Divine Radiant International Ministry

Divine Radiant International Ministry Divine Radiant International Ministry

ለእስራኤል   ይገደኛል መዝሙረ  122:6-9 " እንዲህ ብላችሁ ለኢየሩሳሌም ሰላም ጸልዩ፤ “የሚወድዱሽ ይለምልሙ፤     በቅጥርሽ ውስጥ ሰላም ይሁን፤ በምሽግሽም ውስጥ መረጋጋት ይስፈን”። ...
02/10/2025

ለእስራኤል ይገደኛል

መዝሙረ 122:6-9

" እንዲህ ብላችሁ ለኢየሩሳሌም ሰላም ጸልዩ፤ “የሚወድዱሽ ይለምልሙ፤
በቅጥርሽ ውስጥ ሰላም ይሁን፤ በምሽግሽም ውስጥ መረጋጋት ይስፈን”።
ስለ ወንድሞቼና ስለ ባልንጀሮቼ፣ “በውስጥሽ ሰላም ይስፈን” እላለሁ።
ስለ አምላካችን ስለ እግዚአብሔር ቤት፣ በጎነትሽን እሻለሁ።"

ደረሰ! ደረሰ!! ደረሰ! በመጀመሪያ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ለምትገኙ ቤተሰቦቻችን ሁሉ  እንኳን ለአዲሱ ዓመት 2018 አደረሳችሁ  እያልን   የፊታችን እሁድ መስከረም 10/2018 ...
17/09/2025

ደረሰ! ደረሰ!! ደረሰ!

በመጀመሪያ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ለምትገኙ ቤተሰቦቻችን ሁሉ እንኳን ለአዲሱ ዓመት 2018 አደረሳችሁ እያልን
የፊታችን እሁድ መስከረም 10/2018 " የአሰባበክ ዘዴ " (Homiletics) ኮርስ እግዚአብሔር በዚህ ዘመን ለምድራችን ካስነሳቸው ፍሬያማ አስተማሪ ከሆኑቴ በቄስ ግርማ በየነ ይሰጣል ስለዚህ:-👇👇

✍️ " የእውነትን ቃል በቅንነት የሚናገር የማያሳፍርም ሰራተኛ ሆነህ የተፈተነውን ራስህን ለእግዚአብሔር ልታቀርብ ትጋ"
2ኛ ጢሞ 2:15
👉 ዲቫይን ራዲያንት ቲዮሎጂካል ኮሌጅ በዲፕሎማና ድግሪ መርሐ ግብር በኦንላይን ማስተማር ጀምረናል
ስለዚህ በመንፈስ ቅዱስና በቃሉ ታጥቀንና ተዘጋጅተን እግዚአብሔር የሚያከብር ሕይወት ትውልድ የሚያንጽ ጠቃሚ ሰው ለመሆን በዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ እንድትማሩ እድል በራችሁን እያንኳኳች ነው በመሆኑም ይህን ዕድል ተጠቀሙበት። እድል ሁልጊዜ አይገኝምና
መመዝገብ የምትፈልጉ በዚህ ስልክ ዛሬውኑ ይደውሉ 092 021 7243 ፓ/ር ዳንኤል መኮነን

ቅዳሜ የመንፈስ ቅዱስ ጉብኝት   ኢሳይያስ 60 :1-2" ብርሃንሽ መጥቶአልና፥ የእግዚአብሔርም ክብር ወጥቶልሻልና ተነሺ፥ አብሪ። እነሆ፥ ጨለማ ምድርን ድቅድቅ ጨለማም አሕዛብን ይሸፍናል፤ ነ...
28/07/2023

ቅዳሜ የመንፈስ ቅዱስ ጉብኝት
ኢሳይያስ 60 :1-2

" ብርሃንሽ መጥቶአልና፥ የእግዚአብሔርም ክብር ወጥቶልሻልና ተነሺ፥ አብሪ። እነሆ፥ ጨለማ ምድርን ድቅድቅ ጨለማም አሕዛብን ይሸፍናል፤ ነገር ግን በአንቺ ላይ እግዚአብሔር ይወጣል ክብሩም በአንቺ ላይ ይታያል፤
ነገ ሐምሌ 21/2015 ከጥዋቱ 3-8 ሰዓት በዲቫይን ራዲያንት ሚስዮናዊት ቸርች የመንፈስ ቅዱስ ጉብኝት በፓ/ር ግርማ ከበደ የጸሎትና የትምህርት ጊዜ ተዘጋጅቷል
ስለዚህ ሁላችንም ተጋብዘናል
አድራሻ :- ጉርድ ሾላ ባቡር መሻገሪያ ላይ ትህትና ህንጻ ጀርባ ባጃጅ ከሚቆሙበት ጎን ያለው ህንጻ ላይ
አገልጋይ መጋቢ ግርማ ከበደ

