19/05/2026
ግንቦት 11 የቅዱስ ያሬድ በዓል በሀዋሳ ደብረ ይባቤ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ተከበረ"
"እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ጉባኤ ክቡር ነው!" (መዝ. 88፥7)
የኢትዮጵያዊው የዜማ ሊቅና የቤተክርስቲያናችን ብርሃን የሆነው የቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ የንግሥ በዓልና የታላቁ መንፈሳዊ ጉባኤ ማጠቃለያ ዛሬ ግንቦት 11 ቀን በሀዋሳ ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓትና በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል።
ይህ ታላቅ ዕለት፦
🌹በቅድስት ቤተክርስቲያን ሊቃውንት ያሬዳዊ ጥዑም ዜማ፣ ወረብና ማኅሌት፣
🌹በሀገረ ስብከትና በወረዳ ቤተ ክህነት ከፍተኛ ልዑካን ይፋዊ ተሳትፎና አባታዊ መሪነት፣
🌹በተለያዩ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ መምህራነ ወንጌልና ካህናት በጎ አገልግሎት፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን በተገኙበት በልዩ መንፈሳዊ ድባብ ተከብሯል።
የቅዱስ ያሬድ ረድኤትና በረከት፣ የአባቶቻችን ጸሎትና ቡራኬ በሁላችን ላይ ጸንቶ ይኑር። በዓሉን በሰላም ያስፈጸመ እግዚአብሔር ይመስገን!
"የቅዱስ ያሬድ በረከቱ ይደርብን!"
ከደብሩ ሕዝብ ግንኙነት
ኢዮር ሚዲያ ሲዳማ ሀገረ ስብከት EYOR MEDIA SIDAMA DIOCESE
እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል ፡፡
ዮሐ 3 + 34
You tube
https://www.youtube.com/
Facebook
https://www.facebook.com/share/1EytyXvRwR/
Telegram
https://t.me/sidamade
Tik tok
tiktok.com/@