ገዳም አስቄጥስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም - ደብረማርቆስ

ገዳም አስቄጥስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም - ደብረማርቆስ ✝️🔔 ጥንታዊውን እና ታሪካዊውን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ወ?

✝️🔔 ጥንታዊውን እና ታሪካዊውን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ወክርስቶስ ሰምራ አንድነት ገዳም ለሀገራችን ብሎም ለዓለም የምናስተዋውቅበት፤ የፃድቁ አባታችን ገድል የምንዘክርበት፤ በፃድቁ ስም ተሰባስበን ሀይማኖታችንን የምንጠብቅበት እና በጎ ተግባራትን የምንሰራበት ጉባዔ ነው🔔

29/05/2026

🕊️ በደብረ ምጥማቅ የአምላክ እናት የድንግል ማርያም መገለጥ ከግንቦት 21–25
✍ በመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ

📖✨ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በመዝሙር ፵፬፥፲፪ ላይ፦
🌿 “ወለገጽኪ ይትመሐለሉ ኲሎሙ አሕዛብ ብዑላነ ምድር” 🌿
👑 “የምድር ባለጠጎች አሕዛብ ኹሉ በፊትሽ ይማለላሉ” 👑

🌹 በማለት ትንቢትን እንደተናገረላት፣ ብዙዎች ቅዱሳን ቅድስት ድንግል ማርያምን ተገልጻላቸው የአምላካቸውን እናት ለማየት ተመኝተዋል።

✨ ብዙዎቹም ልመናቸው ተሰምቶላቸው፣ የአምላክ እናት ተገልጻላቸው፣ እጅግ አስደናቂ ውበቷን አይተዋል።

⛪ ከነዚኽ ውስጥ በደብረ ምጥማቅ የነበሩ ምእመናን፣ ሌሎችም ብዙዎች ንጹሓን ክርስቲያኖች ይገኙበታል።

🌍 ልጇ አስቀድሞ በዘመነ ሥጋዌዉ በደብረ ምጥማቅ እንደምትገለጽ በገባላት ቃል ኪዳን መሠረት፣ ከኢትዮጵያ፣ ከግብጽ፣ ከአርመንያ፣ ከሶርያ፣ ከሮም፣ ከጽርዕ፣ ከፋርስ ሀገራት ተሰብስበው፣ በደብረ ምጥማቅ ድንኳን ተክለው፣ አጐበር ጥለው፣ ከግንቦት 21 ቀን ጀምረው እስከ 25 ቀን ድረስ በፍጹም ደስታ የድንግልን በዓሏን ያከብሩ ነበር።

🕊️ “ወድንግልሂ ታስተርእዮሙ በእሉ ኀምስ መዋዕል ዘእንበለ ጽርዐት ምስለ መላእክት ወጻድቃን ወሰማዕት ምስሌሃ” 🕊️

🌟 እመቤታችን ከግንቦት 21–25 ያለማቋረጥ፣ ከመላእክት፣ ከሊቃነ መላእክት፣ ከነቢያት፣ ከሐዋርያት፣ ከጻድቃን፣ ከሰማዕታት፣ ከደናግል፣ ከመነኮሳት ጋራ ኹና ትገለጽላቸው ነበር።

💧 አማኒውም ኢአማኒውም ያያት ነበር። ክርስቲያኖች ይህንን ድንቅ ተአምር እያዩ እምነታቸው ሲጸናላቸው፣ ያላመኑት ደግሞ እያመኑ በመጠመቅ ሀብተ ውልድና ስመ ክርስትናን ይቀበሉ ነበር።

🌞 በጒልላቱ ላይ ስትገለጽ፣ በውስጥ፣ በአፍአ፣ በነፍስ፣ በሥጋ ንጽሕት የኾነችው የቅድስት ድንግል ማርያም የፊቷ ውበትና ብርሃን እጅግ ድንቅ ነበር።

🙏 ካህናቱም ሕዝቡም ኹሉ ልክ እንደ ኤልሳቤጥ፦ “የጌታችን እናት ለእኛ ትገለጪ ዘንድ እኛ ምንድን ነን?” እያሉ ይጮኹ ነበር። ርሷም ያለማቋረጥ ትባርካቸው ነበር።

