Shinshicho MKC

Shinshicho MKC ከተመሠረተው በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሠርት አይችልም፤ እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። 1 ቆሮ. 3:11

የሺንሺቾ ምስራቅ መሠረተ ክርስቶስ ቤተ-ክርስቲያን የአምልኮ አዳራሽ ተመረቀ ።       የሺንሽቾ ምሠራቅ መሠረተ ክርስቶስ ቤተ-ክርስቲያን በ 35 ዓመታት የፅናት ጉዞ ውስጥ ተሻግራ ዘመናዊ ...
15/03/2026

የሺንሺቾ ምስራቅ መሠረተ ክርስቶስ ቤተ-ክርስቲያን የአምልኮ አዳራሽ ተመረቀ ።

የሺንሽቾ ምሠራቅ መሠረተ ክርስቶስ ቤተ-ክርስቲያን በ 35 ዓመታት የፅናት ጉዞ ውስጥ ተሻግራ ዘመናዊ የአምልኮ አዳራሽ በድምቀት አስመረቀች።

በ 1980 ዓ.ም በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት በአራት ልጆች ህብረት የተጠነሰሰችው የሺንሺቾ ምስራቅ መሠረተ ክርስቶስ ቤተ-ክርስቲያን የሦስት አስርተ ዓመታት የፅናትና የዕድገት ጉዞዋን የሚያበስር ታላቅ የዘመናዊ አምልኮ አዳራሽ የምረቃ መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ አከናውናለች።

ቤተ-ክርስቲያኒቱ ላለፉት 32 ዓመታት ስትጠቀምበት የነበረውን አሮጌ አዳራሽ በዘመናዊ ህንፃ ለመተካት በሚያዝያ 17 ቀን 2015 ዓ.ም ግንባታዋን መጀመሯ የሚታወስ ሲሆን በእግዚአብሔር ረዳትነትና በምዕመናን ያላሰለሰ ጥረት ተገንብቶ የተጠናቀቀው ይህ ዘመናዊ የአምልኮ አዳራሽ ዛሬ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ የምስጋና ስነ-ስርዓት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

ግንባታው ሁለት ዓመት ከ አስር ወር የፈጀ ሲሆን በዋንኛነት በምዕመናን የገንዘብ፣ የጉልበትና የቴክኒክ ድጋፍና እገዛ የተገነባ ነው። ሕንፃው ከ 27 ሚልየን ብር በላይ በ ገንዘብ፣ በአይነት እና በጉልበት እንደወጣበት አቶ ሙሉጌታ ወዖሜ የሕንፃው አሰሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ገልፀዋል።

በምረቃው ስነ-ስርዓቱ ላይ የሺንሺቾ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ መለሰ ገብሬ ፣ የቃጫ ቢራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ማቴዎስ ኤርቃሎ ፣ የሺንሺቾ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ዋና ተጠሪ ኢ/ር ቢኒያም ጴጥሮስን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ የፊት አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ፣ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ፣ የቤተክርስቲያኒቱ መስራች አባቶችና እናቶች፣ የተለያዩ አቢያተ ክርስቲያናት ተወካዮችና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ተከናውኗል።

ቤተ ክርስቲያኒቱ ካለፈችባቸው ዋና ዋና ታሪካዊ ክንውኖች መካከል በ1980 ዓ.ም በአራት ልጆች ህብረት የተጀመረች ሲሆን ግንቦት 19 ቀን 1981 ዓ.ም በሰባት አማኞች ወደ ስርጭት ጣቢያነት በማደግ በ1986 ዓ.ም ሙሉ አጥቢያ ለመሆን በቅታለች።

ባለፉት 35 ዓመታት የእምነቱ አባቶች በብዙ መከራና ተጋድሎ ውስጥ በማለፍ የክርስቶስን ወንጌል ለትውልድ እያስተላልፉ የቆዩ ሲሆን ይህም ጥረት ፍሬ አፍርቶ ዛሬ ላይ ዱራሜ፣ ሀደሮ፣ ሙዱላ እና የሺንሽቾ ምዕራብን ጨምሮ ከ18 በላይ አጥቢያዎችንና የስርጭት ጣቢያዎችን ማፍራት መቻሏ ተገልጿል።

