Hawassa chaffe full gospel believers church

Hawassa chaffe full gospel believers church bible This page is created for born again christian to share all spiritual things from our holy Bible. Jesus is our saver,our life,our all things! Eph 1:4

Born again christian are people who believed in Jesus's work that done on cross and saved for ever. Thanks to Him for his love of us. Any one who follow this page he/she can post and share spiritual things only. God already blessed you in all spiritual blessings in heavenly place.

የሰው ሶስትነትሰው በእግዚአብሔር የባሕርይ ምሳሌ ተፈጥሯል (ዘፍ1-:-26-27፣ ያዕ3-:-9)፡፡ ለዚህም ማስረጃ ከሚሆኑት መካከል ጥቂቶቹ፡-ሦስትነቱ (ሥጋ፣ ነፍስና መንፈስ) 1ተሰ5-:-23...
14/12/2025

የሰው ሶስትነት

ሰው በእግዚአብሔር የባሕርይ ምሳሌ ተፈጥሯል (ዘፍ1-:-26-27፣ ያዕ3-:-9)፡፡ ለዚህም ማስረጃ ከሚሆኑት መካከል ጥቂቶቹ፡-

ሦስትነቱ (ሥጋ፣ ነፍስና መንፈስ) 1ተሰ5-:-23፣ ዕብ4-:-12

ዘላለማዊነቱ (ከሞት በኋላ ትንሳኤ ያለው መሆኑና ከተፈጠረበት ቀን ጀምሮ የማይጠፋ መሆኑ (ሉቃ23-:-39-43)

የመግዛት ባሕሪው (ዘፍ1-:-28)

የመስራት ችሎታው (ዘፍ2-:-15)

የማስተዋል ችሎታው (ኢዮ32-:-8)

ሰውን ከሌሎች ፍጥረቶች ልዩ ከሚያደርጉ ባሕሪያት አንዱና ዋናው በግዙፍ አካል ውስጥ የእግዚአብሔር እስትንፋስ መቀመጡ ነው(ሥጋ፣ ነፍስና መንፈስ አለውና)1ተሰ5-:-23፡፡

የሰውን ሦስትነት መጽሀፍ ቅዱስ ሥጋ፣ ነፍስና፣ መንፈስ በማለት በሚገባ ያብራራል:: (1ተሰ5-:-23፣ ዕብ4-:-12)፡፡ የሰው ሦስትነት በተናጠል ሲታይም፡-

ሥጋ

ሥጋ በአይን የሚታይና በእጅ ሊዳሰስ የሚችለው የሰው አካል ሲሆን (ሉቃ24-:-36-40) ለማይታዩት ለነፍስና መንፈስ ማደሪያ ነው:: (ማቴ10-:-28፣ ኢዮ19-:-26)፡፡ ከግዙፍ አለም ወይም ፍጥረት ጋር የሚያገናኙትንም አምስቱን የስሜት ሕዋሳት ይዟል:: ሟችና በስባሽም ነው (1ቆሮ15-:-20፣ 1ጴጥ1-:-24፣ ዘፍ3-:-19)፡፡

ስጋችን እንደምርጫችን ለእግዚአብሔር መንፈስ ወይንም ለሰይጣን መንፈስ ማደሪያ ነው:: (ኤፌ1-:-13፣ 1ቆሮ6-:-19፣ 1ዮሐ4-:-13፣ ማር5-:-1-5፣9-:-17-25፣ ሉቃ8-:-27-33፣ ዘፍ3-:-6)፡፡

በአማርኛ ሥጋ የሚለው አንድ ቃል በግሪክ ቋንቋ አራት ትርጉሞች አሉት:: እነሱም:-

ሶማ - በአይናችን የምናየው ሥጋና አጥንት ነው:: (1ተሰ5-:-23)

ሰርኮስ - ለእግዚአብሔር የማይታዘዘው የሰው የማመጽ ባሕርይ (ከአዳም የተወረሰውና የተበላሸው ተፈጥሮአዊ ማንነት) ነው:: (ሮሜ8-:-3-8፣7-:-24)

ቶ ሶማቶስ ሐማርቲያ - የሰርኮስና የሶማ የመተባበር ውጤት የሆነው የተግባር ኃጢአት መገለጫ በመሆን ለእግዚአብሔር የማይጠቅምና የተበላሸ ማንነት ነው::

ሶማቶስ - እግዚአብሔር የሚፈልገውና የተቀደሰው ማንነት ወይም ከክርስቶስ የተቀበልነው ስጋ ማለት ነው::

