልጆቻችን ንግግር እና የምናደርገው ነገር ግልፅ መሆን አለበት።
2️⃣መገኘት :-ለልጆች ጊዜ መስጠት
3️⃣ፍቅርና ስነ ስርዓት : ያለ ፍቅር የሚሰጥ ስነ ስርዓት አመፅ ነው።
4️⃣አድማጭነት :- ልጆችን በሚገባ ማዳመጥ ከወላጆች ይጠበቃል።
5️⃣ታማኝነት :- ለልጆቻችን ታማኝ መሆን ቃል ከገባንም ለዛ ቃል ታመመኝ መሆን ይገባናል።
#ማጠቃለያ:- ወላጅነት የማያልቅ ግንባታ ነው።
#ልጆችን ማሳደግ ማለት እራሰን መልሶ ማሳደግ ማለት ነው።

Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61567498017093&mibextid=ZbWKwL
Telegram
https://t.me/+AqjPGNRFvlEyMmFk
Youtube
https://youtube.com/?si=fwcZPawNrwOD_thg
Tiktok
https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1&sender_device=pc
Instagram
https://www.instagram.com/hawassaalamurafullgospelchurch/

Follow, Like, Share ስላደረጋችሁ ተባረኩ፡፡

"፤ ነገር ግን ኢየሱስ። ሕፃናትን ተዉአቸው፥ ወደ እኔም ይመጡ ዘንድ አትከልክሉአቸው፤ መንግሥተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉ ናትና አለ፤ " (የማቴዎስ ወንጌል 19: 14) በሚል መሪ ጥቅስ በተዘ...
17/05/2026

"፤ ነገር ግን ኢየሱስ። ሕፃናትን ተዉአቸው፥ ወደ እኔም ይመጡ ዘንድ አትከልክሉአቸው፤ መንግሥተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉ ናትና አለ፤ "
(የማቴዎስ ወንጌል 19: 14) በሚል መሪ ጥቅስ በተዘጋጀው አመታዊ የልጆች ኮንፍራስ በ08/09/2018 ዓ.ም(ዕለተ ቅዳሜ) በጠዋት ፈረቃ ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሪያለው በሚል ርዕሰ ዕድሚያቸው ከ4_8 ዓመት ላሉ ልጆች የተዘጋጀ ትምህርት ሲሆን ቅዳሜ ከሰዓት ዕድሜያቸው ከ8_12ዓመት ላሉ ልጆች ''እራስን መግዛት' በሚል ርዕሰ የተዘጋጀ ትምህርት ሲሆን በሁለቱም ፈረቃ ከልጆች ጋር የተለያዩ መርሐ ግብሮች ተደርጓል።

የእሁድ አምልኮቀን :- 2/9/2018 ዓ.ምፀሎት  :- ፓስተር መርሻ ገብሬአምልኮ :- የቤተክርስቲያን አምልኮ መሪዎች ዝማሬ:- ናዝራዊ መዘምራን የእግዚአብሔር ቃል :- አገልጋይ ወርቅዬ ተስ...
10/05/2026

የእሁድ አምልኮ
ቀን :- 2/9/2018 ዓ.ም
ፀሎት :- ፓስተር መርሻ ገብሬ
አምልኮ :- የቤተክርስቲያን አምልኮ መሪዎች
ዝማሬ:- ናዝራዊ መዘምራን
የእግዚአብሔር ቃል :- አገልጋይ ወርቅዬ ተስፋ
ርዕሰ :- በከባድ ችግር ዉስጥ ሆናችሁ እግዚአብሔር ታመሰግናላችሁ ወይ ?
የንባብ ክፍል :- ሉቃስ 1:5-12