🌺 የእመቤታችን ፍቅር በእጅጉ የበዛለት አባ ጽጌ ድንግልም በማሕሌተ ጽጌ መጽሐፉ ላይ፦

📜 “አመ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ኀምሰ ዕለታተ
ትእምርተ ገጽኪ ይርአይ እስከ ይትነሣእ ዘሞተ
ሚ መጠነ ማርያም ታሥተፌሥሒ ትፍሥሕተ
ኅድጊሰ ጽጌ ፍቅርኪ በጊዜ ንቃሑ መዓልተ
ብፁዕ ዘርእየኪ በሕልሙ ሌሊተ” 📜

🌹 “የፊትሽን መልክ ያይ ዘንድ የሞተ ሰው እስኪነሣ ድረስ፣ በደብረ ምጥማቅ ለዐምስት ቀናት ያኽል በተገለጽሽ ጊዜ፣ ማርያም ምን ያኽል ደስ ታሰኚ ኖሯል! በቀን የታየው የፍቅርሽ አበባ ይቅርና፣ ሌሊት በሕልሙ ያየሽ ምስጉን ነው” 🌹

🔥 ዳግመኛም ይኸው ኢትዮጵያዊ ሊቅ በተመስጦ፦

📜 “ሥዕልኪ ጽግይተ ላሕይ ዘከመዝ ትኤድም በዓለም
እፎ ይሤኒ በሰማይ ላሕየ ገጽኪ ማርያም
ሐሤተ ትእምርትኪ እጽገብ አስተርእዪኒ በሕልም
እስመ አውዐየኒ ነደ ፍቅርኪ ፍሕም
አጥፍኦቶ ዘኢይክል ዝናም” 📜

🌧️🔥 “ማርያም ሥዕልሽ በዓለም እንዲኽ የምታበራ ከኾነ፣ በሰማይ የፊትሽ መልክ ምን ያምር! አንቺን ከማየት የሚገኘውን ደስታ እጠግብ ዘንድ በሕልም ተገለጪልኝ፤ ዝናብ ሊያጠፋው የማይቻለው የፍቅርሽ እሳት አንድዶኛልና” 🔥🌧️

👑 ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በእንዚራ ስብሐት መጽሐፉ ላይ በአድናቆት፦

📜 “ኦ ንግሥት ይገንዩ ለኪ ነገሥት ወለኪ ንግሥታት ይትቀነያ
ወኪያኪ የአኲታ ወለስምኪ ይገንያ
ወለኪ ይሰግዳ ወለክብርኪ የሐልያ
ጢሮስ ወሲዶና ሰብአ ግብጽ ወኢትዮጵያ
ፊንቂ ወሮምያ ማሮን ወአርማንያ
በሥነ ጸዳልኪ ይትፌሥሓ ወበላሕይኪ ይትሐሠያ” 📜

🌍👑 “ንግሥት ሆይ፣ ነገሥታት ለአንቺ ያገለግላሉ፤ ንግሥታትም አንቺን ያመሰግናሉ፤ አንቺንም ያሞግሳሉ፤ ለስምሽም ያጐነብሳሉ፤ ለአንቺ የጸጋ ስግደትን ይሰግዳሉ፤ ለክብርሽም ምስጋናን ያቀርባሉ። ጢሮስና ሲዶና፣ የግብጽና የኢትዮጵያ ሰዎች፣ ፊንቄና ሮምያ፣ ማሮንና አርማንያ በወጋገንሽ ውበት ደስ ይሰኛሉ፤ በደም ግባትሽም እሰይ ይላሉ” 🌍👑

🎶 ቅዱስ ያሬድ አባታችንም በማይ ኪራሕ ሳለ፣ እመቤታችን ተገልጻለት ፊቷን ለማየት ታድሏልና፣ ይኽነን በዐይኑ ያየውን ውበቷን በድጓው ላይ እንዲኽ ሲል ጽፎታል፦

☀️ “አይ ይእቲ ዛቲ እንተ ትወርድ እምሰማይ፤ ብርህት ከመ ፀሓይ፤ አዳም ቆማ ወክሣዳ ከመ አርማስቆስ፤ መዐዛ አፉሃ ከመ ኮል” ☀️

🌞 “ከሰማይ የምትወርደው፣ እንደ ፀሐይም የምታበራው ርሷ ማን ናት! አንገቷ እንደ ግንብ ቀጥ ያለ ነው፤ የአፏም መዐዛ እንደ እንኮይ ነው” 🌞

🎼 ይኽ የቤተ ክርስቲያን ጌጥ ቅዱስ ያሬድ፣ በዚኽ ሳያበቃ፣ በመላእክት እየተመሰገነች ስለተገለጸችለት ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ያየውን የውበቷን ነገር ሲናገር፦

