ኢዮር ሚዲያ EYOR MEDIA

ኢዮር ሚዲያ EYOR MEDIA Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ኢዮር ሚዲያ EYOR MEDIA, Religious organisation, Hawassa, Hawassa.

ግንቦት 11 የቅዱስ ያሬድ በዓል በሀዋሳ ደብረ ይባቤ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ተከበረ"‎‎​"እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ጉባኤ ክቡር ነው!" (መዝ. 88፥7)‎‎​የኢትዮጵያዊው የዜማ ሊቅና ...
19/05/2026

ግንቦት 11 የቅዱስ ያሬድ በዓል በሀዋሳ ደብረ ይባቤ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ተከበረ"

‎​"እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ጉባኤ ክቡር ነው!" (መዝ. 88፥7)

‎​የኢትዮጵያዊው የዜማ ሊቅና የቤተክርስቲያናችን ብርሃን የሆነው የቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ የንግሥ በዓልና የታላቁ መንፈሳዊ ጉባኤ ማጠቃለያ ዛሬ ግንቦት 11 ቀን በሀዋሳ ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓትና በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል።

‎​ይህ ታላቅ ዕለት፦
‎🌹​በቅድስት ቤተክርስቲያን ሊቃውንት ያሬዳዊ ጥዑም ዜማ፣ ወረብና ማኅሌት፣
‎🌹​በሀገረ ስብከትና በወረዳ ቤተ ክህነት ከፍተኛ ልዑካን ይፋዊ ተሳትፎና አባታዊ መሪነት፣
‎🌹​በተለያዩ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ መምህራነ ወንጌልና ካህናት በጎ አገልግሎት፣ ​በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን በተገኙበት በልዩ መንፈሳዊ ድባብ ተከብሯል።
‎​የቅዱስ ያሬድ ረድኤትና በረከት፣ የአባቶቻችን ጸሎትና ቡራኬ በሁላችን ላይ ጸንቶ ይኑር። በዓሉን በሰላም ያስፈጸመ እግዚአብሔር ይመስገን!
‎​"የቅዱስ ያሬድ በረከቱ ይደርብን!"
‎ ከደብሩ ሕዝብ ግንኙነት
ኢዮር ሚዲያ ሲዳማ ሀገረ ስብከት EYOR MEDIA SIDAMA DIOCESE
እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል ፡፡
ዮሐ 3 + 34

You tube
https://www.youtube.com/

Facebook
https://www.facebook.com/share/1EytyXvRwR/

Telegram
https://t.me/sidamade

Tik tok
tiktok.com/@

ማኅበራዊ ሚዲያ ለመንፈሳዊ አገልግሎት በሚል ርእስ በደብረ ምጥማቅ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በደብሩ ውስጥ ላሉ ልዩ ልዩ ክፍሎችና ለምእመናን ስልጠና ተሰጠ።‎         /ግንቦት 9/20...
17/05/2026