ስለዚህ መጽሀፍ ቅዱስ ስጋ እርኩስ ነው የሚለው ከአዳም የወረስነውን አለመታዘዝ ባሕርይን (ሰርኮስን) እንጂ በአይናችን የምናየውን ስጋና አጥንትን (ሶማን) አይደለም::

ስለዚህ ጌታ ኢየሱስ ሶማችንን ወስዶ ከውስጡ የአዳምን አለመታዘዝ ባሕርይ (ሶርኮስን) አስወግዶ ነው ሶማቶስ አድርጎ የለወጠው:: በመሆኑም ስጋችን የክርስቶስ ስጋ (ሶማቶስ) ስለሆነ በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ስጋ ነው::

በቅድስት ማርያም በኩል ሲወለድ ጌታ ኢየሱስ ለብሶት የተገለጠው ስጋ የእኛን ስጋ (ሶማን) ነው፡፡ የአዳምን ዘር ባለመያዙም ሰርኮስ በሕይወቱ አልሰራም (ዘፍ3-:-8-13፣ ዕብ4-:-14-18)፡፡ እኛን ተክቶ በመስቀል ሲሞት ሶማችንን ከወሰደ በኋላም ሰርኮስ እንዳይሰራ ገደለው፤ እንደገና በትንሳኤ ደግሞ ሲነሳ ሶማቶስ በኛ እንዲሰራ በማድረግ ስጋችንን የተቀደሰና የከበረ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ አደረገው:: (ዮሐ14-:-15-17,1ቆሮ6-:-19) ስሙ ለዘለአለም ይክበር፡፡

ነፍስ

እግዚአብሔር የሕይወትን እስትንፋስ በሰው እፍ ባለበት ጊዜ የተፈጠረው የሰው አካል ክፍል ነው (ዘፍ2-:-7)፡፡

በሰው ስጋ ውስጥ የእግዚአብሔር እስትንፋስ ሲቀመጥ ሰው ሕያው ይሆናል:: እስትንፋሱ ሲለይ ደግሞ ይሞታል:: (ዘፍ2-:-7፣ ያዕ2-:-26፣ 1ነገ17-:-20-22፣ መዝ104-:-29፣ ኢዮ34-:-14-15)፡፡ ነፍስ ከሰው ስጋ ቢለይም የማይጠፋና ዘላለማዊ ነው (ማቴ10-:-28)፡፡ የሰ

በሚመጣው ዘመን ያዕቆብ ሥር ይሰድዳል፥ እስራኤልም ያብባል ይጨበጭብማል፤ በፍሬያቸውም የዓለሙን ፊት ይሞላሉ። ትንቢተ ኢሳይያስ 27 : 6🌿☘🍀🌵🌳🌲🎄መልካም አድስ ዓመት ይሁንልን❤️🌵🎄🌴🪴🍀
11/09/2025

በሚመጣው ዘመን ያዕቆብ ሥር ይሰድዳል፥ እስራኤልም ያብባል ይጨበጭብማል፤ በፍሬያቸውም የዓለሙን ፊት ይሞላሉ።
ትንቢተ ኢሳይያስ 27 : 6
🌿☘🍀🌵🌳🌲🎄መልካም አድስ ዓመት ይሁንልን❤️🌵🎄🌴🪴🍀

ከመዳን የሚገኙ በረከቶችከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ (ሮሜ5-:-9-11)አዲስ ፍጥረት መሆን (2ቆሮ5-:-17)ከዘላለም ሞት ወደ ዘላለም ሕይወት መሻገር (1ቆሮ1-:-14)በመንፈስ ቅዱስ መሞላት...
20/08/2025

