Bishoftu/Debre Zeit Emmanuel United Church

Bishoftu/Debre Zeit Emmanuel United Church ራዕያችን ሕዝቦች ሁሉ በክርስቶስ ወንጌል በሁለንተናዊ መልኩ ተለውጠው ማየት ነው! Our Vision: To See Transformed People by gosple of Christ In Holostic Way!
(1)

በመከራ ላሉት ጸጋና ሰላም ይብዛ!ክፍል 21ኛዼጥሮስ 1:2እግዚአብሔር አብ አስቀድሞ ካወቃቸው፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ለመታዘዝ በደሙ ለተረጩትና በመንፈስ አማካይነት ለተቀደሱት፤ጸጋና ሰላም ይብዛ...
25/05/2026

በመከራ ላሉት ጸጋና ሰላም ይብዛ!
ክፍል 2
1ኛዼጥሮስ 1:2
እግዚአብሔር አብ አስቀድሞ ካወቃቸው፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ለመታዘዝ በደሙ ለተረጩትና በመንፈስ አማካይነት ለተቀደሱት፤
ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።
✝️ሐዋሪያው ዼጥሮስ ይህን መልዕክት የጻፈው በተለያየ ፈተናና ስደት ለሚኖሩ አይሁድና አህዛብ አማኞች ሲሆን በሚያልፉበት ፈተና ሊያበረታታቸውና መከተል ስላለባቸው መርህ ሊያሳስባቸው ይጥራል። የተለያየ ምድራዊ ፈተናዎችን እየተጋፈጡ ቢሆንም አይናቸውን በሰማያዊና ዘላለማዊው ተስፋ ላይ እንዲያማትሩ ይጎተጉታል። በተለየ መንገድ ይህን ሰማያዊ ተስፋ የሚጎናፀፉት በጌታችን ዳግም መምጣት ስለሆነ ለምጽዓቱ ጉጉት እና ናፍቆት እንዲያድርባቸው አይናቻውን ከምድር ያላቅቃል።
👉ምንም እንኳ እነዚህ አማኞች በሰው አይን ሲታዪ ስደተኞችና ሀገር አልባ ቢመስሉም ዼጥሮስ ግን በአስደናቂ ማንነት ገላጭ በሆነ ሃሳብ ይጠራቸዋል። ይኸህም “የእግዚአብሔር ምርጦች” ይላቸዋል። ይህ አጠራር ለአይሁድ አማኞች የተለየ ስሜት ይፈጥርባቸዋል። ምክንያቱም በብሉይ ኪዳን ዘመን እስራኤል በዓለም ላይ ካሉ ህዝቦች ሁሉ የተመረጠች ነበረች። እግዚአብሔር የድነት ሃሳቡን ለመግለጥ የተጠቀመበት ህዝብ ነበር። ይህም የኪዳኑ ህዝብ አድርጓታል። ዘጸ 19:5-6 ዘዳ 7:6 ዘዳ 14:2
✍️ልክ እንዲሁ በአዲስ ኪዳን በመጀመሪያው ክፍለ ዘመን የነበሩትን አይሁድና አህዛብ ክርስቲያኖች “የተመረጡ ህዝቦች” እንደሆኑና በክርስቶስ ደም አማካይነት በጋራ ተሳታፊ እንደሆኑ በመንገር የምስራችን በማወጅ ይጀምራል።
ይህ ህዝብ በስደትና በመከራ ውስጥ እያለፈ ቢሆን በእግዚአብሔር የተመረጠ ምርጥ ህዝብ እንዲሆን ያደረገው ምንድነው ስንል:- በስላሴ የተሰራ ስራ እንደሆነ ይገልጻል። ይኸውም:-
1. በእግዚአብሔር አብ አስቀድሞ የታወቀ
ይህ አስቀድሞ መታወቅ የሚለው በግሪክ “ፕሮግኖሲስ” ሲባል ትርጓሜውም “አስቀድሞ መታወቅ” ብቻ ሳይሆን “ጥልቅ ግንኙነትንና መለኮታዊ ንድፍን” ያመለክታል። ይህ ግንኙነት የተመሰረተው በክርስቶስ በማመንና በመስቀል ላይ በፈሰሰው ደም ነው።
2. ኢየሱስ ክርስቶስን ለመታዘዝ በደሙ የተረጨ
የአዲስ ኪዳን ማህበረሰብ አይሁድ ይሁን አህዛብ በክርሰቶስ በመስቀል ላይ በተሰራ ስራ በደሙ የተረጨ ነው። በደሙ ወደ አብ መቅረብን ብቻ ሳይሆን ክርስቶስን ለመታዘዝም ጭመር ነው። ይህ የደም መርጨት የተከናወነው በእንስሳት ደም (ዘጸ 24:3-7) ሳይሆን በሚልቀው በኢየሱስ የአዲስ ኪዳን ደም ነው። (ሉቃ 22:20)
3. በመንፈስ አማካኝነት መቀደስ
እነዚህ የአዲስ ኪዳን አማኞች በደሙ ስለተረጩ በመንፈስ ቅዱስ ተቀድሰዋል ይላል። ስለዚህ ያለምንም ኩነኔና ክስ በአብ ፊት የመቆም ድፍረት አላቸው። ከዚህ የተነሳ እንዚህን አማኞች “የእግዚአብሔር ምርጦች” ይላቸዋል።
⚓️ እንግዲህ እነዚህን አማኞች ነው በአንድነት “ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ” የሚለው። ጸጋና ሰላም ማለቱ በጉባኤዎቹ ውስጥ አህዛብና አይሁድ መኖራቸውን ያመለክታል። ምክንያቱም አይሁድን የሚወክለው ሰላምታ “ሻሎም” የሚለው ሲሆን አህዛብን የሚወክለው ደግሞ “ጸጋ” የሚለው ነው።