ማኅበራዊ ሚዲያ ለመንፈሳዊ አገልግሎት በሚል ርእስ በደብረ ምጥማቅ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በደብሩ ውስጥ ላሉ ልዩ ልዩ ክፍሎችና ለምእመናን ስልጠና ተሰጠ።
‎ /ግንቦት 9/2018 ዓ/ም/
‎ስልጠናውን የከፈቱት የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ስብሐት መምህር ኪነ ጥበብ ያለው ትናንት ያልነበረ ዛሬ ግን ዓለምን የተቆጣጠረ ማኅበራዊ ሚዲያ ነው።
‎በማኅበራዊ ሚዲያ ሰው የፈለገውን የሚጠቅመውንም ይሁን የማይጠቅመውን ያሠራጭበታል።
‎ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ዘመን ባመጣው ማኅበራዊ ሚዲያ በመጠቀም ባላት ሀብት ልጆቿን መጠበቅና በትምህርት ተደራሽ መሆን ግዴታዋ ስለሆነ ይህ ስልጠና ተዘጋጅቷል በማለት ስልጠናው መከፈቱን አብሥረዋል።
‎ በዕለቱ ስለጠናውን የሰጡት ፕርፌሰር ዘመዱ ደምስስ ሲሆኑ ትናንት ከትናንት ወዲያ ሰው ሥራ ውሎ ሲገባ በቴሌቭዥን ወይም በሬዲዮ ዜና ከፍቶ ይሰማ ነበር ዛሬ ግን ትንሹም ትልቁም በየትኛውም ጊዜ በየትኛውም ሰዓት ዜና በእጁ ላይ ይሰማል።
‎ የምንሰማው ግን የሚጠቅምም የማይጠቅምም ሊሆን ይችላል ስለዚህ ይህን ተረድተን ከልጆቻችን ጋር መነጋገር መወያየት ካልቻልን ልጆቻችንን ከክፉ ነገር ጠብቀን በምንፈልገው መንገድ መምራት አንችልም።
‎ ሌላው በአሁኑ ሰዓት ሰው ሁሉ የዜጋ ጋዜጠኛ ሆኗል
‎ ይህ ደግሞ በትምህርት አይደለም እጁ ላይ የሚዲያ መሣሪያ ስላለ እንጂ ስለዚህ እውነትም ሀሰትም በሚተላለፍበት ሚዲያ ቤተ ክርስቲያን ሚዲያ ላይ ንቁ ተሳታፊ ሆና እውነትን በማስተላለፍ ብቻ ምእመናንን መጠበቅ ግዴታዋ ነው
‎ ካሉ በኋላ "በልጆቻችን እጅ ያለው ስልክ ውቅያኖስ ነው ልጆቻችን ግን ዋና አይችሉም" ስለዚህ ሚዲያን በአግባቡ መጠቀም ያስፈልጋል በማለት መልእክታቸውን አጠቃለዋል።
‎ በመቀጠል ስለ ደብሩ ሚዲያ ማለትም በደብሩ ጥያቄ በሀገረ ስብከቱ ጸድቆ ሳዶር የሚል ሚዲያ ተከፍቶ ሥራ መጀመሩንና ሰበካው ለሚዲያው ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ በደብሩ ሕዝብ ግንኙነት ተገልጿል።
‎በመጨረሻም የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ስብሐት መምህር ኪነ ጥበብ ያለው አሰልጣኙንና ስልጠናውን በትእግስት የተከታተሉትን ካህናትና ምእመናንን ካመሰገኑ በኋላ ምእመናን ሚዲያውን እንዲገፉና እንዲከታተሉ መልእክት አስተላልፈው ፕሮግራሙ በጸሎት ተጠናቋል ።

ኢዮር ሚዲያ ሲዳማ ሀገረ ስብከት EYOR MEDIA SIDAMA DIOCESE
እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል ፡፡
ዮሐ 3 + 34

You tube
https://www.youtube.com/

Facebook
https://www.facebook.com/share/1EytyXvRwR/

Telegram
https://t.me/sidamade

Tik tok
tiktok.com/

15/05/2026

Nyd de videoer og den musik, du holder af, upload originalt indhold, og del det hele med venner, familie og verden på YouTube.

✨የዜማው አባት - የኢትዮጵያ ብርሃን"​የቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ የንግሥ በዓልና ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ​"ለእግዚአብሔር በአዲስ ዜማ ዘምሩ፤ ለቅዱሳኑም ምስጋና ይገባል!"​የተወደዳችሁ የእግዚአብሔ...
14/05/2026

✨የዜማው አባት - የኢትዮጵያ ብርሃን"

​የቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ የንግሥ በዓልና ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ

​"ለእግዚአብሔር በአዲስ ዜማ ዘምሩ፤ ለቅዱሳኑም ምስጋና ይገባል!"

​የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች፤ የቅዱስ ያሬድ በረከት ናፋቂዎች፤

​በሀዋሳ ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን፣ የኢትዮጵያዊው የዜማ ሊቅ የቅዱስ ያሬድን ዓመታዊ የንግሥ በዓል ምክንያት በማድረግ ከግንቦት 9 እስከ 11 ቀን የሚቆይ ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ተዘጋጅቷል።

​ይህ ጉባኤ የነፍስ ምግብ የሚቀርብበት፣ በአባቶች ትምህርትና በሊቃውንት ማኅሌት የምንታደስበት ልዩ መድረክ ነው።

ኑ! ከያሬዳዊው ጥዑም ዜማ በረከትን እንቀበል፤ በአባቶች ትምህርት ሕይወታችንን እናድስ።

✨​"ኑ! የበረከቱ ተካፋይ ሁኑ!"✨🙏
@ የደብሩ ሕዝብ ግንኙነት

ኢዮር ሚዲያ ሲዳማ ሀገረ ስብከት EYOR MEDIA SIDAMA DIOCESE
እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል ፡፡
ዮሐ 3 + 34

You tube
https://www.youtube.com/

Facebook
https://www.facebook.com/share/1EytyXvRwR/

Telegram
https://t.me/sidamade

Tik tok
tiktok.com/

"እግዚአብሔር ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሰራው" መክ 3:-11‎ግንቦት/02/2018 ዓ.ም‎❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤‎እንደ እግዚአብሔር መልካም ፍቃድ በሲዳማ ሀገረ ስብከት በንሳ ወረዳ ቤተክህ...
11/05/2026

"እግዚአብሔር ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሰራው" መክ 3:-11
‎ግንቦት/02/2018 ዓ.ም
‎❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
‎እንደ እግዚአብሔር መልካም ፍቃድ በሲዳማ ሀገረ ስብከት በንሳ ወረዳ ቤተክህነት ሐመሾ ቦረና ቀበሌ አዲሱ የእግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን
‎በመጀመራያ ዛፍ ሥር፣ቀጥሎ በሸራ(ዳስ)ውስጥ የወንጌል አገልግሎት የተጀመረው በሀገረ ስብከታችን መልካም ፍቃድ በብፁዕ አቡነ ዮሴፍ መጋቢት 20/2018 ዓ.ም ከአንድ ግለሰብ 400 ካ.ሜ በተለገሠው ቦታ(መሬት) ተባርኮ የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ የሕንጻ አሠሪ ኮሚቴ ተቋቁሞ ኮሚቴው ሦስት ደረጃ ዕቅድ በማቀድ ማለትም:- የአጭር ጊዜ፣መካከለኛ ጊዜ እና የረጅም ጊዜ ዕቅድ በማቀድ በሁለት ቀን ውስጥ የስብከተ ወንጌል አደራሽ በማሰራት በተጨማርም 500 ካ.ሜ ይዞታ ግዥ ብድር ውል በመግባት ይዞታ የማስፋት ሥራ ተከናውኖ ዛሬ የመጀመሪያ በስብከተ ወንጌል አደራሽ መደበኛ የፀሎትና የስብከተ ወንጌል ትምህርት አገልግሎት አገልጋዮችን በማሰማራት ድም ተጀምሯል።

‎ዘገባው:-የወረዳ ቤተ ክህነቱ የሕዝብ ግንኙነት ነው።

ኢዮር ሚዲያ ሲዳማ ሀገረ ስብከት EYOR MEDIA SIDAMA DIOCESE
እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል ፡፡
ዮሐ 3 + 34

You tube
https://www.youtube.com/

Facebook
https://www.facebook.com/share/1EytyXvRwR/

Telegram
https://t.me/sidamade

Tik tok
tiktok.com/

11/05/2026

Nyd de videoer og den musik, du holder af, upload originalt indhold, og del det hele med venner, familie og verden på YouTube.