⁵ በይሁዳ ንጉሥ በሄሮድስ ዘመን ከአብያ ክፍል የሆነ ዘካርያስ የሚባል አንድ ካህን ነበረ፤ ሚስቱም ከአሮን ልጆች ነበረች፥ ስምዋም ኤልሳቤጥ ነበረ።
⁶ ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ።
⁷ ኤልሳቤጥም መካን ነበረችና ልጅ አልነበራቸውም፤ ሁለቱም በዕድሜያቸው አርጅተው ነበር።
⁸ እርሱም በክፍሉ ተራ በእግዚአብሔር ፊት ሲያገለግል፥
⁹ እንደ ካህናት ሥርዓት ወደ ጌታ ቤተ መቅደስ ገብቶ ለማጠን ዕጣ ደረሰበት።
¹⁰ በዕጣንም ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ በውጭ ቆመው ይጸልዩ ነበር።
¹¹ የጌታም መልአክ በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ታየው።
¹² ዘካርያስም ባየው ጊዜ ደነገጠ፥ ፍርሃትም ወደቀበት።
🔸ዘራቸዉ የካህን ቤተሰብ ናቸዉ አሮን ካህን ነበረ
ሦስት ነገር እናያለን ከዚህ ታሪክ
1,ዘካርያስ እና ሚስቱ በእግዚአብሔር ህግጋት ያለነቀፋ በፅድቅ ሚያገለግሉ ናቸዉ
2, ልጅ አልነበራቸውም
3,አርጅተዋል
በፅድቅ÷ በቅድስና ነዉ ያረጁት
▪️ከወጣትነት አንስቶ እስከ እርጅና ከቤተክርስቲያን ያልጠፋ ያለጉረመረሙ ሰወች ነበሩ
▪️ዘካርያስ መሰዉያ ላይ ገብቶ እግዚአብሔር ማገልገል የእለት እለት ኑሮ ነዉ
🔸ቤተክርስቲያን ወደ እዉነተኛ መሰዊያ ካልተመለሰች የእግዚአብሔር ክብር ማየት አትችልም
🔸በሚገጥሙን ፈተናዎች ሁሉ ከመሰዉያ አላነሳም የሚል ትዉልድ አሁን አለ ወይ ?
▪️እግዚአብሔር እጃችን ያስቀመጠው እጣን አለ እንድናጥንለት ሚፈለገው እንድንሰዋለት ሚፈልገው
▪️ጥያቄ የተሞላ ፃድቅ ሰዉ ነበር
ጥያቄ ያለበት እግዚአብሔር የሚታዘዝ ሰዉ ነበር
▪️ዘካርያስ ህይወት ዉስጥ አገልግሎት ይከበራል
በመጨረሻ ፀሎቱን የሚመልስ መልአክ ቆመለት
እኛም ይሄን እናስብ
🔸መሰዉያ ማስከበር
🔸መሰዉያ ማየት
🔸በመሰዉያ መሆን አለብን
▪️በመጨረሻም
በእግዚአብሔር ፊት ስንሆን ፀሎታችን ይቀየራል በማጉረምረም ሳይሆን ፊቱን በመፈለግ በትግስት በመታዘዝ ሆነን መሰዉያ ፊት እንገኝ
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61567498017093&mibextid=ZbWKwL
Telegram
https://t.me/+AqjPGNRFvlEyMmFk
Youtube
https://youtube.com/?si=fwcZPawNrwOD_thg
Tiktok
https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1&sender_device=pc
Instagram
https://www.instagram.com/hawassaalamurafullgospelchurch/

Follow, Like, Share ስላደረጋችሁ ተባረኩ፡፡

09/05/2026
25/08/2018የእሁድ አምልኮ ፕሮግራም ፀሎት:-ዶክተር አሰፍ ዩሐንስ አምልኮ:-በቤተክርስቲያኒቱ አምልኮ መሪዎች ዝማሬ:- ማራናታ መዘምራን የእግዚአብሔር ቃል :-በወንድም መሰለ ቦጋለ ርዕሰ...
03/05/2026

25/08/2018
የእሁድ አምልኮ ፕሮግራም
ፀሎት:-ዶክተር አሰፍ ዩሐንስ
አምልኮ:-በቤተክርስቲያኒቱ አምልኮ መሪዎች
ዝማሬ:- ማራናታ መዘምራን
የእግዚአብሔር ቃል :-በወንድም መሰለ ቦጋለ
ርዕሰ:-ኢየሱስን ማወቅ እና መነካት