ይህ የምረቃ መርሃ-ግብር ቤተ ክርስቲያኒቱ ለደረሰችበት ከፍተኛ የዕድገት ደረጃ ምስክርነት የሰጠ ሲሆን በቀጣይም ለማህበረሰቡ የምታበረክተውን ሁለንተናዊ አገልግሎት አጠናክራ እንደምትቀጥል አመላክቷል።

“እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገልን፥ ደስም አለን።"            መዝ126፥3🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏  የሺንሽቾ ምስራቅ መሠረተ ክርስቶስ ቤተ-ክርስቲያን የአምልኮ ሕንፃ የቤተክርስቲያኒቱ...
14/03/2026

“እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገልን፥ ደስም አለን።" መዝ126፥3
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

የሺንሽቾ ምስራቅ መሠረተ ክርስቶስ ቤተ-ክርስቲያን የአምልኮ ሕንፃ የቤተክርስቲያኒቱ ምዕመናን ፣ መስራች አባቶች እና እናቶች ፣ የአቢያተ ክርስቲያናት ተወካዮች ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ምዕመናን እና የሺንሺቾ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነገ ዕለተ እሁድ 07/07/2018 ዓ.ም በታላቅ የምስጋና ዝግጅት ታስመርቃለች።

14/03/2026

“እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገልን፥ ደስም አለን።" መዝ126፥3
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

ነገ ዕለተ እሁድ 06/07/2018 ዓ.ም ኑ ከእኛ ጋር እግዚአብሔር አመስግኑ !!

14/03/2026

“እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገልን፥ ደስም አለን።" መዝ126፥3
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

“እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገልን፥ ደስም አለን።"            መዝ126፥3🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏1980 ዓ.ም በአንድ ግለሰብ ቤት በአራት ልጆች ህብረት በማድረግ ተጠነሠሠች የዛሬዎ ...
14/03/2026

“እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገልን፥ ደስም አለን።" መዝ126፥3
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

1980 ዓ.ም በአንድ ግለሰብ ቤት በአራት ልጆች ህብረት በማድረግ ተጠነሠሠች የዛሬዎ የሺንሺንቾ ምስራቅ መሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን።

በመቀጠልም በግንቦት 19/1981 ዓ.ም በሰባት አማኞች ወደ ስርጭት ጣቢያነት አደገች። የክርስቶስ ወንጌል እየሰፋ አማኞችም እየተጨመሩ በ 1986 ዓ.ም ወደ ሙሉ አጥቢያ ለመሆን በቃች።

የሺንሺቾ ምስራቅ መሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ባለፉት 35 ዓመታት አባቶች በብዙ መከራና ተጋድሎ ከሐዋሪያት የተቀበሉትን የክርስቶስን ወንጌል እየሰበከች፣ብዙዎችን ወደ መዳን እየጠራች እና የክርስቶስ ትምህርት እያስተማረች ደቀመዝሙር እያደረገች እስከ ዛሬ ቀጥላለች።

ከተመሠረተችበትም ጊዜ አንስቶ የዱራሜን ፣ የሀደሮን ፣ የሙዱላን ፣ የሺንሺቾ ምዕራብ መሠረተ ክርስቶስን ጨምሮ ከ 18 በላይ አጥቢያና የስርጭት ጣቢያ አፍርታለች።

በሚያዚያ 17 2015 ዓ.ም ከ 32 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን የአምልኮ አዳራሽ በአዲስ ዘመናዊ የአምልኮ አዳራሽ ለመተካት አሃዱ ብላ ጀመረች።