 ለወንጌል አገልግሎት ወደ ጀርመን ሀገር ለመስበክ የተጋበዘው ወንጌላዊ ቦንኬ ገና በማለዳው ካረፈበት ሆቴል የእግር ጉዞ ካደረገ በኋላ አንድ መናፈሻ ገብቶ አረፍ አለ።አጠገቡ አንድ በሀያዎቹ ...
07/06/2022



ለወንጌል አገልግሎት ወደ ጀርመን ሀገር ለመስበክ የተጋበዘው ወንጌላዊ ቦንኬ ገና በማለዳው ካረፈበት ሆቴል የእግር ጉዞ ካደረገ በኋላ አንድ መናፈሻ ገብቶ አረፍ አለ።አጠገቡ አንድ በሀያዎቹ የሚገመት አንድ ወጣት ፀሐይ ሲሞቅ አየ። ረዘም ያለውን ዝምታ የሰበረ ንግግር ተናገርኩኝ ሁልጊዜም እንደማደርገው ይህን አጋጣሚ የወንጌሉን የምስራች ለመናገር ስለፈለኩኝ "የማለዳው ፀሐይ እንዴት ናት? ብዬ ዝምታውን ሰበርኩኝ።
ወጣቱ ልጅ:" ቆንጆ ነው በጣም ደስ ይላል" አለኝ

ቦንኬ: "ይህን ውብ ፀሐይ በነፃ የሰጠን ማን እንደሆነ ታውቃለህ? አልኩት

ወጣቱ ልጅ: " አላውቅም" አለ

ቦንኬ: "መጽሐፍ ቅዱስ ታነባለህ? "አልኩት
ወጣቱ ልጅ: " ፊቱን ጭፍግግ አድርጎ አላነብም ለምን አነባለሁ መጽሐፍ ቅዱስ እኮ ያረጀ መጽሐፍ ነው። እንደምታየኝ እኔ ወጣት ነኝ። የ21 ክፍለ ዘመን ሰው ነኝ ወጣት ነኝ ለእኔ የሚመጥኑ አዳዲስ ፍልስፍናዎችን ያየዙ መጽሐፍትን አነባለሁ እንጂ ያረጀ እና ዘመን ያለፈበትን መጽሐፍ ቅዱስ ምን ሊያደርግልኝ አነባለሁ" አለኝ