ከመዳን የሚገኙ በረከቶች
ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ (ሮሜ5-:-9-11)
አዲስ ፍጥረት መሆን (2ቆሮ5-:-17)
ከዘላለም ሞት ወደ ዘላለም ሕይወት መሻገር (1ቆሮ1-:-14)
በመንፈስ ቅዱስ መሞላት (ኤፌ1-:-13)
መልካም ስራን መስራት (ኤፌ2-:-10)
የእግዚአብሔርን በረከት መውረስ (2ጴጥ1-:-2-4)
የቅዱሳን መልአክትን እገዛ ማግኘት (ዕብ1-:-14,መዝ34-:-7)
በቁስሉ የስጋ ፈውስ ማግኘትና ሌሎችም በረከቶች ናቸው:: (ዘፀ12-:-5-6,ቆላ1-:-12-14)
በጌታ ኢየሱስ መጨነቅ የመንፈስ ሰላም ተገኘ (ዘፀ12-:-5-6,ዮሐ12-:-27-30)
በጌታ ኢየሱስ በመገረፍ ቁስል የስጋ ፈውስ ለስጋ ህመምተኞች ተሰጠ:: (ኢሳ53-:-4-5,1ጴጥ2-:-24-25)
በጌታ ኢየሱስ ሞት የነፍስ ደህንነት ተሰጠ:: (ዘፀ12-:-7-13) ከዚህም የተነሳ ጌታ ኢየሱስ ሙሉውን ሰው ሊያድን ችሏል:: (ሐዋ4-:-8-12,ኢሳ53-:-4-12,1ጴጥ2-:-24-25)
ሰዎች በሚከተሉት መንገዶች ፈውሳቸውን ይቀበላሉ

አማኞች እጃቸውን ጭነው (ዘይት ቀብተው) ሲጸልዩ (ማር16-:-18,ያዕ5-:-14-16,ማር6-:-12-13)
ተአምራዊ ፈውስ ስጦታዎች ባላቸው አማኞች በኩል (1ቆሮ12-:-9,ሐዋ19-:-11-12,ሐዋ5-:-12-16)
በቃሉ ውስጥ በሚያልፍ የፈውስ ኃይል (ሉቃ7-:-7-10)
የሰይጣን፣ የኃጢአት፣ የሞትም ሆነ የበሽታ ኃይል በኢየሱስ ክርስቶስ ተሸንፏል:: ስለሆነም የስጋ ፈውስም ሆነ የነፍስ ደህንነት በነፃ የሚገኙ (የሚሰጡ) ስጦታዎች ስለሆኑ ከሰዎች የሚጠበቀው ፈቃደኝነትና እምነት ብቻ ነው:: (ያዕ5-:-14-16)

ጌታ አስቀድሞ ሊሰጠን የሚፈልገው የነፍስንና የመንፈስን ፈውስ ስለሆነ እኛም አስቀድመን ይሄንኑ እንፈልግ:: (ማቴ10-:-5-8,6-:-33,ማር6-:-12-13)

ደህንነት (መዳን) በአንድ ቀን ተጀምሮ የሚተው ነገር ሳይሆን በጥንቃቄና በብዙ መንፈሳዊ ተጋድሎ በዕለት ተዕለት ኑሮ ወደ ፍጻሜ የምናደርሰው የእግዚአብሔር የበረከት ስጦታ ነው:: ሰው ለመዳን የከፈለው ዋጋ የለውም በእምነት የተቀበለው ፀጋ እንጂ በመሆኑም ከዳንን በኋላ የመዳናችንን ፍሬ ማግኘት የምንችለው እስከመጨረሻ ድረስ በእምነታችን በመጽናት ብቻ ነው:: (ኤፌ2-:-8-9,ያዕ2-:-14-26)

ሰው አንድ ጊዜ ከዳነ በኋላ ሊጠፋ አይችልም የሚል የስህተት ትምህርት በዚህ ዘመን አለ:: ይሁን እንጂ የእግዚአብሔር ቃል እስከመጨረሻው እንድንጸና አስቀድሞ ያስጠነቅቀናል (ማቴ24-:-12,1ቆሮ9-:-27,ቆላ1-:-23,ፊል2-:-12,ዕብ2-:-1)፡፡ ከዚህም በተጨማሪ መጽሀፍ ቅዱሳችን አንዳንድ ሰዎች ካመኑ በኋላ እንደሚጠፉ ስማቸውም ከሕይወት መጽሐፍ እንደሚሰረዝ ይገልጻል (1ጢሞ1-:-19-20,2ጴጥ2-:-1,ዕብ4-:-6)፡፡

ደህንነት በእግዚአብሔር ልጅ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ብቻ የሚገኝ እንጂ በሰው ድካም ያልሆነ ለዘላለማዊ ርዕስትና ለጽድቅ አክሊል የሚያበቃ በረከት ነው::(ኤፌ1-:-17-19)

15/08/2025
Betibeb hulu le Egziabher tekegnuna Zemiru!
16/07/2025

Betibeb hulu le Egziabher tekegnuna Zemiru!

