መራሔ ድኅነት ሰንበት ት.ቤት /Hawassa St. Gebriel Sunday School/

  • Home
  • Ethiopia
  • Hawassa
  • መራሔ ድኅነት ሰንበት ት.ቤት /Hawassa St. Gebriel Sunday School/

መራሔ ድኅነት ሰንበት ት.ቤት /Hawassa St. Gebriel Sunday School/ የደብረ ምህረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም መራኄ ድኅነት ሰንበት ?

የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ለሚያስገነባው ጠቅላላ ሆስፒታል የቦታ ጠረጋ ተከናወነ።🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚የሀዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም መንፈሳዊ አገልግሎቱን በቋሚ ገቢ ለማስቀጠል...
22/05/2026

የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ለሚያስገነባው ጠቅላላ ሆስፒታል የቦታ ጠረጋ ተከናወነ።
🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

የሀዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም መንፈሳዊ አገልግሎቱን በቋሚ ገቢ ለማስቀጠል ያቀደውን ጠቅላላ ሆስፒታል ግንባታ ለማስጀመር የቦታ ጠረጋ ሥራ አከናውኗል።

በበጀት ዓመቱ ዕቅድ መሠረት የተከናወነው የጠረጋ ሥራ የገዳሙ አስተዳዳሪ መ/ፀ/መ/ር አባ ኪዳነማርያም አንዱዓለም (ቆምስ) በተገኙበት ሲሆን፣አቶ አንድነት ጌታቸው በነፃ ባቀረቡት ማሽን ተከናውኗል።

በቀጣይ የበጀት ዓመት የሆስፒታሉን ዲዛይን በማጸደቅ እና የግንባታ ፈቃድ በማውጣት ልዩ ልዩ የኦርቶዶክሳውያን ድርጅቶችንና ሕዝበ ክርስቲያኑን በማስተባበር በሚገኝ ገቢ የግንባታ ሥራውን ለመጀመር ዕቅድ መያዙ ተገልጿል።

ከሆስፒታሉ ግንባታ በተጨማሪም፣ በቦታው ላይ በተከራዮች ቅድመ ክፍያ የሚገነቡ የንግድ ሱቆች እንደሚኖሩ ተጠቁሟል።

ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም
© ናዛዚ ሚዲያ

+ ሀ/ደ/ም/ቅ/ገ/ገ/መራሔድኅነት ሰ/ት/ቤት

+++በሚንቦገቦግ የደመና ተን ዐረገ+++ጌታችን ከማረጉ አስቀድሞ ለደቀ መዛሙርቱ በተገለጠላቸው ጊዜ መንፈስ ያዩ መስሏቸው ፈርተው ነበር። ጌታችንም "ስለ ምን ትደነግጣላችሁ? ስለ ምንስ አሳብ...
21/05/2026

+++በሚንቦገቦግ የደመና ተን ዐረገ+++

ጌታችን ከማረጉ አስቀድሞ ለደቀ መዛሙርቱ በተገለጠላቸው ጊዜ መንፈስ ያዩ መስሏቸው ፈርተው ነበር። ጌታችንም "ስለ ምን ትደነግጣላችሁ? ስለ ምንስ አሳብ በልባችሁ ይነሣል? እኔ ራሴ እንደ ሆንሁ እጆቼንና እግሮቼን እዩ ፤ በእኔ እንደምታዩት፥ መንፈስ ፤ ሥጋና አጥንት የለውምና እኔን ዳስሳችሁ እዩ" በማለት ምትሐት አለመሆኑን ፤ ከዚህ ቀደም የሚያስተምራቸው መምህራቸው መሆኑን አይተው ዳሰው እንዲያምኑ ፤ እርሱ ከሞት ከተነሣም በኋላ ሥጋና አጥንት እንዳለው ፍጹም ሰውነቱ እንዳልራቀበት ይነግራቸው ነበር። ነገር ግን ይህን ብሏቸው እንኳን ልባቸው አለማረፉን ተመልክቶ ፤ "በዚህ አንዳች የሚበላ አላችሁን?" አላቸው። (ሉቃ. 24: 41)