ቦንኬ: ጥቂት ሰኮንዶች ዝም ካልኩኝ በኋላ የውይይቱን አቅጣጫ የቀረኩኝ በማስመሰል " አሁን እዚህ ምን ትሰራለህ" አልኩት

ወጣቱ ልጅ:ዘና ብሎ እንደምታየው ፀሐይ እየሞኩኝ ነው አለኝ

ቦንኬ:ቆፍጠን ብዬ ፀሐይ ለምን ትሞቃለህ እንደ አንተ አይነቱ የ21 ክፍለ ዘመን ወጣት ይህችን አሮጌ ፀሐይ መሞቅ አልነበረበትም።የፀሐይ እድሜ ብዙ ሚለየን አመት እንደሆነች ከሳይንስ እንደተማከርክ እርግጠኛ ነኝ።ስለዚህ እንደ አንተ አይነቱ ወጣት አዲስ ነገር መፈለግ ይኖርበታል እንጂ አሮጌ ነገር መፈልግ አይኖርበትም በማለት በማፌዝ ተናገርኩት። ወጣቱ ግራ በመጋባት ማዳመጥ ጀመረ። ቦንኬም በመቀጠል "አየህ ፀሐይ እድሜዋ ረዥም ቢሆንም ዛሬም ብርህን ትሰጣለች ፣ ሙቋቷ አልቀነሰም ፣ ድምቀቷ አልቀነሰም።ዘር፣ ቀለም ፣ሃይማኖት ሳትለይ ለሁሉ ታበራለች።መጽሐፍ ቅዱስ እንደዚህ ነው።ዛሬም ለሰው ዘር ሁሉ ያበራል ፣ ነፃ ያወጣል ፣ ይለውጣል ።የፀሐይ ብርሃን ወደ አንተ የመጣው ከ93 ሚሊየን ማይልስ ርቀት ነው።አንተ ግን ወደ ፀሐይ ለመድረስ ብዙ አልተጓዝክም።ሲነጋ ለፀሐይ በርህን ከፍተህ አሁን ደግሞ ወጥተህ በፀሐይ ፊት ተቀምጠህ ሁለተናህን ለፀሐይ ብርሃኗ እና ለሙቀቷ ሰጠህ። የእግዚአብሔርም ቃል ከአንተ የሚጠበቀው ይሄ ነው። ልብህን ለቃሉ እና ለኃይሉ ብርሃን ክፈት በውስጡ ላለው እውነቱ ራስህን ስጥ "
ወጣቱም ልጅ: ፊቱ በርቶ ደስ ብሎት መስማት ቀጠለ
የእግዚአብሔር ቃል አያረጅም ዛሬም ይሰራል ፣ ለዘላለም ህያው ነው። ከቃሉ የሚመነጨው ብርሃን በውስጥ የተዳፈነውን እምነት እና ተስፋ ቀስቅሶ ወደ ዘላለም ህይወት ይመራል። መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል ነው። የህይወታችን መመሪያችን እንዲሆን ሁልጊዜም ከምንም ነገር በላይ ጊዜ ሰጥተን ልናጠናው፣ ልናሰላስልው ይገባል።

ድንቅ ቀን!!!!!!!      መዝ   118:24 "   እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን።"            ዛሬ የመኖር ውድ ዋጋ ከሚተመንባቸው...
02/06/2022

ድንቅ ቀን!!!!!!!

መዝ 118:24
" እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤
ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን።"

ዛሬ የመኖር ውድ ዋጋ ከሚተመንባቸው፣ ከሚታወቅባቸው፣ ከሚገለጥባቸው ውብ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በዚህም አያበቃም ዳሩ ግን የውብ አስደሳች ቀናት፣ ዋጋ ያላቸው ህይወትን የሚያበሩና፣ የሚያደምቁ፣ ከፍ የሚያደርጉ፣ የተባረኩ ሌሎች ቀናትም ይመጣሉ።

ወዳጆቼ..! ደማቅ ቀናት የኛ ናቸው! የተሰጡት፣ የተላኩት ለኛ ነው። እንድንደምቅባቸው፣ እንድንዋብባቸው፣ እንድንደሰትባቸው ከአምላክ ተበርክተውልናል። በተጨማሪም :-
መዝ 139:14
" ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ፤
ሥራህ ድንቅ ነው፥ ነፍሴም እጅግ ታውቀዋለች።"

እንዲህ በሉ ...አምላኬ ከእኔ ጋር ነው ፤ እንደ ሁል ጊዜው ዛሬም ቀኔ ነው ።" ይህን ስትል ማፈር አይጠበቅብህም ፤ ማንም ሰው ይህን ሊልህ እንደማይመጣ አስታውስ ። እግዚአብሔር የሰጠህን ቀን፤ ውብ እንድትሆን አድርጋት። በቅዱስ ቃሉና በጸሎት አቅምህን አጎልብት ፤ አሳድግ። የድልነሽነትን፣ የአንጸባራቂነትን፣ የሞገስን ስብዕና አዳብር። ውስጥህ ያለውን የእግዚአብሔርን ጸጋና ቅባት በሙላት እንዲለቀቅ ራስህን ክፍት በማድረግ ጌታ እንዲጠቀምበት ፍቀድለት።