የህይወት ተዛምዶ
ይህ ክፍል ለዛሬ አንባቢዎች ምን ያስተምረናል?
1. በየትኛውም የህይወት ፈተና ውስጥ ብንሆንም በእግዚአብሔር መመረጣችንን ዘወትር እናስብ 1ኛቆሮ 1:26
2. በአብ አስቀድሞ መታወቃችን፣በጌታ ደም መረጨታችን እንዲሁም በመምፈስ ቅዱስ መቀደሳችን ከማጉረምረም አውጥቶ በየዕለቱ ለክርስቶስ ለመታዘዝ ይምራን።
3. ፈተናው እንደማያጠፋን በስላሴ ምክር ውስጥ እንደተያዝን እና በጸና ህይወት እንደተመሰረትን በማወቅ እንበርታ

ክፍል 3 ይቀጥላል…!

ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን!
መጋቢ ወንድወሰን ለማ

“በመከራ ውስጥ ያለ ተስፋና ቅድስና” የ1ኛዼጥሮስ መልዕክት ጥናትክፍል 1የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ጴጥሮስ፤በጳንጦስ፣ በገላትያ፣ በቀጰዶቅያ፣ በእስያና በቢታንያ ተበትነው በመጻተኝነት ለሚኖሩ...
22/05/2026

“በመከራ ውስጥ ያለ ተስፋና ቅድስና”
የ1ኛዼጥሮስ መልዕክት ጥናት
ክፍል 1

የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ጴጥሮስ፤
በጳንጦስ፣ በገላትያ፣ በቀጰዶቅያ፣ በእስያና በቢታንያ ተበትነው በመጻተኝነት ለሚኖሩ ለእግዚአብሔር ምርጦች፤
1 ጴጥሮስ 1፥1