የሐዋርያት ሥራ 9:1-8
¹ ሳውል ግን የጌታን ደቀ መዛሙርት እንዲገድላቸው ገና እየዛተ ወደ ሊቀ ካህናት ሄደ፥
² በዚህ መንገድ ያሉትንም ሰዎች ወንዶችንም ሴቶችንም ቢያገኝ፥ እያሰረ ወደ ኢየሩሳሌም ያመጣቸው ዘንድ በደማስቆ ላሉት ምኵራቦች ደብዳቤ ከእርሱ ለመነ።
³ ሲሄድም ወደ ደማስቆ በቀረበ ጊዜ ድንገት በእርሱ ዙሪያ ከሰማይ ብርሃን አንጸባረቀ፤
⁴ በምድርም ላይ ወድቆ ሳለ። ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ ሰማ።
⁵ ጌታ ሆይ፥ ማን ነህ? አለው። እርሱም። አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል አለው።
⁶ እየተንቀጠቀጠና እየተደነቀ። ጌታ ሆይ፥ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ? አለው። ጌታም። ተነሥተህ ወደ ከተማ ግባና ታደርገው ዘንድ የሚያስፈልግህን ይነግሩሃል አለው።
⁷ ከእርሱም ጋር በመንገድ የሄዱ ሰዎች ድምፁን እየሰሙ ማንን ግን ሳያዩ እንደ ዲዳዎች ቁሙ።
⁸ ሳውልም ከምድር ተነሣ፥ አይኖቹም በተከፈቱ ጊዜ ምንም አላየም፤ እጁንም ይዘው እየመሩ ወደ ደማስቆ አገቡት።

✅በዚህ ክፍል ውሰጥ አራት አካላትን እንመለከታለን

1. አሳዳጁን ሳኦልን
2. የሚሰደዱትን ቅዱሳንን
3. ሊቀ ካህናቱን
4. የነገሩ ባለቤት የሆነውን ኢየሱስን

✅ደብዳቤ እንዲሰጥ ያደረገው ዋናው ምክንያት ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ብለው በመስበካቸው ነው። ሐዋርያት 25:18-27
✅ኢየሱስን ማወቅ ከብዙ ነገር ይጠብቀናል ።

ኢየሱስ የበራለት ሰው በሕይወቱ ምን ይሆናል:-

1. ራሱን ለእግዚአብሔር ያስገዛል
2. ለበራለት እውነት መኖር ይጀመራል
3. የበራለትን እውነት ለሌሎች መናገር ይጀመራል
4. ለበራለት እውነት ይሞታል

ማጠቃለያ
-ኢየሱስን ማወቅ ከብዙ ነገር ይጠብቀናል
-ኢየሱስ ገብቶን አገልግሎት ከጀመርን ኢየሱስን እየሰበክን እንጨርሳለን
-ኢየሱስ ሲነካን ምልልሳችን: ንግግራችን እና አድራሻችን ይቀየራል ።
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61567498017093&mibextid=ZbWKwL
Telegram
https://t.me/+AqjPGNRFvlEyMmFk
Youtube
https://youtube.com/?si=fwcZPawNrwOD_thg
Tiktok
https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1&sender_device=pc
Instagram
https://www.instagram.com/hawassaalamurafullgospelchurch/

Follow, Like, Share በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ፡፡

ቀን:- 18/08/18የእሁድ አምልኮ ፕሮግራም ፀሎት:- ወ/ም ተስፉ ኃ/ማርያምአምልኮ:- በቤ/ክቱ የአምልኮ መሪዎችበዝማሬ:- ሮቦት ኳየር የእግዚአብሔር ቃል:- በፓስተር ደረጀ ዳግምርዕስ:- ...
27/04/2026