ቀናት በቀናት ሲተኩ ፣ ሌላ አዲስ እለት ሲከሰት በሰላም ፣ በጤና ሆኖ መመልከት ቀላል አይደለም። ቃላት የማይገልፁት ፣ ሊነገር የማይችል ከስጦታዎች ሁሉ ከላቀው ስጦታ ዋንኛውና አንደኛው ነው። አዲሱ ቀንህን በፍፁም አታባክነው ፤ ዋጋውን አታሳንሰው ፤ ደማቁን ቀን አታፍዝዘው ፤ ይበልጥ ድመቅበት። ከአምላክህ ጋር ተጣበቅበት።
ነገ የዛሬ ልጅ ናትና ዛሬን በአግባቡ ተጠቀምባት፤ የነገዋ ሌላ ናት። ዛሬን ደግመን አናጠኛትምና ዛሬ የዘራነውን ነገ እናጭዳለን፣ የዛሬዋ ቀን በጌታ ነገር ለመደሰት፣ ለመፍካት፣ ለማጣጣም ሌላ የቀጠሮ ቀን አትስጣት። ህይወትህን በደስታ፣ ቀናትህን በእርካታ ለመኖር ደግሞ ቁልፉ ሚስጥር ቃሉን በማንበብ በመጸለይ በአምልኮና በምስጋና ሆነህ ማሳለፍ ነው።
መዝ 27:4
" እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንሁት እርስዋንም እሻለሁ፤
በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፥
እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውንም አይ ዘንድ፥ መቅደሱንም እመለከት ዘንድ።"

መንፈሳዊ መነቃቃት (Revival)                  እንዴት ይመጣል???        ለመንፈሳዊ መነቃቃት ወይም ለመለኮታዊ ጉብኝት መሟላት የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎች እንዳሉ ይታወቃል...
16/05/2022

መንፈሳዊ መነቃቃት (Revival)
እንዴት ይመጣል???

ለመንፈሳዊ መነቃቃት ወይም ለመለኮታዊ ጉብኝት መሟላት የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎች እንዳሉ ይታወቃል።
ልዩ የሆነ መንፈሳዊ ጉብኝት ወይም ሪቫይቫል በግለሰብ ደረጃ በቤተክርስቲያን እና በሀገር ደረጃ እንዲሆን የሰው ድርሻ ወሳኝ ነው።
ከሰው የሚጠበቀው መንፈሳዊ ርሃብ: ጥማትና ምጥ(እርግዝና) ነው
ኢሳይያስ 44:3
" በተጠማ ላይ ውኃን በደረቅም መሬት ላይ ፈሳሾችን አፈስሳለሁና፤ መንፈሴን በዘርህ ላይ በረከቴንም በልጆችህ ላይ አፈስሳለሁ፥"
በተጠማ ላይ እርካታን የሚሰጥ እግዚአብሔር ሲሆን መሻቱና ጥማቱ ግን የሰው ድርሻ ነው።
ዮሐንስ 7: 37
" .. ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ። በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል።"
ስለዚህ ሀገርችንን ትውልዳችንን ሊታደግ የሚችል መለኮታዊ ጉብኝት እንዲሆን በብርቱ ርሃብና ጥማት የአምላካችንን ፊት አብዝተን እንፈልግ
*ሉቃስ 11:10, 13
" የሚለምን ሁሉ ይቀበላልና፥ የሚፈልግም ያገኛል፥ መዝጊያውንም ለሚያንኳኳው ይከፈትለታል። .... በሰማይ ያለው አባት ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መንፈስ ቅዱስን ይሰጣቸው?
ሪቫይቫል እንዲመጣ ከላይ ያየናቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ሃሳቦች በቅድሚያ መሆን ይገባዋል እነዚህ ምጥ:ርሃብና ጥማት በሌለበት ሁኔታ ጉብኝት ሊሆን አይችልም።
በ20ኛው ክ/ዘመን በታላቋ ብሪታኒያ (ስኮትላንድ) የተከሰተው መነቃቃት ህዝብን እንደ ሞገድ ወደ ቤ/ክ እንዲተምም ያደረገው ምክንያት ጆን ኖክስ የተባለ ሰው በነፍሱ ተወራርዶ እንዲህ በማለት ወደ አምላኩ ጸለዬ " ስኮትላድን ስጠኝ አለበለዚያ ግደለኝ" አለ። በተጨማሪም ሚስቱን ወይ እግዚአብሔር ይመጣልኛል አለዚያም እሬሳዬ ይወጣል " በማለት በመጾም ከእንጀራ ጋርና ከእንቅልፍ ጋር ተጣልቶ አብዝቶ በመጮኽ ስኮትላንድን ለክርስቶስ አስወረሳት።
በ1904 በዌልስ ምድር የተከሰተው ሪቫይቫል በአንድ የድሃ ቤተሰብ ከተገኘ ብዙ የትምህርት ዝግጅት በሌለው ኢቫን ሮበርትስ ምጥና ርሃብ የተነሳ ነው። አውሮፓን ያጥለቀለቀው እስከ 20 ሚሊዮን ለሚሆን ህዝብ እንደ ሰደድ እሳት የተመመ ታላቅ ጉብኝት ነው።
የተወደዳችሁ የጽሁፌ ቁም ነገር " በሚገኝበት ፈልጉት ቀርቦም ሳለ ጥሩት" ኢሳ 55:6 እንደሚል ምጥ: ርሃብና ጥማት ሲኖረን ከሰማይ እንጎበኛለን።
ሐዋ. ሥራ 2:17
" እግዚአብሔር ይላል፦ በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ፤"
ፓ/ር ዳንኤል መኮነን