🕊️ “እምኀበ መላእክት ትሴባሕ አዳም ሥና፤ መዐርዒር ቃላ ወኲሉ ነገራ በሰላም … እምወርኅ ወእምፀሓይ ይሤኒ ላሕያ … ከመ ፍሕሶ ቀይሕ ከናፍሪሃ ወከመ ኮል መዐዛ አፉሃ ወከመ ሮማን ቂሐተ መላትሒሃ …” 🕊️

🌙☀️ “በመላእክት ትመሰገናለች፤ ደም ግባቷ ያማረ ነው፤ ቃሏ እንደ ማር የጣፈጠ፣ ነገሯ ኹሉ በሰላም የተመላ ነው፤ ውበቷ ደም ግባቷ ከጨረቃና ከፀሓይ ይልቅ ያምራል፤ ከንፈሮቿ ፍሕሶ እንደሚባል አበባ ቀይ ናቸው፤ የጒንጯ ቅላትም እንደ ሮማን ቅርፍት ነው” 🌙☀️

✨ እያለ ሊቁ ማሕሌታይ በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ይመሰክርላታል።
🌹 አይ መታደል! አይ መባረክ! 🌹
❤ የእመቤታችን ጣዕመ ውዳሴዋ የበዛለት ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በእንዚራ ስብሐቱ ላይ ስለ ውበቷ በተመስጦ ኾኖ ያቀረበላትን ውዳሴ እነሆ፦

“ኦ ፍቅርት ውዕየ ልብየ በእሳተ ፍቅርኪ ወነደ ኅሊናየ እምኀልዮትኪ …”

🔥🌹 “ውዲቱ ሆይ፣ በፍቅርሽ እሳት ልቤ ተቃጠለ፤ አንቺንም ከማሰብ የተነሣ ኅሊናዬ ነደደ፤ ለምስጋናሽ ቃሌን ከፍ ከፍ አደርጋለኊ፤ አንቺን ለማመስገንም አንደበቴን አከፍታለኊ።

👑 ንግሥት ሆይ፣ አንደበቴ ቅንነትሽን በመናገር ደስ ይለዋል፤ ከንፈሮቼም በቸርነትሽ ጣዕም ነገር ደስ ይሰኛሉ፤ ሰላም እያልኹሽም ለስምሽ አጠራር እኔ እሰግዳለኊ።”

🖤🌿 ንግሥት ሆይ፣ የራስሽ ክፍክፋት ተፈጥሮ እንደ አሞራ ጥቁር የኾነ ጠጒርሽም እንደ ሐር የሚመስል ነው።
👑 የራስ ወርቅሽ የቃል ኪዳን ምልክት ነው፤
✨ የንጽሕናሽ ብርሃንም እንደ ጧት ወገግታ ነው።

⚡🌙 ግርምቲቱ ሆይ፣ የቅንድቦችሽ ነበልባል የመብረቅ ፍንጣቂ ነው፤
👁️ ዐይኖችሽም እንደ ጨረቃ ምላት ብርሃንን የተመሉ ናቸው፤
👂 ጆሮችሽም የደስታ በሮች ናቸው፤
🌺 የጒንጮችሽ ቅላትም እንደ ሮማን ቅርፍት ነው።

🌸🪟 ንግሥት ሆይ፣ አፍሽ የበጎ መዐዛ መስኮት ነው፤
💋 ከንፈሮችሽም የደስታ መፍሰሾች ናቸው፤
🍃 የአፍንጫሽ መዐዛም የበረሓ እንኮይ ነው፤
❄️ የጥርሶችሽ ንጣትም እንደሚያምር በረዶ ነው።

🍯🥛 ምርጢቱ ሆይ፣ የአንደበትሽ ሥር የወተት ምንጭ ነው፤
🍯 የንግግርሽ ቃልም እንደ ማር የጣፈጠ ነው፤
🌿 የእስትንፋስሽ ቃልም የሽቱ ቅመም ብናኝ ነው፤
🍯 ጒረሮሽም የማር ወለላ አረፋ ነው።

👰✨ የተሸለምሽ ያጌጥሽ ሙሽሪት ሆይ፣
🏅 የአንገትሽ መገናኛ እንደ ወርቅ ዘንግ ነው፤
🕊️ ትከሾችሽም የሰላምና የቅንነት ማረፊያዎች ናቸው፤
✨ የጀርባሽ ልብስም የብርሃን ሐር ነው፤
📖 ደረትሽም የዕውቀት አዳራሽ ነው፤
☦️ ጉያሽ የመለኮት ማረፊያ ናቸው፤
🤲 እጆችሽም በንጽሕና አንባር የተሸለሙ ናቸው።