ቀን:- 18/08/18
የእሁድ አምልኮ ፕሮግራም
ፀሎት:- ወ/ም ተስፉ ኃ/ማርያም
አምልኮ:- በቤ/ክቱ የአምልኮ መሪዎች
በዝማሬ:- ሮቦት ኳየር
የእግዚአብሔር ቃል:- በፓስተር ደረጀ ዳግም
ርዕስ:- ያልተጠበቀው ምርጫ
ማርቆስ 11÷1-10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ወደ ኢየሩሳሌምም ከደብረ ዘይት አጠገብ ወዳሉቱ ወደ ቤተ ፋጌና ወደ ቢታንያ በቀረቡ ጊዜ፥ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን ልኮ፦
² በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ፥ ወዲያውም ወደ እርስዋ ገብታችሁ ከሰው ማንም ገና ያልተቀመጠበት ውርንጫ ታስሮ ታገኛላችሁ፤ ፈትታችሁ አምጡልኝ።

🔸ንጉስ እና መሪ በፈረስ እና በሰረገላ ወደ ከተማ በሚገባበት ጊዜ ጌታ እየሱስ ግን ወደ እየሩሳሌም ለመግባት የታሰረችውን ያቺን ትንሽ ውርንጫ መረጠ ይህም እጅግ ያልተጠበቀ ምርጫ ነበር

🔸በውርንጭላ ወደ ከተማዋ የገባበት አላማ
“አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል።”
— ዘካርያስ 9፥9-10
1.የትንቢቱ ቃል ይፈፀም ዘንድ
2.በትህትና የሚመጣ የሰላም ንጉስ መሆኑን ለመግለጽ
3.የታሰሩትን ለመፍታት እና ለታላቅ ክብር ለማብቃት መሆኑን ለማሳየት
4.እራሱን የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ለአለም ለመግለጥ
5.ለፋሲካ የሚታረደው በግ ምሳሌ መሆኑን ለመግለጽ - ታልፎ ለመሰጠት 4 ቀን ሲቀረው ነበር ይህ የሆነው

🔸እኛስ ምን እንማራለን
🔻ዛሬም ጌታ በተለያየ እስራት ያሉትን ካሉበት ሁኔታ ያወጣቸዋል
▪️የታሰረብንን የተያዘብንን ነገር ባለበት ሁኔታ ያውቃል ይፈታውማል
🔻የታሰሩትን ለመፍታት እና ለመጠቀም የማንንም ይሁንታ አይፈልግም
▪️እግዚአብሔር በነገራችን ላይ ጣልቃ ሲገባ ማንም ተከራካሪ ሊያስቆም አይችልም
🔻እስራትን የሚበጥሰው እንዲሁ እንድንቀመጥ ሳይሆን ተልዕኮውን እንድንሸከም ነው
▪️ተልዕኮውን ስንሸከም የእግዚአብሔር ክብር በእኛ ላይ ይገለጣል
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61567498017093&mibextid=ZbWKwL
Telegram
https://t.me/+AqjPGNRFvlEyMmFk
Youtube
https://youtube.com/?si=fwcZPawNrwOD_thg
Tiktok
https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1&sender_device=pc
Instagram
https://www.instagram.com/hawassaalamurafullgospelchurch/

Follow, Like, Share በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ

11/08/2018የእሁድ አምልኮ ፕሮግራም ፀሎት በወንድም አማረ አክሊሉ አምልኮ :-በአምልኮ መሪዎች የእግዚአብሔር ቃል ፓሰተር ሰለሞን ደሳለኝርዕሰ:-እግዚአብሔር ሲሰራ ማንም ሊከለክለው    ...
19/04/2026

11/08/2018
የእሁድ አምልኮ ፕሮግራም
ፀሎት በወንድም አማረ አክሊሉ
አምልኮ :-በአምልኮ መሪዎች
የእግዚአብሔር ቃል ፓሰተር ሰለሞን ደሳለኝ
ርዕሰ:-እግዚአብሔር ሲሰራ ማንም ሊከለክለው አይችልም

