16/08/2026
10/12/2018
የእሁድ አምልኮ ፕሮግራም
ፀሎት:- ፖሰተር ተሾመ ሞገሰ
አምልኮ :-በወንድም እንግዳወርቅ ሰይፉ
የእግዚአብሔር ቃል:-ፖሰተር መርሻ ገብሬ
ዘወትር በመሠዊያው ላይ እሳት ይነድዳል፤አይጠፋም ዘሌ 6፡ 8-13
ሉቃ 12፡49 በምድ ላይ እሳት ልጥል መጣሁአሁን የነደደ ከሆነ ዘንድ ም እፈልጋለሁ፡፡
መግቢያ
የዘሌዋውያን መጽሐፍ የሕግ ስብስብ ብቻ ሳይሆን፣ ቅዱሱእግዚአብሔር ከወደቀውና ከኃጢአተኛው ሰው ጋር እንዴትእንደሚገናኝና ሕዝቡም በቅድስና እንዴት ከእርሱ ጋር መኖርእንደሚችሉ የሚያሳይ ነው፡፡
የመጀመሪያውን የመሠዊያ እሳት ያቀጣጠለው እግዚአብሔርነበር (ዘሌ 9:24)።
ለካህናቱ የተሰጠው ዋነኛ ኃላፊነት የነደደው እሳት እንዳይጠፋእንጨት በመጨመር መንከባከብ እና ዘወትር እንዲነድ መጠበቅነው፡፡
«ዘወትር በመሠዊያው ላይ እሳት ይነድዳል፤ አይጠፋም»ትእዛዙ የብሉይ ኪዳን አምልኮ ማዕከል የሆነውን የመሥዋዕትህያውነት ያመለክታል። በመሠዊያው ላይ ያለው እሳትእንዳይጠፋ የካህናቱን ዕለታዊ ትጋትና ንቃት ይጠይቃል፡፡
1. የእግዚአብሔር ህላዌ፤ የምህረት እና ቅድስና መገለጫ
በብሉይ ኪዳን ታሪክ ውስጥ እሳት የእግዚአብሔርን ቅድስናናህላዌ የሚያሳይ ዋነኛ ምልክት ነው (ዘጸአት 3:2)፤
• በመሠዊያው ላይ ዘወትር የሚነደው እሳት እግዚአብሔርበህዝቡ መካከል ዘወትር እንዳለ የሚያሳይ ምስክር ነው።
• መሠዊያው የኃጢአት ማስተስረያና ከእግዚአብሔር ጋርየመታረቂያ ስፍራ ነው።
• እሳቱ ዘወትር መንደድ የእግዚአብሔር የምህረት ደጅ ዘወትርክፍት መሆኑን ነው።
2 . የካህናቱ የትጋትና የኃላፊነት ድርሻ
• እሳቱ እንዳይጠፋ ማድረግ ።
• ማለዳ ማለዳ እንጨት የመጨመር፡
እንጨት ደግሞ ለዕለቱ እሳት መቀጣጠያ የሚሆን አዲስመሥዋዕትና መታዘዝ ነው። ብዙ ጊዜ የመንፈሳዊ ህይወት ቅዝቃዜ ምክንያቱ በትናንት መንፈሳዊ ልምምድ (አመድ) ላይተቀምጠው አዲስ እንጨት (ዕለታዊ የቃልና የጸሎት ሕይወት) ማቅረብ ማቆም ነ
• የመሠዊያውን አመድ ማንሳት
አመድ ትናንት የተቃጠለውና አልፎ የሄደው መሥዋዕትፍሬ ነው። ትናንት የነደደው እሳት ዛሬ አመድ ሆኗል ። አዲስእሳት እንዲነድድ ከተፈለገ አመዱ መወገድ አለበት።
• የመሥዋዕቱን አካል የማዘጋጀት (ዘሌ6:12)። ይህ የሚያሳየውየእግዚአብሔር መንፈሳዊ ስጦታ በሰው በኩል በሚደረግትጋትና እንክብካቤ እንደሚጠበቅ ነው።
እግዚአብሔር በሰው ውስጥ ያስቀመጠው የፀጋ ስጦታእንዳይጠፋ የመንፈስ ቅዱስ እሳት ማቀጣጠል ይገባል፡፡
. በሰው ሰራሽ እሳት አለመተካት፡-
• የነደደው እሳት እንዳይጠፋ መጠበቅ እንጂ ሰው ሰራሽ እሳትማቀጣጠል አልተፈቀደም ፡፡
ያለጥንቃቄ በራሳቸው ተነሳስተው እሳት ያቀጣጠሉ ናዳብናአብድዩ በየራሳቸው ጥናውን ወስደው እሳት አደረጉበት በላዩምእጣን አኖሩበት በእግዚአብሔርም ፊት እርሱ ያላዘዛቸውንሌላእሳት አቀረቡ፡፡ ከእግዚአብሔርም ፊት እሳት ወጥቶ በላቸው በእግዚአብሔርም ፊት ሞቱ / ዘሌ 10፡1-2 ፡፡
ከእግዚአብሔር እንደሆነ በማስመሰል የራስን አሳብ በእግዚአብሔር ስም መናገር ወይንም ማድረግ በእገዚአብሔር ፊት ያስጠይቃል፡፡ ስለሆነም ሁሉን ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ ነው፡፡
ሀ. ከብሉይ ኪዳን
• ዘሌዋውያን 9:24 – "እሳትም ከእግዚአብሔር ፊት ወጣች፥በመሠዊያውም ላይ ያለውን የሚቃጠለውን መሥዋዕትናስቡን በላች..."