የኢየሱስ ክቡር ደም✍ስለ ደም (መስዋዕት ) ስናነሳ የመጀመሪያው ሰውን ለመታደግ እና ለማዳን ሲል ደም ያፈሰሰ እና መስዋዕት ያቀረበ ራሱ እግዚአብሔር መሆኑ እንዴት የሚያስደንቅ ነው።✍እግዚአ...
09/06/2025

የኢየሱስ ክቡር ደም
✍ስለ ደም (መስዋዕት ) ስናነሳ የመጀመሪያው ሰውን ለመታደግ እና ለማዳን ሲል ደም ያፈሰሰ እና መስዋዕት ያቀረበ ራሱ እግዚአብሔር መሆኑ እንዴት የሚያስደንቅ ነው።
✍እግዚአብሔር ደም ያፈሰሰበት እና የራሱን መስዋዕት ያቀረበበት ምክንያቱ ለሰው ልጆች ያለው የራሱ ፍቅር ግድ ስላለው ነው።
✍አዳም እና ሔዋን በሀጥያት ከወደቁ በኃላ በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት ለማግኝት ከበለስ ቅጠልን አገልድመው በሀጥያት የመጣውን ሀፍረታቸውን ለመሸፈን ሞከሩ ነገር ግን የሰው ስራ(ሀይማኖት )ቋሚ የሆነ መፍትሄ አላመጣም። ዘፍ 3፡7
✍እግዚአብሔር ግን ለሰው ልጆች ካለው ፍቅር የተነሳ የራሱን መፍትሄ ተጠቀመ በኤደን ገነት (በአትክልቱ) ስፍራ ምንም የማያውቅ ንፁህ እንስሳ መስዋዕት አደረገ ከዛም ለአዳም እና ለሄዋን የታረደውን እንስሳ ቆዳ አለበሳቸው ገመናቸውንም ሸፈነላቸው። ዘፍ 3:21
✍ይህ ኤደን ገነት ላይ የአዳምን እና የሄዋንን(የሰው ልጆችን) ሞት የሞተው ገመናቸውንም በቆዳው የሸፈነ እንስሳ አካሉ በአዲስ ኪዳን ተገለጠ እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ዮሐ 1:29
✍ኢየሱስ ክርስቶስ በበጎች በረት የተወለደ የእግዚአብሔር በግ ነው።
✍መጥምቁ ዮሐንስም የአለምን ሀጥያት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ በማለት ጮኅ ዮሐ 1:29
✍ይህ በግ መስዋዕት መሆን ስላለበት ሐዋርያው ጳውሎስ ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአል አለ 1ቆሮ 5:7
✍በክርስቶስ ደም ከእድሜ ዘመን ሀጥያታችን እና ከእግዚአብሔር ቁጣ ስናመልጥ
በእግዚአብሄር ፊት እኛነታችን እንዳይታይ ደግሞ ክርስቶስን ለብሰነዋል ክርስቶስ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጽድቃችን ቅድስናችን ጥበባችን እና ቤዛነታችን ሆነ ።1ቆሮ 1:30
ገላትያ 3 27፤ ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና።
✍አዳምና ሔዋንን በደሙ ከእግዚአብሔር ቁጣ ቆዳውን በመልበስ በእግዚአብሔር ፊት በድፍረት የመቆም ብቃት ያገኙበት አማናዊው የእግዚአብሔር በግ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነው።
✍በብሉይ ኪዳን ለ1500 አመታት በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የእንስሳት ደም መስዋዕት ሆኖ ቢፈስም የአንድን ሰው ሀጥያት ማስወገድ ግን አልተቻላቸውም። የእግዚአብሔር አብን የጽድቅ ጥያቄ ሊመልሱለትም ሆነ ደስ ሊያሰኙት አልተቻላቸውም።
✍በአዲስ ኪዳን ግን በማያዳግም ሁኔታ አንዴ ለዘላለም መስዋዕት ሆኖ የቀረበው የእግዚአብሔር በግ ደም አለ።
የኢየሱስ ደም የሰወችን ሁሉ ሀጥያት በማስወገድ ለሚያምኑበት መፍትሔ የሆነ የእግዚአብሔር አብንም በሃጥያት ላይ የነበረውን በብሉይ ኪዳን ያልተመለሰለት የጽድቅ ጥያቄ የመለሰ አንዴ ለዘላለም የቀረበ መስዋዕት ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ እና ብቻ ነው። ዕብ 10:1-
♥ከዚህም የተነሳ በኢየሱስ ክርስቶስ ደም በማመናችን ምክንያት የተደረጉ እና የተቆጠሩልን በረከቶች ፦
በደሙ አዲስ እና ዘላለማዊ ኪዳን ተገባልን ሉቃ 22:20, ዕብ 13:20
በደሙ የእድሜ ዘመን የሀጢአት ስርየት አግኝተናል ..ሮሜ 3፡25, ሮሜ 4:6-7
በደሙ ከእግዚአብሔር ቁጣ ድነናል....ሮሜ 5፡8
በደሙ ፀድቀናል....ሮሜ 5፡9
በደሙ ቤዛነታችንን አግኝተናል.. .ኤፌ 1፡7, ቆላ 1፡14
በደሙ ሰላም አግኝተናል.. ....ቆላ 1፡19-20
በደሙ ወደ አባት እና ወደ ቅድስተ ቅዱሳን የመግባት ድፍረት አግኝተናል.... ኤፌ 2፡13, ዕብ 10፡19-20
በደሙ ተቀድሰናል ዕብ10:10
በደሙ የዘላለም ፍጹማን ሆነናል
ዕብ 10:14
በደሙ ከጥፋተኝነት , ከሚከስ አእምሮ ነፃ ወጥተናል..ዕብ 9፡13-14,
በደሙ ከሀጥያት ሁሉ ታጥበናል
ዮሐ 1:7
በደሙ ታጥበናል....ራዕ 1፡4-5
በደሙ ካህናት እና ነገስታት ተደርገናል
ራዕ 1:4-5, 5:10
በደሙ = ከነገድ (ከዘር) ሁሉ፤ ከቋንቋ ሁሉ፤ከወገን ሁሉ፤ከሕዝብ ሁሉ ተዋጅተናል፡፡ራዕ 5:10
✍ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል። ሮሜ 5:8

ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሣቱ ለሕያው ተስፋና ለማይጠፋ፥ እድፈትም ለሌለበት፥ ለማያልፍም ርስት እንደ ምሕረቱ ብዛት ሁለተኛ የወለደን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ፤...
19/04/2025

ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሣቱ ለሕያው ተስፋና ለማይጠፋ፥ እድፈትም ለሌለበት፥ ለማያልፍም ርስት እንደ ምሕረቱ ብዛት ሁለተኛ የወለደን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ፤ ይህም ርስት በመጨረሻው ዘመን ይገለጥ ዘንድ ለተዘጋጀ መዳን በእምነት በእግዚአብሔር ኃይል ለተጠበቃችሁ ለእናንተ በሰማይ ቀርቶላችኋል።1ኛጴጥ. 1 : 3-5

ክርስቶስ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር እንዲያቀርበን እርሱ ጻድቅ ሆኖ ስለ ዓመፀኞች አንድ ጊዜ በኃጢአት ምክንያት ሞቶአልና፤ በሥጋ ሞተ በመንፈስ ግን ሕያው ሆነ፥1ኛጴጥ.3 : 18

ዮሐንስ በእስያ ላሉት ለሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት፤ ካለውና ከነበረው ከሚመጣውም፥ በዙፋኑም ፊት ካሉት ከሰባቱ መናፍስት፥ ከታመነውም ምስክር ከሙታንም በኵር የምድርም ነገሥታት ገዥ ከሆነ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን። ለወደደን ከኃጢአታችንም በደሙ ላጠበን፥
መንግሥትም ለአምላኩና ለአባቱም ካህናት እንድንሆን ላደረገ፥ ለእርሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ክብርና ኃይል ይሁን፤ አሜን። ራእይ 1 : 4-6

ዳዊት የኢየሱስ ጥላ ?ዳዊት የሚለው የስሙ ትርጉም በእግዚአብሔር የተወደደ ማለት ነው።ኢየሱስም አባቱ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ብሎ መስክሮለታል✍ዳዊት የተወለደው በቤተልሔም ነው!!1...
12/03/2025

