በፍኖተ አበዉ የክርስቶስ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን በደብረ ታቦር/finot Abow In Deber Tabor

  • Home
  • Ethiopia
  • Debre Tabor
  • በፍኖተ አበዉ የክርስቶስ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን በደብረ ታቦር/finot Abow In Deber Tabor

በፍኖተ አበዉ የክርስቶስ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን በደብረ ታቦር/finot Abow In Deber Tabor Jesus Paid It All

25/07/2022

✍️ ፈሶ ወደ ሰማይ
*********************
የተላጠ ጀርባህ ፣ የተገሸለጠው
ለጨካኞች ጅራፍ ፣ ታልፎ የተሰጠው
የተተለተለው ፣ በደም አሸብርቆ
የሚታይ ገላህ ፣ ከገላዎች ልቆ
በኃጢአተኞች እጅ ፣ እየተዋረደ
ምህረት አዝንቦ ፣ ፍቅር ያዥጎደጎደ
በደዌ የደቀቀ ፣ ህማም የበዛበት
ጥፊና ግርፋት ፣ ምራቅ ያረፈበት
ዕርቃን ሰውነትህ ፣ ግፍ የተቀበለው
አንዱ ንጹህ ገላህ ፣ ሁሉን የሰቀለው
በጦሩ ጎንህን ፣ በችንካር እጅህን
በጥፊ ፊትህን ፣ በጅራፍ ጀርባህን
ጭንቀትና ስቃይ ፣ ዝምታ በአንድ ላይ
የተቆለለብህ ፣ በማይስብ መልክህ ላይ
ወደኸኝ ነውና ፣ ልሙትለት ብለህ
እንኳን ስቃይ ገባህ ፣ እንኳን ጭንቅ አለህ
ያለርህራሄ ፣ ያለሀዘኔታ
መስቀል ያሸከመህ ፣ ወደ ጎልጎታ
አባትህ ነውና ፣ ጨክኖ የገደለህ
ኤሎሄ ኤሎሄ ፣ ስትለው ዝም ያለህ
ምነው የዛን ጊዜ ፣ በሰማህ አልልም
አንተ ባትሞት ኑሮ ፣ እኔ ልጅ አልሆንም
ምነው የዛን ጊዜ ፣ ወይ ባለህ አልልም
አንተ ባትቆስልልኝ ፣ የኔ ቁስል አይድንም
እንደውም እንደውም ፣ እንኳንም አልሰማህ
እንኳንም ተላጠ ፣ እንኳን ደማ ጀርባህ
እንኳን ተሰቃየህ ፣ እንኳንም ተጠማህ
እንኳንም ተፉብህ ፣ እንኳን ሲዖል ገባህ
እንኳን አፌዙብህ ፣ እንኳን አንተን ጠሉ
እንኳን ቀሚስህ ላይ ፣ ዕጣ ተጣጣሉ
ኧረ እንደው እንደውም ፣ እንኳን ወይ አላለህ
እንኳን አደቀቀህ ፣ እንኳን አቆሰለህ
እንኳን ውበት አጣህ ፤ እንኳን ደግ እሰየው
አብ እንደሚወደኝ ፣ እንኳን ሰይጣን አየው
ባትጨነቅ ኑሮ
ባትወጋ ኑሮ
ባትገረፍ ኑሮ
ባያደቅህ ኑሮ
አንተ ባትሰቀል ፣ ተተክተህ በ'ኔ
አንፋታም ነበር ፣ እኔና ኩነኔ
ሞተህ ባትነሳ ፣ ጽድቅ ባላገኘሁ
ሞቼ እቀር ነበረ ፣ ሞት እየተመኘሁ
ይብላኝ እንጂ ለሞት ፣ አንተ እንኳን ተሰቀልክ
መልክህን እንድይዝ ፣ እንኳን መልኬን መሰልክ
ከአባትህ ዕቅፍ ፣ እንኳን ወ'ተህ መጣህ
እንኳን ባልሰራኸው ፣ ቅጣቴን ተቀጣህ
በፍቅር እያየህ ፣ ወንድሜ ልትለኝ
ከወዳጅ የሚበልጥ ፣ ወዳጅ ልትሆነኝ
እዛ መስቀሉ ላይ ፣ ተቸንክረህ ሳለ
እዛ መስቀሉ ላይ ፣ ደምህ ሲፈስ ሳለ
እዛ መስቀሉ ላይ ፣ እያማጥክ ሳለ
እዛ መስቀሉ ላይ ፣ ዝለህ ደክመህ ሳለ
ይቅር በለው እያልክ ፣ የበዛ በደሌን
የጠራኸው አንተ ፣ አቤት ያለው እኔን
በእኔ ህመም ቆስለህ ፣ እያከምክ ቁስሌን
ኤሎሄ ያልከው አንተ ፣ አቤት ያለው እኔን