እግዚአብሔርን በመተማን የጀመረችውን በእግዚአብሔር ዕርዳታ በመጨረስ ነገ መጋቢት 06/07/2018 የቤተክርስቲያኒቱ ምዕመናን ፣ መስራች አባቶች እና እናቶች ፣ የአቢያተ ክርስቲያናት ተወካዮች ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ምዕመናን እና የሺንሺቾ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በታላቅ የምስጋና ዝግጅት ታስመርቃለች።

 ከእነርሱም ሰው ሁሉ ልቡ እንዳነሣሣው መንፈሱም እሺ እንዳሰኘው ለመገናኛው ድንኳን ሥራ ለማገልገያውም ሁሉ ለተቀደሰውም ልብስ ለእግዚአብሔር ስጦታ አመጡ።ዘጸአት 35:21ወንድማማቾቹ (ምህረቱ...
10/03/2026


ከእነርሱም ሰው ሁሉ ልቡ እንዳነሣሣው መንፈሱም እሺ እንዳሰኘው ለመገናኛው ድንኳን ሥራ ለማገልገያውም ሁሉ ለተቀደሰውም ልብስ ለእግዚአብሔር ስጦታ አመጡ።
ዘጸአት 35:21

ወንድማማቾቹ (ምህረቱ ጴጥሮስ & ማሬ ጴጥሮስ)
🙏🙏🙏

🗓 ይህ ለነገ ዕለተ ረቡዕ መጋቢት 02/2018 ብቻ የሚቆይ የአብሮነት ጥሪ ነው።

ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ለሚሠራ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይግባውና የመስኮት መጋረጃ ግዥ ጥሪ ባቀረብን በጥቂት ቀናት ውስጥ ብዙዎች ለጥሪው ምላሽ ሠጥተዋል።

የተቆረሱ ቅዱሳንን እየባረክን፤ ላቀረብነው ጥሪ መቆረስ እየፈለጉ ነገር ግን ባለፉት ጥቅት ቀናት በተለያዩ ምክንያቶች ዕድሉን ላላገኙ ለአንድ ቀን ብቻ የሚቆይ ዳግመኛ ጥሪ ስናቀረብ ከመጨረሻው በረከት እንዲካፈሉ ካለን ጥልቅ መሻት ነው።

እግዚአብሔር ይባርካችሁ፣ ያገልግላችሁም 🙏

   ።  " ከእነርሱም ሰው ሁሉ ልቡ እንዳነሣሣው መንፈሱም እሺ እንዳሰኘው ለመገናኛው ድንኳን ሥራ ለማገልገያውም ሁሉ ለተቀደሰውም ልብስ ለእግዚአብሔር ስጦታ አመጡ።"ዘጸአት 35:21ቤተ-ክር...
07/03/2026





" ከእነርሱም ሰው ሁሉ ልቡ እንዳነሣሣው መንፈሱም እሺ እንዳሰኘው ለመገናኛው ድንኳን ሥራ ለማገልገያውም ሁሉ ለተቀደሰውም ልብስ ለእግዚአብሔር ስጦታ አመጡ።"
ዘጸአት 35:21

ቤተ-ክርስቲያን ላቀረበችው ጥሪ
✍️ ሰብስቤ ማርቆስ ከ 🇿🇦 - 3 መጋረጃ
✍️ ስሙ ያልተጠቀሰ ከ 🇺🇸 - 3 መጋረጃ
✍️ ቡሽሮ ቡናሮ ከ 🇿🇦 - 2 መጋረጃ
✍️ ተገኝ ታገሰ ከ 🇿🇦 - 1 መጋረጃ
✍️ መስራች ኤርሚያስ - 1 መጋረጃ
✍️ ኤፍሬም ታምራት- 1 መጋረጃ
✍️ ምህረቱ ደጀኔ - 1 መጋረጃ ወጪ በመሸፈን ለቤተ-ክርስቲያን ጥሪ በፍቅር ምላሽ ተሰጥተዋል ።

እግዚአብሔር ይባርካችሁ ይጠብቃችሁም፤ እግዚአብሔር ፊቱን ያብራላችሁም፤ ይራራላችሁም እግዚአብሔር ፊቱን ይመልሳላችሁ፤ ሰላሙንም ይስጣችሁ ። ተባረኩ 🙏