  #‎በሀዋሳ ደብረ ሰላም ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሁለተኛ ደረጃ ትምህር ቤት ሕንጻ ግንባታ ፍጻሜ ‎  በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው መንፈሳዊ ጉዞ  መነሻውን ከደብረ ሰላም ቅድስት ሥላሴ ካቴድራ...
10/05/2026

#
‎በሀዋሳ ደብረ ሰላም ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሁለተኛ ደረጃ ትምህር ቤት ሕንጻ ግንባታ ፍጻሜ
‎ በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው መንፈሳዊ ጉዞ መነሻውን ከደብረ ሰላም ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ያደረገ ሲሆን መዳረሻው ደብረ ምህረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሆኖ በርካታ ምእመናን በተገኙበት ታሪካዊ ጉዞ ተደርጓል ።
‎ ግንቦት 2/2018 ዓ/ም
‎@ የካቴድራሉ ሕዝብ ግንኙነት

ኢዮር ሚዲያ ሲዳማ ሀገረ ስብከት EYOR MEDIA SIDAMA DIOCESE
እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል ፡፡
ዮሐ 3 + 34

You tube
https://www.youtube.com/

Facebook
https://www.facebook.com/share/1EytyXvRwR/

Telegram
https://t.me/sidamade

Tik tok
tiktok.com/

በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሀዋሳ ከተማ በደብረ ሰላም ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የእመቤታችን የድንግል ማርያም የልደት በዓል ተከበረ።‎           ግንቦት 1/2018 ዓ/ም         ‎   ...
09/05/2026

በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሀዋሳ ከተማ በደብረ ሰላም ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የእመቤታችን የድንግል ማርያም የልደት በዓል ተከበረ።
‎ ግንቦት 1/2018 ዓ/ም
‎ ፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
‎በበዓሉ ላይ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ጥበባት ቀሲስ ሞላልኝ መርጊያ፣ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ምክትል ሥራ አስኪያጅና የታቦር ፍኖተ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ ዲን መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ነጻነት አክለወግ፣የሀገረ ስብከቱ የየክፍል ኃላፊዎች፣የሀዋሳ ከተማና ዙሪያ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ ላዕከ ወንጌል ቀሲስ ደግፌ ባንቡራ፣የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ምእመናንና ምእመናት ተገኝተዋል።
‎በዐውደ ምሕረቱ በኩረ ትጉሃን ቀሲስ ደመላሽ ቶጋ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ ስለ ዕለቱ በዓል ካስተማሩ በኋላ የካቴድራሉ አስተዳዳሪ መልአከ መንክራት ቆሞስ አባ ወልደ ሰንበት አባቡ ከደብሩ ማኅበረ ካህናት ጀምሮ የተለያዩ ክፍሎችንና ለካቴድራሉ ልዩ ልዩ አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ምእመናንን አመስግነዋል።
‎በመጨረሻም የሲዳማ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ጥበባት ቀሲስ ሞላልኝ መርጊያ የእመቤታችን ልደት የእኛ ልደት መሆኑንና የድኅነታችን መሠረት እንደሆነ ገልጸው በካቴድራሉ ስላለው የልማት እንቅስቃሴ ከአስተዳዳሪው ጀምሮ የሰበካ ጉባኤ አባላትንና ልዩ ልዩ ክፍሎችን ካመሰገኑ በኋላ በዋና ሥራ አስኪያጁ ጸሎት የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል።

ኢዮር ሚዲያ ሲዳማ ሀገረ ስብከት EYOR MEDIA SIDAMA DIOCESE
እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል ፡፡
ዮሐ 3 + 34

You tube
https://www.youtube.com/

Facebook
https://www.facebook.com/share/1EytyXvRwR/

Telegram
https://t.me/sidamade

Tik tok
tiktok.com/

በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሀዋሳ ከተማ ሪፈራል አካባቢ አዲስ በተተከለው በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን የሐዋርያው የቅዱስ ማርቆስ የዕረፍት በዓል ተከበረ።‎           ሚያዚያ 30/2018...
08/05/2026

በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሀዋሳ ከተማ ሪፈራል አካባቢ አዲስ በተተከለው በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን የሐዋርያው የቅዱስ ማርቆስ የዕረፍት በዓል ተከበረ።
‎ ሚያዚያ 30/2018 ዓ/ም
‎ ፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
‎በበዓሉ ላይ የተገኙት የሲዳማ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ጥበባት ቀሲስ ሞላልኝ መርጊያ የሐዋርያው የቅዱስ ማርቆስን ተጋድሎ ገለጸው ከዚህ ሐዋርያ በረከት ለማግኘት ቦታው አዲስ እነደ መሆኑ ለቦታው መስፋፋት ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ መልእክት አስተላልፈው በዋና ሥራ አስኪያጁ ጸሎት የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል።

ኢዮር ሚዲያ ሲዳማ ሀገረ ስብከት EYOR MEDIA SIDAMA DIOCESE
እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል ፡፡
ዮሐ 3 + 34

You tube
https://www.youtube.com/

Facebook
https://www.facebook.com/share/1EytyXvRwR/

Telegram
https://t.me/sidamade

Tik tok
tiktok.com/

በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሸበዲኖ፣ጎርቼ፣ይርባ ስድስቱ ወረዳዎች ቤተ ክህነት በለኩ ከተማ የሊቀ ሰማዕታት ቅዱሰ ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በለኩ ገነተ ፅጌ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስ...
02/05/2026

በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሸበዲኖ፣ጎርቼ፣ይርባ ስድስቱ ወረዳዎች ቤተ ክህነት በለኩ ከተማ የሊቀ ሰማዕታት ቅዱሰ ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በለኩ ገነተ ፅጌ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን 23/8/2018 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።
:::::::::::::::
የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በረከቱ ይድረስን አሜን

@ የወረዳው ቤተ ክህነት ሕዝብ ግንኙነት

ኢዮር ሚዲያ ሲዳማ ሀገረ ስብከት EYOR MEDIA SIDAMA DIOCESE
እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል ፡፡
ዮሐ 3 + 34

You tube
https://www.youtube.com/

Facebook
https://www.facebook.com/share/1EytyXvRwR/

Telegram
https://t.me/sidamade

Tik tok
tiktok.com/

በሲዳማ ሀገረ ስብከተ በሀዋሳ ከተማ በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ ዕረፍት ተከበረ።‎        ሚያዚያ 23/2018 ዓ/ም‎      በበዓሉ ...
01/05/2026

በሲዳማ ሀገረ ስብከተ በሀዋሳ ከተማ በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ ዕረፍት ተከበረ።
‎ ሚያዚያ 23/2018 ዓ/ም
‎ በበዓሉ ላይ የሲዳማ ሀገረ ስብከት የየክፍል ኃላፊዎች፣የሀዋሳ ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪጅና ሠራተኞች፣ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን ተገኝተዋል።
‎በዕለቱ በውደ ምሕረት በረዳው ዋና ሥራ አስኪያጅ በላዕከ ወንጌል ቀሲስ ደግፌ ባንቡራ የዕለቱ ትምህርት ከተሰጠ በኋላ በደብሩ አስተዳዳሪ በመልአከ ሰላም ቀሲስ ታረቀኝ እንግዳ ጸሎትና ቡራኬ የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል።

ኢዮር ሚዲያ ሲዳማ ሀገረ ስብከት EYOR MEDIA SIDAMA DIOCESE
እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል ፡፡
ዮሐ 3 + 34

You tube
https://www.youtube.com/

Facebook
https://www.facebook.com/share/1EytyXvRwR/

Telegram
https://t.me/sidamade

Tik tok
tiktok.com/

Address

Hawassa
Hawassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኢዮር ሚዲያ EYOR MEDIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ኢዮር ሚዲያ EYOR MEDIA:

Share