Pastor Riesom Negash

Pastor Riesom Negash በፊቱ ቅዱሳንና ነውር አልባ እንድንሆን ዓለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ በእርሱ መርጦናልና። ኤፌሶን 1:-4
(2)

እግዚአብሔርን ፈለግሁት መለሰልኝም፥ ከመከራዬም ሁሉ አዳነኝ።”(መዝሙር 34፥4)​በሕይወታችን ውስጥ የጨለማ ወራት፣ የጭንቀትና የፈተና አውሎ ነፋሶች ሊበዙ ይችላሉ። ነገር ግን በጸሎት ወደ እ...
14/09/2026

እግዚአብሔርን ፈለግሁት መለሰልኝም፥ ከመከራዬም ሁሉ አዳነኝ።”

(መዝሙር 34፥4)

​በሕይወታችን ውስጥ የጨለማ ወራት፣ የጭንቀትና የፈተና አውሎ ነፋሶች ሊበዙ ይችላሉ። ነገር ግን በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ስንጮኽ የሚሰማ፣ የልባችንን ስብራት የሚያክም፣ ከጭንቀታችንም ሁሉ የሚያወጣ ታማኝ አምላክ አለን!

​ዛሬ በምንም ዓይነት መከራና የሕይወት ውጥረት ውስጥ ብትሆን ተስፋ አትቁረጥ። እርሱን በፍጹም ልብህ ፈልገው፤ እርሱ በጊዜው ይ መልስልሃል፣ ከከበበህም መከራ ሁሉ ያወጣሃል።

​እግዚአብሔር ጸሎትን የሚሰማ አምላክ ነው።

​ለእርሱ የሚሳነው ነገር የለም።

​በፍጹም ልብህ የፈለግኸው ዕለት መላሹን ታገኘዋለህ!

​የዕለቱ መልእክት፦ ዛሬ ጭንቀትህን፣ ፍርሃትህንና ሸክምህን ሁሉ ወደ እግዚአብሔር አቅርብ። እርሱ አሁንም ይሰማል፤ ዛሬም ይታደጋል!

11/09/2026

የጠራን እግዚአብሔር የታመነ ነው!
እርሱ ወደ ልጁ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ህብረት ጠርቶናል። በቃሉ የማይለወጥ፣ በቃል ኪዳኑ የታመነ አምላክ ስላለን እናመሰግነዋለን።
​1ቆሮ1:9

የፍጥረት ናፍቆት የእግዚአብሔርን ልጆች መገለጥ ይጠባበቃልና።" — ሮሜ 8፥19​ዓለም ዛሬ ከምንጊዜውም በላይ የመፍትሔ፣ የፍቅርና የእውነተኛ ብርሃን እጥረት አለባት። ፍጥረት ሁሉ ከሕመም፣ ከ...
10/09/2026

የፍጥረት ናፍቆት የእግዚአብሔርን ልጆች መገለጥ ይጠባበቃልና።" — ሮሜ 8፥19

​ዓለም ዛሬ ከምንጊዜውም በላይ የመፍትሔ፣ የፍቅርና የእውነተኛ ብርሃን እጥረት አለባት። ፍጥረት ሁሉ ከሕመም፣ ከጭንቀትና ከውድቀት የሚያስመልሰውን ያንን እውነተኛ የእግዚአብሔር ሕልውና የያዘ ስውር ማንነት—የእግዚአብሔርን ልጆች መገለጥ በናፍቆት እየጠበቀ ነው።

​✨ አንተ/አንቺ የተጠራኸው/ሽው የዚህ ትውልድ መፍትሔ እንድትሆን/ኚ ነው።

✨ ፍጥረት የሚጠብቀው ያንተን/ያንንሽን መገለጥ ነው!