"የመንፈስ ቅዱስ እሳት "       ዘጸአት 40:38 "   በመንገዳቸውም ሁሉ በእስራኤል ቤት ሁሉ ፊት የእግዚአብሔር ደመና በማደሪያው ላይ በቀን ነበረና፥ እሳትም በሌሊት በዚያ ላይ ነበረና...
08/05/2022

"የመንፈስ ቅዱስ እሳት "

ዘጸአት 40:38
" በመንገዳቸውም ሁሉ በእስራኤል ቤት ሁሉ ፊት የእግዚአብሔር ደመና በማደሪያው ላይ በቀን ነበረና፥ እሳትም በሌሊት በዚያ ላይ ነበረና። "
ክርስትና በመንፈስ ቅዱስ ሃይልና ደስታ በማይቋረጥ ሁሌም በሃልዎቱ ውስጥ ሁነን የምንኖረው ሕይወት ነው።
በብሉይ ኪዳን ዘመን እሳት የፍርድ ምሳሌ ብቻ ሳይሆን፡ የኃይልና የክብር የድል ምሳሌ ነው። እሳቱ ይመራቸው ነበር እሳቱ ይዋጋላቸው ቅጥራቸውም ጭምር ነበረ … " እኔ በዙሪያዋ የእሳት ቅጥር እሆንላታለሁ፥ በውስጥዋም ክብርን እሆናለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር። " ዘካ 2:5
እግዚአብሔር ራሱ እንደ እሳት እየተገለጠ ጠላቶቻቸውን ያጠፋቸው ነበር :- ዘዳግም 9:3
" አምላክህም እግዚአብሔር እንደሚበላ እሳት ሆኖ በፊትህ እንዲያልፍ ዛሬ እወቅ፤ እርሱ ያጠፋቸዋል፥ በፊትህም ያዋርዳቸዋል፤ እግዚአብሔርም እንደ ነገረህ አንተ ታሳድዳቸዋለህ፥ ፈጥነህም ታጠፋቸዋለህ።"

"………እግዚአብሔር ባሪያዎቹን በመንፈስ ቅዱስ እሳት ነክቶ ከአሰልቺና ከድግግሞሽ እንዲሁም ፍሬ ከሌለው ባዶ ድካም ይታደጋቸዋል።" አገልጋዮቹንም የእሳት ነበልባል የሚያደርግ "
እብ 1:7