ደቀ መዛሙርቱም "ከተጠበሰ ዓሣ አንድ ቁራጭ፥ ከማር ወለላም ሰጡት ፤ ተቀብሎም በፊታቸው በላ" ፤ በእውነት ይገርማል!!! ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት የደቀ መዛሙርቱን ዓሣ መሥጠት እንዲሁ ያለ ምሥጢር በቀላሉ አላለፉትም። ከቀደምት ሊቃውንት አንዱ ፤ ዓሣ በውኃ ውስጥ እንዲኖር ፤ ክርስቶስም ስለሰው ልጆች ፍቅር ወደ ሰው ልጆች ዓለም ወረደ በዚያም ተመላለሰ። ዓሣ በሰዎች በመንጠቆ ተይዞ ከውኃ ወጥቶ እንደሚሞትና እንደሚጠበስ ፤ ጌታችንም ስለ ሰው ፍቅር ፤ በሰዎች ተይዞ እሳት የተባለ መከራን ተቀብሎ ነፍሱን ከሥጋው ለየ ፤ በማለት ያስተምራል።

ዓሣ በቀደምት ክርስቲያኖች ዘንድ የተለመደ ምልክት ነበር። ዓሣ በላቲን Icthus ይባላል። የዚህ የላቲን ቃል እያንዳንዱ ፊደል ራሱን የቻለ ትርጉም አለው። Icthus የሚለው ቃል በግሪክ ቃላት I=Iota; C=Chi; T=Theta; U=Upsilon; S=Sigma ወይም Iesous CHristos THeou Uiou Soter ተብሎ ይተነተናል። ትርጉሙም "መድኃኒት የሆነ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ" ማለት ነው። [1]

ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ደግሞ "በቀደመው ሕግ በብሉይ ኪዳን እስራኤል ፋሲካን መራራ ቅጠል በመብላት እንዲፈጽሙት መታዘዛቸው ፤ ከባርነት ቀንበር ገና አለመውጣታቸውን እንዲዘከሩ ነው። እውነተኛው ትንሣኤ ግን እውነተኛውን ፋሲካ ከሠጠን በኋላ መራራውን ፤ ጣፋጭ በሆነው ማር ለወጠልን" ይላል። [2]

መድኃኔ ዓለም ምትሐት እንዳልሆነ እርሱነቱን ያምኑ ዘንድ እዩኝ ፣ ዳስሱኝ ከማለት በላይ በልቶ አሳያቸው። ከሞት ከተነሣ በኋላ መብላት መጠጣቱ የሚጠቅመው ሆኖም አይደለም ፤ ምትሐት አለመሆኑን ሊያሳያቸው እንጂ። (after His resurrection eat part of a broiled fish and of a honey-comb, not to allay hunger and to gratify His palate, but to show the reality of His own body. For whenever He raised anyone from the dead He ordered that food should be given him to eat, lest the resurrection should be thought a delusion.) [3]

አስተውለን ከሆነ ጌታችን የሞቱ ሰዎችን ከሞት ካስነሣቸው በኋላ ምግብ እንዲበሉ በማድረግ ሰውነታቸውን ሌሎች እንዳይጠራጠሩ ያደርግ ነበር፡፡ ለምሳሌ፡ አልዓዛርን ከሞት ካስነሣው በኋላ ከጌታ ጋር እራት ለመብላት አብሮ እንደተቀመጠ ተጽፏል፡፡ ‹‹ከዚያም እራት አደረጉለት፤ ማርታም ታገለግል ነበር፤ አልዓዛር ግን ከእርሱ ጋር ከተቀመጡት አንዱ ነበረ።›› (ዮሐ. 12፡2) ፤ በሌላም ክፍል የምኩራብ አለቃውን ልጅ ከሞት ካስነሣት በኋላ ‹‹የምትበላውን ስጡአት›› (ማር. 5፡43) ሲል እናገኘዋለን፡፡ [4]