   ።  " ከእነርሱም ሰው ሁሉ ልቡ እንዳነሣሣው መንፈሱም እሺ እንዳሰኘው ለመገናኛው ድንኳን ሥራ ለማገልገያውም ሁሉ ለተቀደሰውም ልብስ ለእግዚአብሔር ስጦታ አመጡ።"ዘጸአት 35:21ቤተ-ክር...
06/03/2026





" ከእነርሱም ሰው ሁሉ ልቡ እንዳነሣሣው መንፈሱም እሺ እንዳሰኘው ለመገናኛው ድንኳን ሥራ ለማገልገያውም ሁሉ ለተቀደሰውም ልብስ ለእግዚአብሔር ስጦታ አመጡ።"
ዘጸአት 35:21

ቤተ-ክርስቲያን ላቀረበችው ጥሪ

✍️ ሰማየሱስ አለሙ - 1 መጋረጃ
✍️ ፀጋዬ ተፈራ - 1 መጋረጃ
✍️ ቢኒያም ጴጥሮስ - 1 መጋረጃ
✍️ ሙሉቀን ተገኝ- 1 መጋረጃ
✍️ ቸርነት ኃ/መሪያም - 1 መጋረጃ ወጪ በመሸፈን ለቤተ-ክርስቲያን ጥሪ ምላሽ ተሰጥተዋል ።

እግዚአብሔር ይባርካችሁ ይጠብቃችሁም፤ እግዚአብሔር ፊቱን ያብራላችሁም፤ ይራራላችሁም እግዚአብሔር ፊቱን ይመልሳላችሁ፤ ሰላሙንም ይስጣችሁ ። ተባረኩ 🙏

    " ከእነርሱም ሰው ሁሉ ልቡ እንዳነሣሣው መንፈሱም እሺ እንዳሰኘው ለመገናኛው ድንኳን ሥራ ለማገልገያውም ሁሉ ለተቀደሰውም ልብስ ለእግዚአብሔር ስጦታ አመጡ።"ዘጸአት 35:21የእግዚአብሔ...
05/03/2026



" ከእነርሱም ሰው ሁሉ ልቡ እንዳነሣሣው መንፈሱም እሺ እንዳሰኘው ለመገናኛው ድንኳን ሥራ ለማገልገያውም ሁሉ ለተቀደሰውም ልብስ ለእግዚአብሔር ስጦታ አመጡ።"
ዘጸአት 35:21

የእግዚአብሔር ፀጋ እና ሠላም ይብዛላችሁ እያልን የከበረ ሠላምታችንን እናቀርባለን።

የተወደዳችሁ ቅዱሳን ሆይ የእግዚአብሔርን ቤት ሥራ በብዙ እየደገፋችሁ አብራችሁን ስለቆማችሁ ደግመን ደጋግመን እያመሰገንን ፤ እግዚአብሔርም በበረከቱ እንዲጎበኛችሁ የዘወትር ልመናችን ነው።

የመስኮት መጋረጃ ግዥ የሚሆን እንጠይቃችሁ ዘንድ ተገደን ዳግም ፈታችሁ ቆመናል። አጠቃላይ የመጋረጃው ግዥ ዋጋ 150,000 ብር ሲሆን በግል፣ በቡድን፣ በቤተሰብ ትደግፉን ከስር ባለው መሠረት አሠናድተናል።

ይህንን አፋጣኝ ጥሪ
☞ 20 ሰው-- 7,500 ብር = 150,000 ብር
☞ 30 ሰው-- 5,000 ብር = 150,000 ብር
☞ 50 ሰው--3,000 ብር = 150,000 ብር
☞ 60 ሰው-- 2,500 ብር = 150,000 ብር
☞ 100 ሰው - 1,500 ብር = 150,000 ብር
☞ 150 ሰው--1,000 ብር =150,000 ብር