ዳዊት የኢየሱስ ጥላ
?
ዳዊት የሚለው የስሙ ትርጉም በእግዚአብሔር የተወደደ ማለት ነው።
ኢየሱስም አባቱ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ብሎ መስክሮለታል
✍ዳዊት የተወለደው በቤተልሔም ነው!!1ሳሙ 16:4
✍ ኢየሱስ የተወለደው በቤተልሔም ነው!! ማቴ 2:1
❤ዳዊት የበጎች እረኛ ነበር!! 1ሳሙ 16:11❤ኢየሱስ የበጎች እረኛ ነው!! ዮሐ 10:11
ዳዊት በወንድሞቹ መካከል ተቀብቷል!!1ሳሙ 16:13፤ኢየሱስ በወንድሞቹ መካከል ተቀብቷል!!
ሐሥ 1:46
✍ዳዊት በአባቱ ፈቃድ ታዞ ወደ ወንድሞቹ ተልኳል!! 1ሳሙ 17:17
✍ኢየሱስ በአባቱ ፈቃድ ታዞ ወደ ወንድሞቹ ተልኳል!! ዮሐ 8:42
ዳዊት ያለ ጥፋቱ ተወንጅሏል!! 1ሳሙ 17:28፤ኢየሱስ ያለ ጥፋቱ ተወንጅሏል!! ማቴ 27:12
✍ዳዊት ጎልያድ ፊት ሲቀርብ በእግዚአብሔር ተማምኗል!! 1ሳሙ 17:37
✍ኢየሱስ ወደ መስቀል ሞት ሲቀርብ በእግዚአብሔር ተማምኗል!! ማቴ 20:17-19
❤ዳዊት ብቻውን ጎልያድን ድል አድርጓል!!1ሳሙ 17:40-45❤ኢየሱስ ብቻውን ሞትን ድል አድርጓል!!
ዮሐ 16:32
ጎልያድ አንገቱ የተቆረጠው ዳዊትን ሊቆርጥበት በነበረው ሰይፍ ነው!! 1ሳሙ 17:50-53
ዲያብሎስ ስራው የፈረሰው ኢየሱስን ለማጥፋት ባዘጋጀው መስቀል ነው!! ቆላ 2:15
✍ዳዊት ጎልያድን በመግደል እስራኤልን ከባርነት አድኗል!! 1ሳሙ 17:9
✍ኢየሱስ ሞትን በመግደል ህዝቡን ከባርነት አድኗል!! ዕብ 2:14-15
❤ዳዊት ድል በመንሳቱ እስራኤላውያን ሁሉ ድል ነስተዋል!! 1ሳሙ 17:52
❤ኢየሱስ ድል በመንሳቱ በክርስቶስ የሆኑ ሁሉ ሞትን ድል ነስተዋል!! 1ቆሮ 15:55-57
✍ዳዊት ከስደት በኃላ በኬብሮን 7 ዓመት በኢየሩሳሌም ደግሞ የቀረ ዘመኑን ነግሷል1 ነገስት 2:1 ✍ኢየሱስም ለ 1,000 ሺ ዓመት በምድር ላይ የሚቀጥለውንም ዘላለም ከቤተክርስቲያን ጋር ይነግሳል:: ራዕይ 20:4, 22:5

ሜምፊቦስቴ የኢየሱስ ጥላ♥️የእግዚአብሔር በክርስቶስ የሆነውን የማዳን ስራ እንመለከታለን✍️ንጉስ ዳዊት እና ሜምፊቦስቴ ፦2ሳሙ 4፡4, 9፡4-13✍️ሜምፊቦስቴ የሳኦል የልጅ ልጅ የዮናታን ልጅ...
13/02/2025