" ……እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል፤ "ማቴዎስ 3:11 .....ታዲያ መፍትሔው ወደ አጥማቂው ሁልጊዜም መቅረብ መራብና መጠማት አንኳኩ መንፈስ ቅዱስ ትቀበላላችሁ ብሏል ሉቃ 11:13
" ………በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ፤ ለጌታ ተገዙ፤" ሮሜ 12:11
ከመንፈሳዊ ድንዛዜ ወጥተን ሕይወታችን በግለት እንዲቀጥል ሁል ጊዜ ትኩስ(fresh) እንዲሆን በመንፈስ ቅዱስ እሳት የተቀጣጠለ ሊሆን ያስፈልጋል
" ...ስለዚህ ምክንያት፥ እሳት እንደሚያቀጣጥል ሰው፥ እጆቼን በመጫኔ " 2ኛ ጢሞ 1:6
" ሰው ሁሉ በእሳት ይቀመማልና፥ መሥዋዕትም ሁሉ በጨው ይቀመማል።" ማርቆስ 9:49
ስለዚህ ትርጉም ያለው ሕይወት እና በመልካም ተፅእኖ የተሞላ ኑሮ እንድንኖር እሳቱን እንቀበል። መፍትሔ አልባ ከሆነ ንትርክና ጭቅጭቅ ወጥተን በመንፈስ ቅዱስ እሳት እንቀጣጠል።
ጥሪያችን ሰዎችን ከፍርድና ከጥፋት እሳት አውጥተን ወደ በረከትና ደስታ ወደ ሞላበት የመንፈስ ቅዱስ እሳት ማነሳሳት ነው::
እንዲህ አይነት ክብር ውስጥ ለመግባት ፍሬ ከሌለው ከማንኛውም ሕብረት ራሳችንን በመጠበቅ ከጨለምተኛ እይታ ካላቸው ራሳችንን በመጠበቅ ነው::
የተወደዳችሁ ያባቴ ብሩካን የመንፈሱንእሳት በብርቱ እንሻ
ፓ/ር ዳንኤል

28/04/2022

አስደናቂው ታሪክ
ጥቂት ስለ ኤሚ ማክፐርሰን

ኤሚ ማክ ፐርሰን እግዚአብሔር ይዟት ከነበረው በሽታ ጣልቃ ገብቶ ነጻ እንዳወጣት ከአዲስ የመለኮት ራእይ ጋር ተጋጠመች፡፡ ዛሬ በአለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቀውን እዛው ኒውዎርክ the Foursquare Gospel ቤተክርስቲያንን መሰረተች፡፡ እዛው በበሽታ ማቃ ልትሞትበት በነበረው የኒዎርክ ከተማ ውስጥ በእግዚአብሔር የእንደገና ምህረት ተነስታ KFSG የተባለ የወንጌል ራዲዮ ጣቢያ መሰረተች፡፡ ከሁለት ዓመት በኋላ ደግሞ ማለትም በ1926 ዓ.ም Lighthouse of International Foursquare Evangelism (L.I.F.E.) Bible Collegeን አቋቋመች፡፡