ለዚህ አፋጣኝ ጥሪ አቅም በፈቀደው ሁሉ ከቤቱ ስራ ጎን ትቆሙ ዘንድ ዛሬም እንደ ትናንቱ የፍቅር ጥሪ እናቀርባለን ።

!
እግዚአብሔር ይባርካችሁ ፣ ያገልግላችሁም።

ምላሻችሁን screen Shoot በማድረግ inbox አድርጉልን 🙏

"አቤነዘር ፥ እስከዛሬ ድረስ ፥ እግዚአብሔር ረድቶናል!"
05/03/2026

"አቤነዘር ፥ እስከዛሬ ድረስ ፥ እግዚአብሔር ረድቶናል!"

እነሆ ሚያዚያ 17/2015 ዓ.ም ቤተ ክርስቲያን ለአዲሱ የአምልኮ አዳራሽ ህንፃ ግንባታ የመሬት ቁፋሮ ለመከወን ቀጠሮ ይዛ ምዕመኗን እየጠበቀች ነው:: ከማለዳ ጀምሮ ዝናብ መጣል በመጀመሩ ህ...
05/03/2026

እነሆ ሚያዚያ 17/2015 ዓ.ም ቤተ ክርስቲያን ለአዲሱ የአምልኮ አዳራሽ ህንፃ ግንባታ የመሬት ቁፋሮ ለመከወን ቀጠሮ ይዛ ምዕመኗን እየጠበቀች ነው:: ከማለዳ ጀምሮ ዝናብ መጣል በመጀመሩ ህዝቡ አይመጣ ይሆን የሚል ትንሽዬ ስጋት ፈጥሮ ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔር የላከው አይቀርምና ዝናብ ያለ እስካይመስል ወጣቶች ፣ አባቶች ፣ እናቶች እንዲሁም ህፃናት ሳይቀሩ መቆፍሪያ ይዘው ማለዳ ተገኙ። የዚህም ትልቅ ህንፃ የመሬት ቁፋሮ ሥራ በአንድ ቀን ጥንቅቅ ብሎ ተጠናቆ በምስጋና ስንለያይ እግዚአብሔር የራሱን ቤት በተዓምር እንደሚሠራው አረጋገጠልን። ከዚህያ ወዲያ የነበረው በተዓምራቱ ብቻ የሆነ ታሪክ ነው።

ባለፉት ሶስት ዓመታት እግዚአብሔር ሲያደርግልን የነበረውን ግሩም እና ዕጅን በአፍ የሚያስጭን ሥራ በተከታታይ ልጥፎች ስናጋራችሁ ስለነበር እናንተም ስለ እግዚአብሔር ታማኝነት ምስክር ናችሁ።

ኦ! አቤቱ አንተ እንዴት ድንቅ ነህ!

የእግዚአብሔርን ባለጠግነት በመታመን ብቻ የጀመርነው የህንፃ ግንባታ ሥራ ሊጠናቀቅ ጥቂት አዳራሹ የማስዋብ ሥራዎች ብቻ ይቀራሉ።

ከእነዚህም ሥራዎች የመጨረሻው የሆነውን ለመስኮት መጋረጃ ግዢ እንደገና እየለገሳችሁ ከሥራው ጎን እንድትቆሙ ዘንድ ዳግም የመባረኪያ መንገድ እያቀረብን እግዚአብሔር ቢፈቅድና በህይወት ብንኖር መጋቢት 6/2018 ዓ.ም የቤተ ክርስቲያኒቱ ምዕመናንና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት እግዚአብሔርን ስለ ተዓምራቱ የምናመሰግንበት የምስጋና ዝግጅት ይኖረናል።

ስለሆነም የአንዱ መጋረጃ ዋጋ 5 ሺህ ብር ሲሆን ፤ እግዚአብሔር ልባችሁ ላይ በሞላው መጠን በመታዘዝ ትቆረሱ ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን።

Address

Durame
SHINSHICHO

Telephone

+251941001459

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Shinshicho MKC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Shinshicho MKC:

Share