🔥 ክንዶችሽም የንጉሥ መጠጊያዎች ናቸው፤
💪 ክርንሽም የኀይል ረድኤት ቦታ ነው፤
🔥 ክንዶችሽም የእሳት ምሳግ ናቸው፤
🤲 መኻል እጆችሽም ለመስጠት የተዘረጉ ናቸው፤
🏵️ በጥፍሮችሽ የተጋረዱ ጣቶችሽ እንደ ወርቅ ፍቅፋቂ ናቸው።

🍇🌿 ሙሽሪት ሆይ፣ ጡቶችሽ እንደ ወይን ፍሬ የተወደዱና ያማሩ ናቸው።
🌾 ጐኖችሽም በወርቅ ሐመልማል ያጌጡ ናቸው።
🌸 የማሕፀንሽ መቅደስ በአበባ የታጠረ ነው፤
💗 የልቡናሽ ጥልቀትም በቸርነት ቃል የተሞላ ነው፤
📜 ኲላሊቶችሽ የትእዛዝ ጽላት ናቸው፤
🧠 ኅሊናሽም የጥበብ መሠረት ነው፤
🕊️ አንጀትሽም የይቅርታ ሣጥን ነው፤
⛪ የውስጥ ሰውነትሽም የቅዱሳን ቅድስት ምልክት ነው፤
🔘 የዕንብርትሽ ዙሪያም እንደ ማኅተም ቅርጽ ነው፤
👑 ማሕፀንሽም የምስጋና ዙፋን ነው።

📖🔒 የድንግልናሽም ምሳሌ የታተመ የነቢያት መጽሐፍ ነው፤
✨ የወገብሽ ትጥቅም የቅድስና ጸጋ ነው፤
☁️ ጒልበትሽም የአርያም ወገን ናቸው፤
🏛️ የጭኖችሽ አነዋወርም እንደ እብነ በረድ ምሶሶች ነው፤
👣 እግሮችሽም ምሕረትን ለማድረግ የተፋጠኑ ናቸው፤
🌿 የማይታበዩ ጫማዎችሽም የጥበብ መድረክ ናቸው፤
🛤️ እግርሽም በቅንነት ጐዳና የጸኑ ናቸው፤
💎 የእግርሽ ጣቶችም በጥፋት ደንጊያ የማይሰነካከሉ ናቸው፤
✨ ጥፍሮችሽም በላያቸው እንደ ብርሃን ብልጭ የሚሉ ናቸው።

🌴🌹 የቁመናሽ አካልም እንደ ዘንባባ ያማረ ነው፤
🌺 የመልክሽ ደም ግባትም ለዐይን የተወደደ ነው።
🌷 ድንግል ሆይ፣ እጅግ በጣም አማርሽ፤
🕊️ ከራስሽ እስከ እግርሽ ክፉ ነገር የለብሽም።
✨ ደም ግባትሽን የሚመስለው የለም፤ ኹለንተናሽንም የሚተካከለው የለም።
🌹 ምርጢቱ ሆይ፣ መልካም በኾነውና በጎም በኾነው ኹሉ መሰልኹሽ፤ ነገር ግን ምስጋናሽን መጨረሽ አልቻልኹም።
— አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ

🌞✨ የመልክአ ማርያም ደራሲም የአምላኩን እናት ቅድስት ድንግል ማርያምን ፊቷን ለማየት ሽቶ፣ በናፍቆት ኾኖ፦

📜 “ሰላም ለመልክእኪ ዘተሠርገወ አሜረ ዘያበርህ ወትረ ፍቅርትየ አንቲ እንተ ታበድሪ ፍቅረ አርእዪኒ ገጸ ዚኣኪ ማርያም ምዕረ ዘኢይሰምዖ ካልእ እንግርኪ ነገረ” 📜

☀️ “ኹልጊዜ የሚያበራ ፀሓይን ጌጥ ላደረገ መልክሽ ሰላምታ ይገባል።
💞 ፍቅርን የምትመርጪ አንቺ ፍቅረኛዬ ማርያም፣
🙏 ሌላ የማይሰማው ነገርን እነግርሽ ዘንድ፣ አንድ ጊዜ ያንቺን ፊት ግለጪልኝ”