ኤሚ ማክ ፐርሰን በልጅነት ዘመኗ እምብዛም በትምህርት የገፋች አልነበረቺም፡፡ እንደ ዘመኑ የሥነ መለኮት ሊቃውንት በርካታ አውደ እውቀቶችን አላገላበጠቺም፡፡ የአገልግሎቷ ልዕቀት ያረፈው በእጇ ላይ ባለው የመጽሐፍ ቅዱስና በእርሷ ውስጥ ካደረው ክቡሩ የእግዚአብሔር መንፈስ የተነሳ ነው፡፡ በርካታ የአገልግሎት መድረኮች ላይ ቆማ ስትናገር በነገረ መለኮት ትንታኔዋ በአሰባበክ ሳቢነቷ አለማዊያን ሚዲያ ሳይቀሩ አንገታቸውንና ጆሮአቸውን ወደ እርሷ አስግገው ቃሏን ያደምጡ ነበር፡፡ በአንድ ወቅት ኤሚ ማክ ፐርሰን በዘመኑ አቆጣጠር 1925 ዓ.ም ላይ ሎስ አንጀለስ ከተማ አደባባይ ላይ በመቶ ሺህ ለሚቆጠሩ ሠዎች የወንጌል ቃል እያካፈለች ባለቺበት ሠዓት ነበር፡፡ ከዚህ የተነሳ በአንድ ወቅት ኒዎርክ ሎስ አንጀለስ የሚገኝ አለማዊ ሚዲያ በፊት ለፊት የመጽሔት ሽፋኑ ላይ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡-
ሲል ዘግቧል፡፡
የኤሚ ማክ ፐርሰን መሳጭ ቃለ እግዚአብሔር በሀሳብ ላይ ብቻ የዋለለ አልነበረም፡፡ ቃሏ ከዛሬ 2000 ዓመት በፊት እንደነበሩት እንዲሁም በአሜሪካና በካናዳ በእርሷ ዘመን እንደተነሱት የእግዚአብሔር ሠዎች በተግባር የታጀበ ነበር፡፡ ለምሳሌ ከላይ በገለጽነው የሎስ አንጀለስ ታላቅ የህዝብ አደባባይ ላይ በአንድ ጊዜ አገልግሎቷ ብቻ ከአስር ሺህ በላይ የሚሆኑ ሠዎች ሀኪም በማስረጃ ባቀረበላቸው በሽታና ህመም በክርስቶስ ኢየሱስ ስም በዚህች የእግዚአብሔር ሴት አገልግሎት ተፈውሰዋል፡፡ ከመቶ 90 የሚሆኑት እነዚህ ታማሚዎች በማክ ፐርሰን አገልግሎት የተፈወሱት በፀሎት ሳይሆን እላይዋ ላይ ከነበረው ብሎም በቆመቺበት ሥፍራ ከሚሰማው ኃልወተ እግዚአብሔር የተነሳ ነበር፡፡ ያም ብቻ አይደለም እርሷ በቆመቺበት መድረክ ላይ አጋንንት ፍፁም መቆም አይችልም፤ በታላቅ ኃይል እየጮኹ ከሠዎች ውስጥ ይወጡ ነበር፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ያልተሞሉ ቅዱሳን ሠዎችን መንፈስ ቅዱስን እየተሞሉ በአዲስ ቋንቋ ይናገሩና የፀጋ ሥጦታዎች በህይወታቸው ላይ ይገለጥ ነበር፡፡ የሪቫይቫል ታሪክ ፀሐፊዎች ማክ ፐርሰን ወደዚህ የአገልግሎት ክብር የገባቺው መንፈስ ቅዱስ ላይ መቶ ከመቶ ባላት ፍፁም መደገፍ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ኤሜ ማክ ፐርሰን ቅዱሳን ወገኖች ገንዘብ አዋጥተው የገዙላትን የዘመኑን ባለ አራት ጎማ ተሸከርካሪ መኪና ላይ ኢየሱስ ያድናል የሚል ትልቅ ባነር ለጥፋ በየአደባባዩና በየመንገድ ዳር ላይ በቀስታ እያሽከረከረች በትልቅ ሜጋ ፎን ወንጌልን ለሠዎች ትመሰክር ነበር፡፡