• ነገሥት 18: 38 – "የእግዚአብሔርም እሳት ወደቀች፥የሚቃጠለውንም መሥዋዕትና እንጨቱን ድንጋዮቹንምአፈርህንም በላች. "
• ኢሳይያስ 6: 6-7 – "ከሰራፌልም አንዱ በመቆንጠጫከመሠዊያው የወሰደውን ፍም በእጁ ይዞ ወደ እኔ በረረ፤አፌንም ዳሰሰበት..
ለ. ከአዲስ ኪዳን ከጥላ ወደ እውነት፡
የብሉይ ኪዳን መሠዊያና እሳት የአዲስ ኪዳን ታላቅ እውነት እና ጥላ ናቸው።
• መሠዊያው፡ በብሉይ ኪዳን ከነሐስ እና የድንጋይ ወይምየቦርድ መሠዊያ ነበረ፤ በአዲስ ኪዳን
ግን የክርስቶስ መስቀልና የአማኙ ልብ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያመሠዊያ ሆኗል 1ቆሮ 3፡ 17 ።
በአዲስ ኪዳን በክርስቶስ ኢየሱስ አምነው የዳኑ ሁሉ ካህናቶች ናቸው 1ጴጥሮስ 2፡9 �መሥዋዕቱ፡ በብሉይ ኪዳን የእንስሳት ደም ነበረ፤ በአዲስ ኪዳንክርስቶስ አንድ ጊዜ ፈጽሞ ራሱን ያቀረበው ፍጹም መሥዋዕትነው / ዕብ 5፡ 7 ።
• እሳቱ፡ በብሉይ ኪዳን በድንኳኑ ውስጥ ይነድድ የነበረውእሳት፤ በአዲስ ኪዳን በበዓለ ጴንጤቆስቴ ወርዶ በቤተክርስቲያንና በአማኞች ልብ ውስጥ የሚነድደው መንፈስቅዱስ ነው።
• የሐዋርያት ሥራ 2:3-4 – "የእሳት ነበልባል የሚመስሉየተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በእያንዳንዳቸው ላይተቀመጡባቸው። በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው .."
• ሮሜ 12:1፤ 11 – "ሰውነታችሁን ሕያው፥ ቅዱስ፥እግዚአብሔርንም ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት አድርጋችሁታቀርቡ ዘንድ... በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ፤ ለጌታ ተገዙ።"
• 2 ጢሞቴዎስ 1:6 – የእግዚአብሔርን ስጦታ እንድታነሣሣ እንድታቀጣትል አሳስብሃለሁ ይላል ።
• 1 ተሰሎንቄ 5:19 – "መንፈስን አታጥፉ።
ማጠቃለያ
እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠው ትእዛዝ "እሳቱ ዘወትርይነድዳል፤ አይጠፋም" የሚል ከሆነ፣
እሳት እንዳይጠፋ አራት ዋና ዋና ነገሮች ያስፈልጋሉ፡
• አየር (የመንፈስ ቅዱስ ህልውና)፡ ያለ መንፈስ ቅዱስ እርዳታሃይማኖታዊ ሥርዓት ብቻ ይሆናል፡፡
• እንጨት (የእግዚአብሔር ቃልና ጸሎት)፡ በየዕለቱ ቃሉንማብላትና በጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር እሳቱንያቀጣጥለዋል።
• አመዱን ማንሳት (ንሰሐ)፡ ክፉ ምኞት፣ ቂም፣ አድመኝነትን እና አጠቃላይ የኃጢአት ልምምድ ማስወገድ፡፡
• መሥዋዕት ማቅረብ እሳት ያለ መሥዋዕት የሚበላው አጣሁብሎ ይጠፋል። ሕይወታችንን ሙሉ በሙሉ ለጌታ ፈቃድአሳልፈን ስንሰጥ እሳቱ ዘወትር ይነድዳል ሮሜ 12፡1-2፡፡
ተግባራዊ እርምጃዎች
1. መሠዊያችንን ማደስ የፈረሰውን የግልና የቤተሰብ ጸሎትመሠዊያ እንደገና አድሱ ። እሳቱ እንዲነድ መሰዊያውን / ልባችንን/ ማደስ፡፡
2. ከሕይወታችን አመድ የሆነውን ማስወገድ፡- በትናንትስኬት ወይም በትናንት መንፈሳዊ ልምምድ ላይ ብቻ አለመደገፍ ። እንዲሁም በልብ ውስጥ የተቀመጠውንየቂም፣ የኃጢአትና የዓለማዊነት አመድ በንሰሐ ማስወገድ ፡፡
3. በየቀኑ የእግዚአብሔርን ቃል በማንበብ፣ በማሰላሰልናበመታዘዝ አዲስ እንጨት በመሠዊያው ላይ በመጨመር ማቀጣጠል ። እሳቱ እንዳይጠፋ የማድረግ ኃላፊነት የየግላችን ነው።
Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61567498017093&mibextid=ZbWKwL
Telegram
https://t.me/+AqjPGNRFvlEyMmFk
Youtube
https://youtube.com/?si=fwcZPawNrwOD_thg
Tiktok
https://www.tiktok.com/?is_from_webapp=1&sender_device=pc
Instagram
https://www.instagram.com/hawassaalamurafullgospelchurch/
Follow, Like, Share በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ፡፡