መግቢያ
የመልዕክቱ ታሪካዊ ዳራና አጠቃላይ ዕይታ
1. የተጻፈበት ጊዜ:- ከ60-67 ዓ.ም እንደሆነ ይገመታል።
2. ጸኃፊው:- ሐዋሪያው ዼጥሮስ ሲሆን የግሪክ አጻጻፉን ስንመለከት በጣም ጥሩ ግሪክ ስለሆነ ምናልባት ጸሐፊ ተጠቅሞ ይሆናል። ከዚህ የተነሳ ሲላስ የሚባለው ስልዋኖስ ጽፎለት ሊሆን ይችላል።
3. የተጻፈው:- ከሮም ሲሆን የብዕር ስም ወይም ምስጢራዊ በሆነ አገላለጽ በመጠቀም ባቢሎን እያለ ይጠራታል።
4. የመልዕክቱ ተቀባዮች:- በዘመናዊዋ ተርክዬ የሚገኙ አምስት የሮማን ግዛቶች ውስጥ ለተበተኑ መጻተኛ ስደተኛ አይሁድና አህዛብ አማኞ ነበሩ።
5. አድራሻዎች:- እስያ፣ቢታኒያ፣ገላቲያ፣ዻንጦስና ቀዸዶቂያ የተበተኑ መጻተኞች:-
- ከምድራቸው ውጪ በሌላ ምድር የሞኖሩ
- ከሰማያዊው ሀገር ውጪ በምድር የሚኖሩ
6. ጭብጥ:- ክርስቲያኖች ባላቸው የበለጸገ መንፈሳዊ እድሎች እና በክርስቶስ ዳግም ምጽአት ጊዜ የሚጠብቃቸውን የክብር የወደፊት ጊዜ እንዲያዩና በእግዚአብሔር ጸጋ እንዲደሰቱ የሚያበረታታ ነው።
7. ዓላማ:- ፈተናዎችን ሲጋፈጡ ክርስቲያኖችን ለክርስቶስ በታማኝነት እንዲኖሩ ለማነሳሳት። አሁን ባለው ህይወት ውስጥ ተቃውሞ እና መከራ እንዲቋቋሙ ለማሳሳብ ነው።
የዚህ መልዕክት መዋቅር
1. መግቢያ 1:1-2
2. ማበረታታት- በእግዚአብሔር ምህረት የተገኘ የአማኞች ማንነትና ስፍራ 1:3-12
በፊት 3-5
አሁን 6-9
ወደፊት 10-12
3. ማሳሰብ- በመጠበቅ ውስጥ ለቅድስና የቀረበ ጥሪ 1:13-2:3
4. ማበረታታት- የማንነት ዕድሎችና ሌሎችን ማገልገል 2:4-10
5. ማሳሰብ- በማያምን ዓለም የአማኞች ኃላፊነት 2:11-3:12
6. ማበረታታት- በመከራ ለወደቁ ምሪትን መስጠትና ማጽናናት 3:13-4:19
7. ማሳሰብ- ለሽማግሌዎችና ለጎልማሶች የተሰጠ ምክር 5:1-11
8. መዝጊያ 5:12-14

ክፍል 2 ይቀጥላል…!
በመጋቢ ወንድወሰን ለማ

 #እሁድ!!!🔥🔥
22/05/2026

#እሁድ!!!🔥🔥

 !
21/05/2026

!

19/05/2026
19/05/2026


 #ዛሬ! ! !!!!✝️✝️🔥🔥
17/05/2026

#ዛሬ!
!
!!!!✝️✝️🔥🔥

ከዚህ ሁሉ በኋላ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) አብርሃምን ፈተነው፤ “አብርሃም!” አለው። እርሱም “አቤቱ አለሁ” አለ።እግዚአብሔርም (ኤሎሂም)፣ “የምትወድደውን አንዱን ልጅህን፣ ይስሐቅን ይዘህ ወ...
16/05/2026