እናማ ምን ሆነ......
በእርግማን ሞትህ ፣ በረከት ሆነኸኝ
ከጽዮን መጥተህ ፣ ከሲዖል ነጥቀኸኝ
በአብ ቀኝ ተገኘሁ ፣ ሞትን ዳግም ላላይ
የደምህ ጅረቱ ፣ ፈሶ ወደ ሰማይ



https://t.me/joinchat/RrbSCabYHAXQ6nx7

06/01/2022

እንኳን አደረሰን!

16/09/2021

ፀጋ ይብዛልሽ

06/09/2021

✍️✍️
አንድ ነገር ሁሌም ይገርመኛል ሰው ሰውን የሚወድበት የራሱ ምክንያት አለው በምክንያት ስለሆነ የሚወደን በምክንያት ይጠላናል።
አይገርምም የእግዚአብሔር ፍቅር ግን ሁሌ ይገርመኛል ያለ ምክንያት ስለሚወደን በምክንያት አይጠላንም።
ምክንያቱም ደግሞ በመጀመሪያም የወደደኝ ሙት የማንጠቅም + በሌለንበት ነው እንዲሁ የወደደን ስለዚህ ነው ምክንያት አልባ ፍቅር የሆነው በኔ ሆኔታ አይጨምርም አይቀንስም እግዚአብሔር ሰትበረታ በጣም አይወድህም ስትደክምም ደግሞ አይጠላህም የእርሱ ፍቅር ያው ነው የሰው ፍቅር ነው ከፍ ዝቅ የሚለው ይሄንን ሳስብ ሁሌም ይገርመኛል ያለ ምክንያት መወደዴ ታዲያ በዚህ ያልቸገረምኩ በምን ልገረም ለምን አልቀነሰም ለምንስ አልጨመረም ካላችሁኝ እግዚአብሄር እኛን የወደደን በሚወደው በአንድያ ልጁ ነው ስለዚህ ደግሞ በእርሱ መወደድ ልክ ስለወደደን ነው ስለዚህ ወዳጀ በሰሞኑ ሁኔታ የእግዚአብሔርን ፍቅር አትለካው ክብር ሁሉ ለእርሱ ይሁን።

17/08/2021
እንዴት?ገና በሐጢያቴ ሞት ሆኘ ወደድከኝአለም ሳይፈጠር በልጅሕ መረጥከኝየኔን ሀጢያት ወስዶ ፀድቁን ሊያለብሰኝሙት የነበርኩትን ህያው ሊያደርገኝአባቱ የተወው ፊቲን ያዝረበትበሚወደው ልጁ እንዲ...
01/05/2021

እንዴት?
ገና በሐጢያቴ ሞት ሆኘ ወደድከኝ
አለም ሳይፈጠር በልጅሕ መረጥከኝ
የኔን ሀጢያት ወስዶ ፀድቁን ሊያለብሰኝ
ሙት የነበርኩትን ህያው ሊያደርገኝ
አባቱ የተወው ፊቲን ያዝረበት
በሚወደው ልጁ እንዲያ የጨከነበት
ግድ ስላለው ነው የሐጢያተኛው ሞት
ሀጢያቴን በውሉ በመስቀል ቸንክሮ
መተላለፌንም በጉድጓድ ውስጥ ቀብሮ
ኢየሱስ ሲነሳ እኔንም አስነሰኝ
ካለብኝ ኩነኔ ከበደሌ አነጻኝ
ያለ ሃጢያት አርጎ በእርሱ ፊት አቆመኝ
እንዴት ካለችሑኝ ኢየሱስ ተነስቷል
ሁሉ እንዳለቀ አውቆተ ፈፀመ ብሏል
አሑን ያለ ሃጢያት በአብ እታያለሁ
ወደ አብ ለመግባት ድፍረት አገንቻለሁ
በመጋረጃየ በእርሱ ቀርቢያለሁ።

#ፅድቅ ነኝ ቅዱስ
እንዴት?
#በኢየሱስ።

Address

Debre Tabor
1212

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በፍኖተ አበዉ የክርስቶስ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን በደብረ ታቦር/finot Abow In Deber Tabor posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to በፍኖተ አበዉ የክርስቶስ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን በደብረ ታቦር/finot Abow In Deber Tabor:

Share