የሐዋርያት ሥራ 11:1-18
¹ ሐዋርያትና በይሁዳም የነበሩት ወንድሞች አሕዛብ ደግሞ የእግዚአብሔርን ቃል እንደ ተቀበሉ ሰሙ።
² ጴጥሮስም ወደ ኢየሩሳሌም በወጣ ጊዜ ከተገረዙት ወገን የሆኑት ሰዎች ከእርሱ ጋር ተከራክረው።
³ ወዳልተገረዙ ሰዎች ገብተህ ከእነርሱ ጋር በላህ አሉት።
⁴ ጴጥሮስ ግን ከመጀመሪያው ጀምሮ በተራ ገለጠላቸው እንዲህም አለ።
⁵ እኔ በኢዮጴ ከተማ ስጸልይ ሳለሁ ተመስጬ ራእይን አየሁ፤ ታላቅ ሸማ የመሰለ ዕቃ በአራት ማዕዘን ተይዞ ከሰማይ ወረደና ወደ እኔ መጣ፤
⁶ ይህንም ትኵር ብዬ ስመለከት አራት እግር ያላቸውን የምድር እንስሶች አራዊትንም ተንቀሳቃሾችንም የሰማይ ወፎችንም አየሁ።
⁷ ጴጥሮስ ሆይ፥ ተነሣና አርደህ ብላ የሚለኝንም ድምፅ ሰማሁ።
⁸ እኔም። ጌታ ሆይ፥ አይሆንም፤ ርኵስ ወይም የሚያስጸይፍ ከቶ ወደ አፌ ገብቶ አያውቅምና አልሁ።
⁹ ሁለተኛም። እግዚአብሔር ያነጻውን አንተ አታርክሰው የሚል ድምፅ ከሰማይ መለሰልኝ።
¹⁰ ይህም ሦስት ጊዜ ሆነ እንደ ገናም ሁሉ ወደ ሰማይ ተሳበ።
¹¹ እነሆም፥ ያን ጊዜ ሦስት ሰዎች ከቂሣርያ ወደ እኔ ተልከው ወዳለሁበት ቤት ቀረቡ።
¹² መንፈስም ሳልጠራጠር ከእነርሱ ጋር እሄድ ዘንድ ነገረኝ። እነዚህም ስድስቱ ወንድሞች ደግሞ ከእኔ ጋር መጡ ወደዚያ ሰውም ቤት ገባን።
¹³ እርሱም መልአክ በቤቱ ቆሞ እንዳየና። ወደ ኢዮጴ ሰዎች ልከህ ጴጥሮስ የተባለውን ስምዖንን አስመጣ፤
¹⁴ እርሱም አንተና የቤትህ ሰዎች ሁሉ የምትድኑበትን ነገር ይነግርሃል እንዳለው ነገረን።
¹⁵ ለመናገርም በጀመርሁ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ለእኛ ደግሞ በመጀመሪያ እንደ ወረደ ለእነርሱ ወረደላቸው።
¹⁶ ዮሐንስ በውኃ አጠመቀ እናንተ ግን በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ ያለውም የጌታ ቃል ትዝ አለኝ።
¹⁷ እንግዲህ እግዚአብሔር በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ላመነው ለእኛ ደግሞ እንደ ሰጠን ያን ስጦታ ለእነርሱ ከሰጠ፥ እግዚአብሔርን ለመከልከል እችል ዘንድ እኔ ማን ነበርሁ?
¹⁸ ይህን በሰሙ ጊዜም ዝም አሉና። እንኪያስ እግዚአብሔር ለአሕዛብ ደግሞ ለሕይወት የሚሆን ንስሐን ሰጣቸው እያሉ እግዚአብሔርን አከበሩ።