ከዚህ ሁሉ በኋላ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) አብርሃምን ፈተነው፤ “አብርሃም!” አለው። እርሱም “አቤቱ አለሁ” አለ።
እግዚአብሔርም (ኤሎሂም)፣ “የምትወድደውን አንዱን ልጅህን፣ ይስሐቅን ይዘህ ወደ ሞሪያ ምድር ሂድ፤ እኔ በማመለክትህ በአንዱ ተራራ ላይ የሚቃጠል መሥዋዕት አድርገህ ሠዋው” አለው።
በማግስቱም ጧት አብርሃም ማልዶ ተነሣ፤ አህያውን ጭኖ፣ ሁለት አገልጋዮቹንና ልጁን ይስሐቅን ይዞ፣ ለመሥዋዕት የሚበቃውን ዕንጨት ከቈረጠ በኋላ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ወዳመለከተው ቦታ ለመሄድ ጕዞውን ጀመረ፤ በሦስተኛው ቀን አብርሃም ቀና ብሎ ቦታውን ከሩቅ ተመለከተ፤ አገልጋዮቹንም “እናንተ አህያውን ይዛችሁ እዚህ ቈዩን፤ እኔና ልጄ ግን ወደዚያ ሄደን ለእግዚአብሔር ሰግደን እንመለሳለን” አላቸው። አብርሃም ለሚቃጠል መሥዋዕት የሚሆነውን ዕንጨት ወስዶ፣ ልጁን ይስሐቅን አሸከመው፤ እሳቱንና ቢላዋውንም ራሱ ያዘ። ሁለቱም አብረው ሄዱ። ይስሐቅም አባቱን አብርሃምን፣ “አባቴ ሆይ” አለው።
አብርሃምም፣ “እነሆኝ፤ አለሁ ልጄ” አለው።
ይስሐቅም፣ “እሳቱና ዕንጨቱ ይኸው፤ ነገር ግን የሚቃጠለው መሥዋዕት የት አለ?” ብሎ ጠየቀ።
አብርሃምም፣ “ልጄ ሆይ፤ ለሚቃጠለው መሥዋዕት የሚሆነውን በግ እግዚአብሔር ያዘጋጃል (ኤሎሂም ይሬህሎ)” አለው። ሁለቱም አብረው ጕዟቸውን ቀጠሉ።
እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ወደ አመለከተው ቦታ እንደ ደረሱ፣ አብርሃም መሠዊያ ሠራ፤ በላዩም ላይ ዕንጨት ረበረበ፤ ልጁን ይስሐቅንም አስሮ በመሠዊያው ዕንጨት ላይ አጋደመው። ከዚያም ልጁን ለማረድ እጁን ዘርግቶ ቢላዋውን አነሣ። የእግዚአብሔር (ያህዌ) መልአክ ግን ከሰማይ፣ “አብርሃም፤ አብርሃም፤” ብሎ ጠራው፤
አብርሃምም፣ “እነሆ፤ አለሁ” አለ።
እርሱም፣ “እጅህን በብላቴናው ላይ አታሳርፍ፤ ምንም ጕዳት አታድርስበት፤ እነሆ፤ እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) እንደምትፈራ ተረድቻለሁ፤ ልጅህን፣ ያውም አንዱን ልጅህን ለእኔ ለመስጠት አልሳሳህምና” አለው።
አብርሃም ቀና ብሎ ተመለከተ፤ በቍጥቋጦ መካከልም ቀንዶቹ የተጠላለፉ አንድ አውራ በግ ከበስተ ኋላው አየ፤ ወደዚያው ሄዶ በጉን አመጣና የሚቃጠል መሥዋዕት አድርጎ ሠዋው።
ዘፍጥረት 22፥1-13

በዛሬው ዕለት የጋብቻ ስርዓታችሁን የፈጸማችሁ የቤተክርሰሰቲያናችን አባል የሆነሽ እህታችን ሰላም አየለ እና ወንድም ኤባ ገመቹ እንኳን ደስ ያላችሁ እያልኩ መልካም ጋብቻ እንዲሆንላችሁ እመኛለ...
16/05/2026

በዛሬው ዕለት የጋብቻ ስርዓታችሁን የፈጸማችሁ የቤተክርሰሰቲያናችን አባል የሆነሽ እህታችን ሰላም አየለ እና ወንድም ኤባ ገመቹ እንኳን ደስ ያላችሁ እያልኩ መልካም ጋብቻ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

መጋቢ ወንድወሰን ለማ
ግንቦት 08 ቀን 2018 ዓ.ም

 ! 🔥🔥🔥
16/05/2026

! 🔥🔥🔥

https://youtu.be/SLd4u6ivyiw?si=J8gJnPGnRI5dOjHL
15/05/2026

https://youtu.be/SLd4u6ivyiw?si=J8gJnPGnRI5dOjHL

የኢትዮጵያ አማኑኤል ኅብረት ቤተክርስቲያን ቢሾፍቱ አጥቢያ እሁድ ማለዳ 3፡00 – 6፡00 የአምልኮ ጊዜ እሮብ ጠዋት 3፡00 – 7፡00 ሰአት የፈውስና የጸሎት ጊዜ አርብ ምሽት 11፡00 – 1:00 የትምህርት ...

Address

Ras Hotel Hora Lake
Debre Zeyit

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bishoftu/Debre Zeit Emmanuel United Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Bishoftu/Debre Zeit Emmanuel United Church:

Share