በማለት ተማፅኗታል።

⛪🕯️ በመኾኑም በደብረ ምጥማቅ የተገለጠችላቸው ምእመናን የአምላክን እናት አይተው እንደተደሰቱ፣ ዛሬም ለእኛ በመስቀል ሥር ከልጇ ለተቀበለችን ለአደራ ልጆቿ በረድኤት ትገለጽ ዘንድ፣ አበው ካህናት ሌሊቱን በሰዓታት ምስጋና፦

🙏 “ንዒ ኀቤየ ኦ ድንግል ምስለ ወልድኪ ፍቁርኪ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ትባርኪ ላዕሌነ” 🙏

🕊️ “ድንግል ሆይ፣ ከተወዳጅ ልጅሽ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋራ ወደ እኔ ነዪ፤ እኛን ትባርኪ ዘንድ፣ በእኛ ላይ በረከትን እንድታሳድሪ” 🕊️

🌹✨ የአምላክ እናት ሆይ፣ ዛሬም ለእኛ በረድኤት ተገለጪልን፤ በልጅሽ ፊት አማልጂን፤ በረከትሽም ከእኛ አይለይ። ✨🌹

✍ ከመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ

👉 በመስቀል ሥር ስጦታችን የተጽናናችኹ የብርሃን ልጆች፣ በአስተያየት መስጫው ላይ እናታችኹን አወድሷት።

🙏✝️🙏   በሠላም አደረሳችሁ፤ አደረሠን!!💚💛❤️
09/05/2026

🙏✝️🙏 በሠላም አደረሳችሁ፤ አደረሠን!!💚💛❤️

10/04/2026
10/04/2026
04/04/2026
💚💛❤️   አደረሰን አደረሳችሁ!!🙏✝️🙏
18/01/2026

💚💛❤️ አደረሰን አደረሳችሁ!!🙏✝️🙏

⛪️  ል  ደ   ታ   ለ  ማ  ር  ያ  ም   ⛪️       𝙏𝙝𝙚 𝙉𝙖𝙩𝙞𝙫𝙞𝙩𝙮 𝙤𝙛 𝙩𝙝𝙚 𝘽𝙡𝙚𝙨𝙨𝙚𝙙 𝙑𝙞𝙧𝙜𝙞𝙣 𝙈𝙖𝙧𝙮           𝟮𝟬𝟯𝟮ኛው የእመቤታችን ቤዛዊተ ዓለም  የልደት ...
09/05/2025

⛪️ ል ደ ታ ለ ማ ር ያ ም ⛪️
𝙏𝙝𝙚 𝙉𝙖𝙩𝙞𝙫𝙞𝙩𝙮 𝙤𝙛 𝙩𝙝𝙚 𝘽𝙡𝙚𝙨𝙨𝙚𝙙 𝙑𝙞𝙧𝙜𝙞𝙣 𝙈𝙖𝙧𝙮
𝟮𝟬𝟯𝟮ኛው የእመቤታችን ቤዛዊተ ዓለም የልደት ቀን

ሰላም ሰላም ለልደትኪ ኦ እግዚእትየ ማርያም
እስመ ኮነ ልደትኪ ምክንያተ ድጎነ ለዓለም
እመቤቴ ማርያም ሆይ ለልደትሽ ሰላምታ ይገባል
ልደትሽ ዓለምን ለማዳን ምክንያት ሆኗልና።

ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ
ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ ❗

የእመቤታችን የትውልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለው ተራራማ ሀገር ነው፡፡ አስቀድሞ ጠቢቡ ሰሎሞን ‹‹ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ ንዒ ወተወፅኢ እምቅድመ ሃይማኖት እምርእሰ ሳኔር ወኤርሞን እምግበበ አናብስት ወእምአድባረ አናምርት /ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ ከአማና ራስ ከሳኔር ከኤርሞን ራስ ከአንበሶች መኖሪያ ከነብሮችም ተራራ ተመልከች/››
(መኃልይ ዘሰለሞን 4፡8) በማለት ተናግሮ ነበር፡፡
በፈቃደ እግዚአብሔር በብሥራተ መልአክ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም በዕለተ እሑድ ነሐሴ ፯ ቀን ተፀነሰች። “ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ - ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ” እንዳለ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም።
ዛቲሂ ሊባኖስ ሀለወት እስከ ናሁ ወኢተወለጠ ስማ። ባሕቱ ይበዝሑ ባቲ አሕዛብ ወሀለወት በሕገ አሕዛብ። ትንቢቱም ሲፈጸም ግንቦት 1 ቀን በ15 ዓ.ዓ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ወይም ግንቦት 1 ቀን 5485 ዓ/ዓ የ 5500 የመከራው ዘመን ሊያልቅ 15 ዓመታት ሲቀሩት ሊባኖስ በሚባል ተራራ ከፀሐይ የምታበራ ሴት ልጅ ተወለደች፡፡
እሷም ፍጥረት ሁሉ ተስፋ ሲያደርጓትና ሲጠባበቋት የነበረች የድኅነታቸው ምልክት ቅድስት ድንግል ማርያም እመቤታችን ናት፡፡