ሜምፊቦስቴ የኢየሱስ ጥላ
♥️የእግዚአብሔር በክርስቶስ የሆነውን የማዳን ስራ እንመለከታለን
✍️ንጉስ ዳዊት እና ሜምፊቦስቴ ፦2ሳሙ 4፡4, 9፡4-13
✍️ሜምፊቦስቴ የሳኦል የልጅ ልጅ የዮናታን ልጅ ነው፡፡
ሽባ የሆነበትም ምክንያት የአያቱን እና የአባቱን ሞት የሰማች ሞግዚት ይዛው ለመሸሽ ስትሞክር ከእጇ በመውደቁ ነው፡፡
2ሳሙ 4፡4
✍️የሜምፊቦስቴ አያት የሆነው ሳኦል የንጉስ ዳዊት ቀንደኛ ጠላት እንደነበር ይታወቃል፡፡
✔️እንዲሁ የሰው ልጆች ምንጭ የሆነው አዳም በሀጥያት ምክንያት የእግዚአብሔር ጠላት ሆነ፡፡ ሮሜ 5፡9
✍️የሜምፊቦስቴ ሞግዚት ይዛው ልትሸሽ ስትሞክር ነው በ 5 አመቱ ወድቆ ሽባ የሆነው፡፡
✔️እንዲሁ የሰው ልጅ በክርስቶስ በማመን በፀጋ ብቻ እንጂ ሞግዚት በሆነው በሙሴ ህግ ህይወት ሊያገኝ እና ሊፀድቅ አይችልም፡፡
ገላ 2፡16, 3፡17-21,ሉቃ 14፡15
✍️የሜምፊቦስቴ አባት ዮናታን የንጉስ ዳዊት የልብ ጓደኛ ከመሆኑ የተነሳ ንጉሱ ስለ ዮናታን ቸርነት እና ምህረት ማድረግ ፈለገ፡፡ 2ሳሙ 9፡7
✔️እግዚአብሔር ለሀጢያተኛው ሰው በክርስቶስ በኩል ምህረት ማድረግ እና ከቁጣው ሊያድነው ፈለገ።
ዮሐ 3፡14-18,ሮሜ 3፡21,ሮሜ 4፡22- ,5:1, ኤፌ 2፡4-6
✍️ሜምፊቦስቴ ይኖር የነበረው ሎዶባር (ምድረበዳ) በሚባል ቦታ ነበር፡፡ 2ሳሙ 9፡4
✔️የሰው ልጅም በሀጥያቱ ምክንያት ከእግዚአብሔር መገኝት እና መግቦት ርቆ ይኖር ነበር፡፡ ኤፌ 2፡11, 1ጴጥ 2፡25
✍️ሜምፊቦስቴ ካለበት ቦታ ወደ ንጉስ ዳዊት እንዳይሄድ እግሩ ሽባ ነው ንጉስ ዳዊት ግን መልዕክተኛ በመላክ ወደ እርሱ እንዲመጣ አደረገው፡፡ 2ሳሙ 9፡1-2
✔️ሀጥያተኛ የሆነውም የሰው ልጅ በራሱ መልካም ስራ በአምላክ ፊት ተቀባይነት ማግኘት ስለማይችል እግዚአብሔር ግን በክርስቶስ ወደ ራሱ ማቅረብ ፈለገ፡፡ ኤፌ2፡8, ሮሜ 3፡21-24,ሮሜ 5፡6-10,
✍️ንጉስ ዳዊት ስለ ዮናታን ሲል ለሜምፊቦስቴ ቸርነትን በማድረግ
2ሳሙ 9፡7
1) እንደ ንጉስ ልጅ ሆነ
2) ከንጉሱ ጋ በማእድ ተቀምጦ ንጉሱ የሚበላውን በላ
3) በኢየሩሳሌም ከንጉሱ ጋር መኖር ጀመረ
4) የአያቱን ምድራዊ ርስት መለሰለት
✔️እንዲሁ እግዚአብሔር ለሀጥያተኛው በክርስቶስ ምክንያት
1) ልጅ አደረገው
2) በክብር በክርስቶስ በቀኙ አስቀመጠን
3) የሕይወት እንጀራ የሆነው ክርስቶስ ምግቡ ሆነለት
4) በአዲሲቱ ኢየሩሳሌም በክርስቶስ መኖር ጀመረ
5) በአዳም ምክንያት ያጣነውን ከዚያም በላይ በክርስቶስ ባረከን ፡፡ ኤፌ 1፡3, ዮሐ 1፡12,1ዮሐ 3፡1-,ዮሐ 6
ኤፌ 2:6-7,ዕብ12:22-24
ቅዱሳን ልብ ሊሉት የሚገባ ፦
✍️ሜምፊቦስቴ በንጉስ ዳዊት ቸርነት እንዲህ ቢሆንም አሁንም ግን #እግሩ #ሽባ #ነው፡፡
✔️ሰው በክርስቶስ አምኖ ከዳነ በኃላ ለመኖር መፍጨርጨር የለበትም ይልቅስ ጻዲቅ በእምነት በሕይወት ይኖራል፡፡

ዮሴፍ የኢየሱስ ጥላ   ?ዮሴፍ እረኛ ነበር ዘፍ 37:2፤ኢየሱስ እረኛ ነው ። ዮሐ 10:11❤️ዮሴፍ በአባቱ የተወደደ ነበርዘፍ 37:3፤❤️ኢየሱስ በአባቱ የተወደደ ነው ማቴ 3:17♦️ዮሴፍ ...
31/12/2024