​እራሳችንን በክርስቶስ ማንነት እንግለጥ! 🙏✨

01/09/2026

🔥 ሰበር ዜና! 🔥
​በባዶ እጅህ ወደ 2019 አትገባም! 🙏✨
​እግዚአብሔር ለአንተ/ለአንቺ አዲስ መንገድ ያዘጋጃል። ያላሰብከው ይከፈታል፤ የዘጋኸው ምዕራፍ በበረከት ይተካል።

18/08/2026

አንድ በር ሲዘጋባችሁ አትዘኑ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር አነስተኛውን በር የሚዘጋው፣ ታላቁንና የተሻለውን በር ሊከፍትላችሁ ስለሆነ ነው!
//ሀሌሉያ//

13/08/2026

ዛሬ የሚያስለቅሳችሁ ጉዳይ ነገ ለማመስገን ምክንያት ይሆናል። ዛሬ የወደቀው ጠብታ እንባችሁ፣ ነገ የሚበቅለውን የደስታችሁን አበባ የሚያጠጣ ውኃ ነውና በምንም ሁኔታ ውስጥ ብትሆኑ ተስፋ አትቁረጡ።

12/08/2026

እግዚአብሔርን ፈለግሁት መለሰልኝም፥ ከመከራዬም ሁሉ አዳነኝ።” (መዝሙር 34፥4)
​ !
​በጭንቅና በፈተና ውስጥ ሆነን ወደ እርሱ ስንጮህ፣ እርሱ ይሰማናል፤ ከከበበንም መከራ ሁሉ በፍቅርና በኃይሉ ያወጣናል። ዛሬም ቢሆን እርሱን የሚፈልጉና በእርሱ የሚታመኑ ሁሉ ታምራቱን ያያሉ፤ ልባቸውም በሰላምና በደስታ ይሞላል።
​ይህንን መልእክት ለሚያነቡ ሁሉ፦ አምላካችን እግዚአብሔር ጸሎታችሁን የሚሰማበት፣ መከራችሁን የሚያርቅበትና የተከፈለላችሁን ድል የሚያሳያችሁ መልካም ቀን ይሁንላችሁ! 🙏✨

10/08/2026

ዓለም ሊያናውጥህ ሲሞክር፣ እግዚአብሔር በቀኝህ እንዳለ አስብ። እርሱን በፊታችን ካስቀደምን የትኛውም ማዕበል ሊጥለን አይችልም!
​🕊️ «ሁልጊዜ እግዚአብሔርን በፊቴ አየዋለሁ፤ በቀኜ ነውና አልታወክም።መዝ 16፥8

06/08/2026

እግዚአብሔርም ከዮሴፍ ጋር ነበረ፤ ምሕረትንም አበዛለት፥ ዘፍ 39፥21
​ሰው ሊጥልህ፣ ሊረሳህ ወይም በጨለማ ውስጥ ሊጥልህ ይችላል፤ እግዚአብሔር ግን በነበርክበት ቦታ ሁሉ አብሮህ አለ!

በአንድነትና በፍቅር መጠራታችን ምንኛ ድንቅ ነው! ከመንፈሳዊ ቤተሰቦቼና ከቅዱሳን ጋር ያሳለፍነው የመንፈሳዊ ጉዞ ጊዜ በበረከትና በደስታ የተሞላ ነበረ። እግዚአብሔር ይህንን ቅዱስ ህብረት ስ...
04/08/2026

በአንድነትና በፍቅር መጠራታችን ምንኛ ድንቅ ነው! ከመንፈሳዊ ቤተሰቦቼና ከቅዱሳን ጋር ያሳለፍነው የመንፈሳዊ ጉዞ ጊዜ በበረከትና በደስታ የተሞላ ነበረ። እግዚአብሔር ይህንን ቅዱስ ህብረት ስለባረከው ስሙ የተባረከ ይሁን!"

​"ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው።"

መዝዳዊት 133:1 🕊️✨

Address

Chqala Street
Debre Zeyit

Telephone

+251961951514

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Pastor Riesom Negash posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Pastor Riesom Negash:

Shortcuts

Share