ጴጥርቃ እና ቴክታ የሚባሉ ሰዎች በኢየሩሳሌም በአንድነት ተጋብተው ይኖሩ ነበር። እነዚህም በእግዚአብሔር የሚያምኑ የተወደዱ ጻድቃን ደግ ሰዎች ነበሩ። እነዚህም ሰዎች በእግዚአብሔርም በሰውም ዘንድ የተመሰከረላቸው ባለጸጎች ነበሩ። ነገር ግን የሚወርሳቸው ልጅ አልነበራቸውምና መካን ነበሩ። ከዕለታትም ባንድ ቀን ቴክታ ለባሏ ጴጥርቃ አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን የሚያውቅ የለም ትላንትና ማታ በሕልሜ “ርኢኩ በሕልምየ ጸዓዳ ጣዕዋ ወጽአት እምከርስየ - ነጭ ጥጃ ከማኅጸኔ ስትወጣ ያችም ነጭ ጥጃ ሌላ ነጭ ጥጃ ስትወልድ እንዲሁ እስከ ፯ት ትውልድ ሲዋለድ ሰባተኛይቱም ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃዋም ፀሐይን ስትወልድ አየሁ አለችው።
እርሱም በጧት ከሕልም ፈቺ ዘንድ ሂዶ የነገረችውን ሁሉ ነገረው፤ ያም ህልም ፈቺ “እግዚአብሔር በምህረቱ አይቷችኋል በሣህሉ መግቧችሁኋል ፯ አንስት ጥጆች መውለዳችሁ ፯ ሴቶች ልጆች እና የልጅ ልጆች ትወልዳላችሁ፤ ከቤታችሁ ሰባተኛይቱ ጨረቃ መውለዷ ከሰው የበለጠች ከመላእክትም የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላችሁ። የፀሐይ ነገር ግን አልተገለጠልኝም” አለው። እርሱም የነገረውን ሁሉ ሄዶ ነገራት። እርሷም እንጃ አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን ማን ያውቃል? ብላ ዝም አለች። ከዚያም ፀንሳ ሴት ልጅ ወለደች፤ ስሟንም ‘ሄሜን’ ብለው አወጡላት፤ ሄሜንም አድጋ ለአካለ መጠን ስትደርስ አጋብተዋት ሴት ልጅ ወለደች። በስምንተኛ ቀኗም ‘ደርዲ’ ብለው ስም አወጡላት። ደርዲም አድጋ እንዲሁ ሴት ልጅ ወለደች እና ‘ቶና’ አለቻት። ቶናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ‘ሲካር’ አለቻት። ሲካርም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ‘ሴትና’ አለቻት። ሴትናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ‘ሔርሜላ’ አለቻት። ሔርሜላም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ንጽህት ቅድስት ክብርት የምትሆን እመቤታችንን የምትወልደውን ሐናን ወለደች። ሐና በሥርዓት አደገች፡፡ ለአእምሮ ስትበቃ፣ አካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ መንግሥት ወገን ከነቅዱስ ዳዊት ወገን ከሆነው ከቅዱስ ኢያቄም ጋር አጋቧት።
እነዚህ ቅዱሳን ኢያቄም እና ሐና በአንድነት ተጋብተው ሲኖሩ ልጅ አጡ፤ ከእለታት አንድ ቀን ወደ ቤተ እግዚአብሔር ሂደው ሲጸልዩ ሲያዝኑ ዋሉ። ሀዘናቸው እንዴትስ ነው ቢሉ፡- ኢያቄም፡- "አቤቱ ጌታዬ ያባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁ አትጣለኝ አትናቀኝ ጸሎቴን ስማኝ ፈቃዴን ፈጽምልኝ፤ ለዐይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋ የሚሆን የተባረከ/ች ወንድ ወይም ሴት ልጅ ስጠኝ" ብሎ ሲለምን ዋለ። ሐናም በበኩሏ "አቤቱ ጌታዬ የአባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁ፤ ስማኝ ለዐይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋ የምትሆነኝ የተባረከች ሴት ልጅ የማኅጸኔን ፍሬ ስጠኝ" ብላ ስትለምን ዋለች። እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲጸልዩ ውለው ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት ዐይታ አቤቱ ጌታዬ ለዚች ግእዛን ለሌላት እንስሳ ልጅ የሰጠህ አምላክ ምነው ለኔ ልጅ ነሳኸኝ ብላ ምርር ብላ አለቀሰች። ከሊቀ ካህናቱ ዘካርያስ ሄደው አቤቱ ጌታችን ሆይ ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ፣ ቤተ እግዚአብሄርን አገልግሎ እንዲኖር እንሰጣለን፤ ሴት ልጅም ብንወልድ ማይ (ውሃ) ቀድታ፣ መሶብ ወርቅ ሰፍታ፣ መጋረጃ ፈትላ፣ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር እንሰጣለን ብለው ስዕለት ገቡ። ዘካርያስም እግዚአብሔር ጸሎታችሁን ይስማችሁ ስእለታችሁን ይቀበልላችሁ ጻህቀ ልቦናችሁን ይፈጽምላችሁ ብሎ አሳረገላቸው። ከዚያም በኋላ ቅድስት ሐና እና ቅዱስ ኢያቄም ዕለቱኑ ራዕይ ዐይተው ነገር አግኝተው አደሩ። ራዕዩም ኢያቄም “ርኢኩ በህልምየ እንዘ ይትረኀው ሰባቱ ሰማያት - ፯ቱ ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ” አላት ፤ ወፍ የተባለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ነጭነቱ ንጽሐ ባሕሪው ነው፤ ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ ዐየሁ ማለቱ፤ አምላክ የኢያቄምን ( የሰውን) ባሕርይ ባሕርይ እንዳደረገው ሲያጠይቅ ነው፤ ፯ቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ልዩ ልዩ ባሕርይው፣ ምልአቱ፣ ስፍሃቱ፣ ርቀቱ፣ ልእልናው፣ ዕበዩ መንግሥቱ ናቸው።
ሐናም እኔም አየሁ አለችው፤ ምን አየሽ ቢላት፤ “ዖፍ ጸዓዳ መጽአት ኀቤየ ወነበረት ዲበ ርዕስየ ወቦአት ውስተ ዕዝንየ ወኀደረት ውስተ ከርስየ - ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማኅጸኔ ስትተኛ አየሁ” አለችው። ርግብ የተባለች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት። ነጭ መሆንዋ ንጽህናዋ፣ ቅድስናዋ፣ ድንግልናዋ ነው። ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማሕጸኔ ስትተኛ አየሁ ማለቷ ብሥራተ ገብርኤልን በጆሮዋ ሰምታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችንን መጽነሷን ነው። ይህንኑም ራዕይ ያዩት ሐምሌ ፴ (ሠላሳ) ዕለት ነው። እነሱም እንዲህ ያለ ራዕይ ካየን ነገር ካገኘን ብለው ዕለቱን በሩካቤ ሥጋ አልተገናኙም፤ ፈቃደ እግዚአብሔር ቢሆን ብለው አዳምንና ሔዋንን ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሏት ብሎ ያበሰረ አምላክ ለኛስ ይልክልን የለምን? ብለው ዕለቱን አልጋ ምንጣፍ ለይተው እስከ ፯ ቀን ድረስ ለየብቻቸው ሰነበቱ። በነሐሴ በሰባተኛው ቀን ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላችሁና ዛሬ በሩካቤ ሥጋ ተገናኙ ብሏችኋል ጌታ ብሎ መልአኩ ለሐና ነገራት። በፈቃደ እግዚአብሔር በብሥራተ መልአክ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም በዕለተ እሑድ ነሐሴ ፯ ቀን ተፀነሰች። እመቤታችን ከተፀነሰች በኋላ አይሁድ ቀንተው ተነሱባቸው። ከቅናትም የተነሳ ሊገድሏቸው ይፈልጉ ነበርና በመልአኩ ትዕዛዝ ሸሽተው በሊባኖስ ተራራ ላይ እመቤታችን እግዝትእነ ማርያም በተፀነሰች በ፱ ወር ከአምስት ቀን የግንቦት መባቻ ዕለት ግንቦት ፩ ተወለደች።