ዮሴፍ የኢየሱስ ጥላ
?
ዮሴፍ እረኛ ነበር ዘፍ 37:2፤ኢየሱስ እረኛ ነው ። ዮሐ 10:11
❤️ዮሴፍ በአባቱ የተወደደ ነበርዘፍ 37:3፤❤️ኢየሱስ በአባቱ የተወደደ ነው ማቴ 3:17
♦️ዮሴፍ ያለ ምክንያት በወንድሞቹ ተጠልቷል ዘፍ 37:4-8፤♦️ኢየሱስ ያለ ምክንያት በወንድሞቹ ተጠልቷል ማር 3:21 ዮሐ 7:5
ዮሴፍ በአባቱ ፈቃድ ወደ ወንድሞቹ ምግብ ይዞ ተላከ ዘፍ 37:13፤ኢየሱስ በአባቱ ፈቃድ ወደ ወንድሞቹ ምግብ ሆኖ ተላከ ዮሐ 8:42
ዮሴፍን ተሳልቀውበታል ዘፍ 37:19፤ኢየሱስን ተሳልቀውበታል ሉቃ 22:63-65
ዮሴፍን ልብሱን ገፈውታል ዘፍ 37:23፤ኢየሱስን ልብሱን ገፈውታል ዮሐ 19:23-24
❤️በይሁዳ ሀሳብ ዮሴፍ በ 20 ብር ተሽጧል ዘፍ 37:26-28፤❤️ይሁዳ ኢየሱስን በ30 ዲናር ሽጧል።
ማቴ 26:14-16
ዮሴፍን ታላቅ የሆነው ሮቤል ሊታደገው ሞክሯል ። ዘፍ 37:21፤ኢየሱስን መሪ የሆነው ጲላጦስ ሊታደገው ሞክሯል። ዮሐ 19:12
♦️ዮሴፍ ባሪያ ሆኗል ዘፍ 39:1-2♦️ኢየሱስ ባሪያ ሆኗል። ማቴ 20:28 ፊሊ 2:7
❤️ዮሴፍ በሀሰት ተመስክሮበታል ዘፍ 39:14❤️ኢየሱስ በሀሰት ተመስክሮበታል ማቴ 26:59-62
ዮሴፍ የበደሉትን ይቅር ብሏል ዘፍ 45:4 ኢየሱስ የበደሉትን ይቅር ብሏል ሉቃ 23:34
ከዮሴፍ ጋር ከታሰሩት አንዱ ወንጀለኛ ድኗል ሌላኛው ሙቷል ዘፍ 40:1-3 ኢየሱስ ጋር ከተሰቀሉት አንዱ ወንጀለኛ ድኗል ሌላኛው ሙቷል። ሉቃ 23:32-33
ዮሴፍ ከውርደቱ በላኃ ከብሯል ዘፍ 41:41 ኢየሱስ ከውርደቱ በኃላ ከብሯል ሉቃ 24:26 & ፊሊ2:9-11
❤️ዮሴፍ ህዝብን ከርሀብ አዳኝ ሆኗል ዘፍ 45:5 & 47:25❤️ኢየሱስ ህዝብን ከሞት አዳኝ ነው።ማቴ 1:21 & 1ዮሐ 4:14
ዮሴፍ ወደ ደረቅ ጉድጓድ በወንድሞቹ መጣሉ ደግሞም ከጉድጓድ መውጣቱ ዘፍ 37:24 ኢየሱስ ወደ ሞት አሸዋ መውረዱ ደግሞም መነሳቱ ማቴ 27፡60, ሐሥ 2:38, 1ቆሮ 15:1-
♦️ዮሴፍ በህይወት እንዳለ ያዕቆብ አላመነም ነበር ። ዘፍ 45:26♦️ኢየሱስ በህይወት እንዳለ ደቀመዛሙርቱ አላመኑም ነበር። ሉቃ 24:10-11 & ማር 16:9-12
ዮሴፍ ከኪዳን ውጪ የሆነችውን አስናትን አገባ። ዘፍ 41:45፤ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን ምስጢየነበረችውን ቤተክርስቲያንን የራሱ አደረገ። ኤፌ 5:30
❤️ዮሴፍ ከፈርኦን ጋር በሰረገላ ተቀመጠ በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ ተሾመ ዘፍ 41:40-43❤️ኢየሱስ በአባቱ ቀኝ በዙፋን ተቀመጠ ኤፌ 1:20-22
ዮሴፍ በመጨረሻ አባቱን እና ወንድሞቹን አገኛቸው ከርሃብ አዳናቸው ዘፍ 46:1 ኢየሱስ የእስራኤላውያን ከቅሬታ ከመከራው ዘመን በማዳን ለ 1ሺ አመት ከቤተክርስቲያን ጋር ይነግሳል። ራዕ 20:3-6

The great gift of God! Download and repost! It is the message of Ethiopia full gospel believers church!
27/12/2024

The great gift of God! Download and repost! It is the message of Ethiopia full gospel believers church!

Address

Hawassa
Hawassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hawassa chaffe full gospel believers church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category