የጌታችን መብላት ሊቃውንት "ከኃይሉ የተነሣ በላ እንላለን እንጂ ምግቡ ሊጠቅመው ሊረባው አይደለም"(He ate indeed by His power, not from necessity) ይላሉ። በምሳሌ ሲገልጹት ፤ ውኃ የጠማው ደረቅ መሬትም ውኃን ሲያገኝ መጥጦ ውኃውን ይወስደዋል ፤ ውኃ የማይሻ ቦታ ላይ ያቆረ የተቀመጠን ውኃም ፀሐይ አትንኖ ያጠፋዋል። በሁለቱም መንገድ ውኃው ይጠፋል። የደረቀው መሬት ውኃ ስለሚያሻው ውኃውን የመጠጠው ሲሆን ፤ ፀሐዩ ደግሞ ከኃይሉ የተነሣ ውኃውን አትንኖታል። የጌታችንም መብላት ልክ እንደ ፀሐዩ ከኃይሉ የተነሣ እንደሆነ አበው ያስተምራሉ!!!

+++

"ወልደ እግዚአብሔርሰ ዐርገ እንበለ ሰዋስው በሳሕወ ደመና ዘያነበለብል" "የእግዚአብሔር ልጅ ግን ያለ መሰላል በሚንቦገቦግ የደመና ተን ዐረገ።" [5]

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
(መጽሐፈ ምሥጢር ፤ ምንባብ ዘዕርገት)




ስብሐት ለእግዚአብሔር
©ዲያቆን ደረጀ ድንቁ

+ ሀ/ደ/ም/ቅ/ገ/ገ መራሔድኅነት ሰ/ት/ቤት

ታላቅ የንግስ በዓል ግንቦት 19
19/05/2026

ታላቅ የንግስ በዓል ግንቦት 19

12/05/2026
ሁለት አዲስ ዝማሬዎች በቅርብ ቀን በመራሔ ድኅነት ሰ/ት/ቤት
10/05/2026

ሁለት አዲስ ዝማሬዎች በቅርብ ቀን በመራሔ ድኅነት ሰ/ት/ቤት

ግንቦት ልደታ……ቅዳሜ ግንቦት 1/2018 ዓ.ም+ መራሔድኅነት ሰ/ት/ቤት
07/05/2026

ግንቦት ልደታ……

ቅዳሜ ግንቦት 1/2018 ዓ.ም

+ መራሔድኅነት ሰ/ት/ቤት

"…በእውነት መመስገን ይገባሻል ለማለዳው ኮከብ ምሥራቅ ሆነሻልና። በእውነት መደነቅ ይገባሻል ለጥምቀት ልጆች መመኪያ ሆነሻልና። በእውነት ብፅዕና ይገባሻል ለሃይማኖት መሠረት ሆነሻልና……"አባ...
29/04/2026

"…በእውነት መመስገን ይገባሻል ለማለዳው ኮከብ ምሥራቅ ሆነሻልና። በእውነት መደነቅ ይገባሻል ለጥምቀት ልጆች መመኪያ ሆነሻልና። በእውነት ብፅዕና ይገባሻል ለሃይማኖት መሠረት ሆነሻልና……"

አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ /አርጋኖን ዘረቡዕ/

+መራሔድኅነት ሰ/ት/ቤት

የፌስቡክ ገፅ:https://www.facebook.com/profile.php?id=100069444095761

የቴሌግራም አድራሻ: https://t.me/SaintGebrielSundaySchool

የዩቲዩብ ገፅ:የማኅበራዊ https://youtube.com/?feature=shared

" ሦስቱ ወጣቶች እሳት ውስጥ ሆነው እንደዘመሩ በመከራ ውስጥ ሆኖ ፈጣሪን የሚያመሰግን ሰው የመከራው እሳት ውኃ ይሆንለታል። ለድሆች ምጽዋትን የሚሰጥ ሰው ደግሞ ሠልስቱ ደቂቅን ከእሳት የታደ...
27/04/2026

" ሦስቱ ወጣቶች እሳት ውስጥ ሆነው እንደዘመሩ በመከራ ውስጥ ሆኖ ፈጣሪን የሚያመሰግን ሰው የመከራው እሳት ውኃ ይሆንለታል። ለድሆች ምጽዋትን የሚሰጥ ሰው ደግሞ ሠልስቱ ደቂቅን ከእሳት የታደገውን የእግዚአብሔር መልአክን ይመስለዋል…"
/ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/