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያለን ምዕመናን ከጌታችን ልደት ቀጥሎ በታላቅ ድምቀት የምናከብረው የልደት በዓል የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደት ቀን ነው፡፡
ስለ ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል (ሉቃ 1፡14)›› ከተባለ የድንግል ማርያም ልደት ምንኛ የሚያስደስት ይሆን?! የነቢያቱ ትንቢት የተፈፀመበት፣ የታየው ራዕይም በገሀድ የተከናወነበት፣ የብሉይ ኪዳን ማብቂያ የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ ናትና ልደቷ ለሰው ልጆች ሁሉ (ለሕያዋን ሁሉ) ታላቅ የደስታ ቀን ነው፡፡ ሰማያውያን ቅዱሳን መላእክትም በንጽህናዋ በቅድስናዋ ተደንቀው “እህትነ ነያ/እህታችን እነኋት” ብለው ያመሰግኗታል፡፡ በዘመናችን ያሉ የሰዎች ልደት በድምቀት የሚከበር ከሆነ ለሰው ልጅ መዳን ምክንያት የሆነች የአምላክ እናት የተወለደችበት ቀን ምንኛ ሊከበር ይገባው ይሆን?! ቤተክርስቲያን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት በታላቅ ድምቀት የምታከብረው ከዚህ ታላቅ በዓል በረከት ረድኤትን እንድናገኝበት ነው፡፡ የሕይወት ክርስቶስ እናት ዛሬ ተወልዳለችና፡፡