ይህን ክፍል ሰንመለከት አራት ነገሮችን መረዳት እንችላለን :-
1. ለአህዛብ የመዳንን እድል የሰጠው እግዚአብሔር ነው
2. ሐዋርያው ጴጥሮስ ለአህዛብ የደህንነት መልዕክት እንዲያስተላልፉ የተላከ መልዕክተኛ ነው።የሰራው ባለቤት ግን እግዚአብሔር ነው ።
✅የመልዕክቱ ዋና ማዕከል ኢየሱስ ነው።
✅የኢየሱስ ሰም ለሰዎች ምህረት እና ይቅርታን ያስገኛል ።
3. እድል የተሰጣቸው ሰዎች ከእግዚአብሔር የሆነውን ለመስማት ተሰበሰቡ ።
✅ከእግዚአብሔር የሆነውን የተሰበሰቡ ሰዎች የእግዚአብሔርን በረከት ያገኛሉ ።
4. እግዚአብሔር አህዛብን መቀበሉን ያረጋገጠው መንፈሱን በመሰጠት ነው።ሐዋ 11:15

ማጠቃለያ
• እግዚአብሔር ዛሬም በስራ ላይ ነው።
• እግዚአብሔር መልዕክቱን የሚያደርሱትን መልዕክተኞችን ይፈልጋል ።
• ያኔ መንፈሱን ያፈሰሰ እግዚአብሔር ዛሬም ያፈሳል ።

Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61567498017093&mibextid=ZbWKwL
Telegram
https://t.me/+AqjPGNRFvlEyMmFk
Youtube
https://youtube.com/?si=fwcZPawNrwOD_thg
Tiktok
https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1&sender_device=pc
Instagram
https://www.instagram.com/hawassaalamurafullgospelchurch/

Follow, Like, Share በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ፡

የእሁድ አምልኮቀን :- 4/8/2018 ዓ.ምፀሎት  :-ወንድም  ፍቅሩ ፀጋዬ አምልኮ :- በወንድም እንግዳወርቅ ሰይፉዝማሬ :-  የቤተክርስቲያኒቱ አራቱም መዘምራን የእግዚአብሔር ቃል :- ፓስ...
12/04/2026

የእሁድ አምልኮ
ቀን :- 4/8/2018 ዓ.ም
ፀሎት :-ወንድም ፍቅሩ ፀጋዬ
አምልኮ :- በወንድም እንግዳወርቅ ሰይፉ
ዝማሬ :- የቤተክርስቲያኒቱ አራቱም መዘምራን
የእግዚአብሔር ቃል :- ፓስተር ወልዴ ኬሬ
ርዕሰ :- ኢየሱስ ይመጣል
የንባብ ክፎሎች ሐዋርያት ስራ 1:8-11
ማርቆስ 14:61-62
ሉቃስ 21:27
ዮሐንስ 14:1-3