+መራሔድኅነት ሰ/ት/ቤት

የፌስቡክ ገፅ:https://www.facebook.com/profile.php?id=100069444095761

የቴሌግራም አድራሻ: https://t.me/SaintGebrielSundaySchool

የዩቲዩብ ገፅ:የማኅበራዊ https://youtube.com/?feature=shared

የመራሔ ድኅነት ሰ/ት/ቤት ሥራ አመራርና ንዑሳን ክፍላት ተጠሪዎች  የሀገረ ስብከታችን  የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ኮሚቴ ም/ሥራ አስኪያጅ ዲ/ን አርክቴክት አንተነህ ጌትነት መኖርያ ቤት በመ...
27/04/2026

የመራሔ ድኅነት ሰ/ት/ቤት ሥራ አመራርና ንዑሳን ክፍላት ተጠሪዎች የሀገረ ስብከታችን የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ኮሚቴ ም/ሥራ አስኪያጅ ዲ/ን አርክቴክት አንተነህ ጌትነት መኖርያ ቤት በመገኘት የትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሶት መርሐግብር አከናወኑ

ሚያዝያ /፳፻፲፰ ዓ.ም

በዕለቱም የሰ/ት/ቤቱ ሥራ አመራር አባላት እና የክፍላት ተጠሪዎች በየተራ ለመምህራችን የእንኳን አደረሶት መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በመቀጠልም የሰ/ት/ቤቱ ሰብሳቢ ታምራየሁ ግርማ የሰ/ት/ቤቱን መልዕክት አስተላልፈው ስጦታ ለዲ/ን አርክ. አንተነህ ጌትነት እና ለባለቤታቸው አበርክተዋል.

ዲ/ን አርክ አንተነህ ጌትነት የሰ/ት/ቤት ፍሬ ሲሆኑ ለበርካታ ዓመታት ከሰ/ት/ቤት ጀምሮ በግቢ ጉባኤያትና በቤተክርስቲያን በተለያዩ መዋቅራት በበጎ ፍቃድ ያገለገሉ በሞያቸው በርካታ ዲዛይኖችን ለቤተ ክርስቲያን በነጻ የሰሩ እና በተጨማሪም እንደ ሰ/ት/ቤታችን በልዩ ልዩ መርሐግብራት ሥልጠና በመስጠት በማስተማር የሚያገለግሉ ሰንበት ት/ቤታችን የተሻለ እንዲሆን ልምድና ምክርን በማካፈል እንዲሁም የሰንበት ት/ቤቱን ህንጻ ዲዛን ከ3 ጊዜ በላይ በመስራት እና በማሻሻል አሁን ለታነጸው ህንጻ ትልቅ አሻራቸውን ያኖሩ ባለውለታችን ናቸው።

በመጨረሻም "ABCD ብቻ አይበቃህም/ሽም አቦጊዳውን ከቤተ ክርስትያን አዋህደህ ያዘው" በሚል ንግግራቸው የሚታወቁት ዲ/ን አርክ.አንተነህ የሰ/ት/ቤቱ ተወካዮች አባላት ስላከናወኑት የእንኳን አደረሶት መርሐግብር ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይ እንደ ቤተክርስቲያን(እንደ ሰ/ት/ቤትም)በርካታ መሥራት የሚገባን የሚጠበቅብን ኃላፊነት እንዳለ በማስገንዘብ ምክርም ከሰጡ በኋላ የመርሐግብሩ ፍጻሜ ሆኗል ።

በአማን ተንሥአ እግዚእነ እሙታን

መራሒ ሚድያ

የፌስቡክ ገፅ:https://www.facebook.com/profile.php?id=100069444095761

የቴሌግራም አድራሻ: https://t.me/SaintGebrielSundaySchool

የዩቲዩብ ገፅ:የማኅበራዊ https://youtube.com/?feature=shared

እንኳን አደረሳችሁ/አደረሰን…!
19/04/2026

እንኳን አደረሳችሁ/አደረሰን…!

Address

Hawassa
Hawassa

Telephone

+251462215117

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when መራሔ ድኅነት ሰንበት ት.ቤት /Hawassa St. Gebriel Sunday School/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share