አይጥለንም አይረሳንምም    ዘዳ 4 :31፤ አምላክህ እግዚአብሔር መሐሪ አምላክ ነውና አይተውህም፥ አያጠፋህምም፥ ለአባቶችህም የማለላቸውን ቃል ኪዳኑን አይረሳም። "የጠጅ አሳላፊዎች አለቃ ግ...
11/04/2022

አይጥለንም አይረሳንምም
ዘዳ 4 :31፤ አምላክህ እግዚአብሔር መሐሪ አምላክ ነውና አይተውህም፥ አያጠፋህምም፥ ለአባቶችህም የማለላቸውን ቃል ኪዳኑን አይረሳም።
"የጠጅ አሳላፊዎች አለቃ ግን ዮሴፍን አላሰበውም፥ ረሳው እንጂ።" ዘፍጥ 40: 23

ለእውነት ወግነህ እና በጽድቅ እየኖርክ መረሳት ልብን ያደክማል፡፡ ከማድከምም አልፎ ልብን የሚሰብረው ደግሞ ያጭበረበሩ ተርፎአቸው በብዙሃንም ታጅበው ወደ አደባባይ ባቀኑበት ዘመን የእግዚአብሄርን ፊቱን ፈርተው አመጻን እምቢ ያሉ ልብሳቸውን ተገፈው ወደ እስር ቤት መወርወራቸው ነው።
በተሰማሩበት ታምነው እና የብዙዎችን ህልም ፈተው በፋንታው መረሳት የእውነተኞች ፍጻሜ ሳይሆን ከቀድሞው የተሻለ ወደ ሚጠቅሙበት ለመድረስ ከእስር ቤቱ ወደ ቤተ መንግስቱ የሚሻገሩበት ጠባቡ መንገድ ነው።
በጠጅ አሳላፊው መረሳት ለዘላለም ሳይሆን ትውልዱ ቅዠቱን እስኪጨርስ እና ንጉሱ እስኪያልም ድረስ ነው። ባንተ የሚፈታው ህልም እስኪታለም ከቅባትህ ጋር ለበጎ ተረስተህ ብትቆይም የንጉሱን ህልም ትፈታ ዘንድ በችኮላ ከእስር የምትፈታበት ጊዜ በደጅ ነውና እያለፍክበታ ባለው መንገድ አትድከም።
ንጉሱም ዮሴፍን ልኮ አስጠራው!!!
በነገር ሁሉ ትኩረት እና መፈለግን የምናገኝበት፡ ለመልካም የምንታሰብበት ወራቱ ገባ!!!!
ዘዳ 31 :8 በፊትህም የሚሄድ እርሱ እግዚአብሔር ነው፤ ከአንተ ጋር ይሆናል፥ አይጥልህም፥ አይተውህም፤ አትፍራ፥ አትደንግጥ፡ አለው።
አሜን !!!!!

ከማንነት ቀውስ የሚፈውስ ምክር   ማንነትን ማወቅ ጽናት እንዲኖርህ ያደርጋል ከውጭ ወደ ውስጥ ሳይሆን ከውስጥ ወደ ውጭ የምትመለከት ስለምትሆን   ለውጪው  ነገር መጫወቻ አትሆንም።  በመጽሐ...
05/04/2022

ከማንነት ቀውስ የሚፈውስ ምክር

ማንነትን ማወቅ ጽናት እንዲኖርህ ያደርጋል ከውጭ ወደ ውስጥ ሳይሆን ከውስጥ ወደ ውጭ የምትመለከት ስለምትሆን ለውጪው ነገር መጫወቻ አትሆንም። በመጽሐፍ ቅዱሳችን የኢያሱንና የካሌብን ታሪክ ለዚህ ሃሳብ ጥሩ ምሳሌ ሊሆነን ይችላል። ( ዘህ 14 :24 )

♥ በህይወት ውስጥ ትልቁ ስህተት ለሁሉም ሰው ትክክለኛ ሆኖ ለመታየት መሞከር ነው። መልካም ብትሆን ክፉዎች ይጠሉሀል። አዋቂ ብትሆን አላዋቂዎች ባዶነታቸውን ስለምትገልጥባቸው አብዝተው ይፀየፉሀል። ብርሃናዊ ራዕይ ቢኖርህ የጨለምተኞችን ጨለማ ስለምታሳይ መኖርህ ያንገበግባቸዋል። ነፃ አውጭ ብትሆን ጨቋኞች ያሳድዱሀል። ምናለፋህ በአለም ስትኖር በሙሉ ድምፅ ልትወደድም፣ ልትጠላም አትችልም። ስለዚህ በደረስክበት ሁሉ ልክ እንደ ውሃ ቅርፅህን አትቀያይር! ከምንም በላይ በፈጣሪህ ፊት ትክክል ሁን!"
አንድ ነገር ልንገራችሁ … በህይወታችሁ ማንንም አትውቀሱ ጥሩ ሰዎች ደስታን ይሰጡዃችዋል። መጥፎ ሰዎች ልምድ ይሆኑዃችሀል። ክፉ ሰዎች ማስጠንቀቂያ ይሆኑዃችዋል። ምርጥ ሰዎች ትዝታ ይሆኑዃችዋል።

♥ ሁሌም ቢሆን ለሌሌች መልካም አድርግ፣ ጥሩ ተናገር፣ ለበጎ ነገር አስብ ያኔ በጎ ነገሮች ባላሰብከው መልኩ ወደ ህይወትህ ይመጣሉ።

♥ ሰዎች ሲተቹህ፣ ሲሰድቡህና ሲጮሁብህ በጭራሽ ግድ አይስጥህ፤ አስተውል በእግር ኳስ ሜዳ የሚጮሁት ተጫዎቾቹ ሳይሆን ተመልካቾች ናቸው።

ምንጭ ካነበብኩት(unknown source)

21/03/2022

Address

Dese

Telephone

+251920217243

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Divine Radiant International Ministry posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Divine Radiant International Ministry:

Share