⁸ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አለ።
⁹ ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው።
¹⁰ እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኵር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ፥ እነሆ፥ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች በአጠገባቸው ቆሙ፤
¹¹ ደግሞም፦ የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።
▪️ሐዋርያት 1:8 ላይ ሊያደርጉት የሚገባቸዉን ነዉ የነገራቸው
ትዕዛዙ ከይሁዳ :ከሰማሪያ : እስከምድር ዳር ድረስ እንዲሄዱ ነዉ ያሳሰባቸው
▪️ቀድሞ የነገራቸውን ቃል እየነገራቸው እያስታወሳቸዉ አብሯቸው ቆየ
🔻 የጌታ ወደ ሰማይ መዉጣት በአካል የሚታይ ነበር ሚስጥራዊ አይደለም
▪️ደመና ከይናቸዉ ሰዉራ ተቀበለችሁ::
ኢየሱስን የሚቀበል ደመና በሰማይ እንዳለ ያመለክታል
▪️ደመና ካይናቸዉ ሲሰዉረዉ ፈተና ነዉ የገጠማቸው
* ቆመዉ ነበር ግራ ገብቷቸዉ መልአኩ ሲመጣ ግን
ተንቀሳቀሱ አላቸው ወደ አገልገሎት ተመለሱ አላቸው ወደተሰጣቸዉ ተልዕኮ
▪️የኢየሱስ መሄድ ማረግ እነሱን ሐዋርያቱን አንቀሳቀሳቸዉ
▪️የኢየሱስ ማንነት
ኢሳያስ 53:1 ጀምሮ ያለዉ
ተጎሳቁሎ የነበረዉ : ተቸግሮ የነበረዉ ያዉ ኢየሱስ ነዉ ተመልሶ ይመጣል
▪️የተናቀዉ በሰዉ የተጠላ ያዉ ኢየሱስ ፍቅር የሆነ አምላክ
▪️ጨካኞች ሲጫወቱበት የነበረው የእኛ ብሎ እራሱን የሰጠዉ ያዉ ኢየሱስ ነዉ ምንጠብቀው
# የመመለሻ መንገዶች
1,በሚታይ ሁኔታ ይመጣል
2,በአካል ይመጣል
3,የከበረ በደመና ዉስጥ ይመጣል
“እነሆ፥ ከደመና ጋር ይመጣል፤ ዓይንም ሁሉ የወጉትም ያዩታል፥ የምድርም ወገኖች ሁሉ ስለ እርሱ ዋይ ዋይ ይላሉ። አዎን፥ አሜን።”
— ራእይ 1፥7
▪️የመምጣቱ አስፈላጊነት
* ደሞዝ ስላለን የምናገለግለው አገልግሎት ክፍያ ስላለ ነዉ
* በድፍረት እንድንሰራ ያነሳሳናል ምፅአቱ
ሐዋርያት ስራ 4:31
▪️አሁን ምንኖረው በአስቸጋሪ ሁኔታ ነው እርሱ ሲመጣ ግን ሁሉ ይለወጣል
🔻ኢየሱስ ስለሚመጣ እኛ ምን እናድርግ
1,በንቃት እንጠብቅ ማቴዎስ 25:13 /24:42
ሳንዝል ዛሬ ብቻ እንደሚኖር ሰዉ እንኑር
2 ጴጥሮስ 3:10
2,ተዘጋጅተን እንኑር ማቴዎስ 24:44
ዕብ 10:37
3,በፍቅር በመዋደድ በመያያዝ እንኑር
ዮሐንስ 13:34
4,ህብረት በማረግ መንፈሳዊ ህብረቶች
ዕብራውያን 10:24
5,ቃሉን በማጥናት እንጠብቅ ቆላሲያስ 3:16
6,በፀሎት በትጋት እንጠብቅ
7,የወንጌል ተልዕኮ በማከናወን እንጠብቅ
ማቴዎስ 28:20 ማርቆስ 16:15
▪️ማጠቃለያ
ጌታ ይመጣል በንቃት ተዘጋጅተን በመዋደድ በህብረት እና ቃሉን በማጥናት በፀሎት እንጠብቅ ኢየሱስ ይመጣል :: ማራናታ
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61567498017093&mibextid=ZbWKwL
Telegram
https://t.me/+AqjPGNRFvlEyMmFk
Youtube
https://youtube.com/?si=fwcZPawNrwOD_thg
Tiktok
https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1&sender_device=pc
Instagram
https://www.instagram.com/hawassaalamurafullgospelchurch/

Follow, Like, Share ስላደረጋችሁ ተባረኩ፡፡

ቀን:- 27/07/18የእሁድ አምልኮፀሎት:- በወንድም ናኦድ ቦጋለአምልኮ:- በቤተክርስቲያኒቱ የአምልኮ መሪዎችየእግዚአብሔር ቃል:- በዶ/ር ተመስገን ለአርዕስ:-ጤናማ ቤተሰብ🔸እግዚአብሔር የሚ...
05/04/2026

ቀን:- 27/07/18
የእሁድ አምልኮ
ፀሎት:- በወንድም ናኦድ ቦጋለ
አምልኮ:- በቤተክርስቲያኒቱ የአምልኮ መሪዎች
የእግዚአብሔር ቃል:- በዶ/ር ተመስገን ለአ
ርዕስ:-ጤናማ ቤተሰብ

🔸እግዚአብሔር የሚጠነቅቅበት 2 ትላልቅ ተቋም ቤተክርስቲያን እና ቤተሰብ ምክኒያቱም ቤተሰብ እናት እና አባትነትን የምንማርበት ፍቅርን የምንለማመድበት ስለሆነ

🔸ስለቤተሰብ ከመጀመሪያው ቤተሰብ እንመልከት
ዘፍጥረት 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፥ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ።
⁷ የሁለቱም ዓይኖች ተከፈቱ፥ እነርሱም ዕራቁታቸውን እንደ ሆኑ አወቁ፤ የበለስንም ቅጠሎች ሰፍተው ለእነርሱ ለራሳቸው ግልድም አደረጉ።


¹¹ እግዚአብሔርም አለው፦ ዕራቁትህን እንደ ሆንህ ማን ነገረህ? ከእርሱ እንዳትበላ ካዘዝሁህ ዛፍ በውኑ በላህን?
¹² አዳምም አለ፦ ከእኔ ጋር እንድትሆን የሰጠኸኝ ሴት እርስዋ ከዛፉ ሰጠችኝና በላሁ።
¹³ እግዚአብሔር አምላክም ሴቲቱን፦ ይህ ያደረግሽው ምንድር ነው? አላት። ሴቲቱም አለች፦ እባብ አሳተኝና በላሁ።

⭕️ኑሮአችን እየተዛባ እንደሆነ ቤተሰባችን እየተናጋ እንደሆነ የሚያሳዩ ምልክቶች

1.ሦስተኛ ወገን መስማት እና ጣልቃ ማስገባት ስንጀምር
2.አንዱ በአንዱ ማፈር ሲጀምር (መተፋፈር ሲመጣ) በሁለቱ መካከል አላስፈላጊ ሚስጢሮች ሲኖሩ እምነት ሲጠፋ
3.መካሰስ እና አላስፈላጊ መዋቀስ ሲጀመር

⭕️ልጆች እና ወላጆች ሊኖራቸው የሚገባ መልካም ልምምድ
1.ከልጆቻችሁ ጋር ትጫወታላቹ??
2.ከልጆቻችሁ ጋር ትፀልያላቹ?
3.ለልጆቻችሁ የእግዚአብሔር ቃል ታካፍላላቹ
4.ልጆቻችሁ የእግዚአብሔር ቃል ያካፍሏችኋል??
5.የግል ሚስጥራቹን ለልጆቻችሁ ታካፍላላቹ?
6.ልጆቻችሁ የግል ሚስጥራቸውን ያካፍሏችኋል?
7.ልጆቻችሁ ቢያጠፋ መተጥተው ተናግረው ይቅርታ ጠይቀው ያውቃሉ?
8.እናነተስ ልጆቻችሁን አሳዝናቹ ይቅርታ ጠይቃቹ ታውቃላቹ?
9.የልጆቻችሁን ውሎ ተከታትላቹ ታውቃላቹ?
10.ልጆቻችሁ ሲወጡ ባርካቹ ሸኝታቹ ታውቃላቹ?
ዘኍልቁ 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²³ ለአሮንና ለልጆቹ ንገራቸው፦ የእስራኤልን ልጆች ስትባርኩአቸው እንዲህ በሉአቸው፦
²⁴ እግዚአብሔር ይባርክህ፥ ይጠብቅህም፤
²⁵ እግዚአብሔር ፊቱን ያብራልህ፥ ይራራልህም፤
²⁶ እግዚአብሔር ፊቱን ወደ አንተ ያንሣ፥ ሰላምንም ይስጥህ።
²⁷ እንዲሁ ስሜን በእስራኤል ልጆች ላይ ያደርጋሉ፤ እኔም እባርካቸዋለሁ።

⭕️ማጠቃለያ
ጤናማ ቤተሰብ ጤናማ ትውልድ ያፈራል።ጠንካራ ቤተሰብ ጠንካራ ትውልድን ይገነባል።

Address

Hawassa
Hawassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hawassa Alamura Full Gospel Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share