እመቤታችን ለፀሐዩ መምጣት የተዘረጋች ሰማይ፣ በቅድመ አያቶቿ በነ ቴክታና ጰጥሪቃ ህልም እንደታየችው በሌሊት የምታበራ ጨረቃ ናት።
አባታችን አዳም በኃጢአት ከወደቀ በኋላ፣ ንስሃ በገባ ጊዜ አምላካችን ጌታ እግዚአብሔር የድኅነት ቃል ኪዳን ገባለት፡፡ ቃል ኪዳኑም “ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ” የሚል ነበር፡፡ ስለሆነም አዳም 5500 ዘመን የሕይወት ምክንያት የሆነች የልጅ ልጁ እመቤታችን ድንግል ማርያም ከአብራኩ ከተከፈሉ ቅዱሳን ልጆቹ የምትወለድበትን ቀን ተስፋ እያደረገ ኖረ፡፡ የእመቤታችንን የድንግል ማርያምን የመወለዷን ዜና ተስፋ በማድረግ “ሴት” ይላት የነበረውን ሚስቱን ሔዋንን በእመቤታችን ምሳሌነት “ሔዋን”፣ የሕያዋን ሁሉ እናት ብሎ ሰየማት፡፡ (ዘፍ. 3፡20) ዳግማዊ አዳም የተባለ ክርስቶስም የአዳምን ተስፋ በመስቀል ላይ በፈጸመ ጊዜ እውነተኛዋን ሔዋን (ዳግሚት፣ አማናዊት ሔዋንን) ድንግል ማርያምን በዮሐንስ ወንጌላዊ በኩል ለሕያዋን ምዕመናን ሁሉ እናት አድርጎ ሰጠ፡፡ (ዮሐ. 19፡26)

ይህን የከበረ ምስጢር የማይረዳ “ክርስቲያን” እንዴት ያሳዝናል!?
እኛ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ግን የቀዳማዊ አባታችንን የአዳምን፣ እንዲሁም በዳግም ተፈጥሮ ያከበረንን ዳግማዊ አዳም የተባለ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ቃል ተቀብለን “የሕያዋን ሁሉ እናት” ድንግል ማርያምን ልደቷን በፍፁም ደስታ እናከብራለን፣ ከተወደደ ልጇ ምሕረትን ትለምንልን ዘንድም ወደ እርሷ እናንጋጥጣለን፡፡

ሦሪያዊው ሊቅ ቅዱስ ኤፍሬም “አክሊለ ምክሕነ ወቀዳሚተ መድኀኒትነ፡፡ ወመሠረተ ንጽሕነ ኮነ በማርያም ድንግል፡-
የመመኪያችን ዘውድ የደኅንነታችን መጀመሪያ የንጽሕናችንም መሠረት በድንግል ማርያም ሆነልን” በማለት መናገሩ ስለዚህ ነው፡፡

አክሊል ምክሐነ አላት፦ ከነገሥታት መካከል እንደ ዳዊት የከበረ የለም፡፡ ምንም እንኳን ቅዱስ ዳዊት የከበረ ቢሆን የመመኪያችንን ዘውድ ማምጣት አልተቻለውም፡፡

ወቀዳሚተ መድኀኒትነ አላት፡- ከመሳፍንት ወገን የሚሆን ኢያሱ ምንም የስሙ ትርጓሜ መድኃኒት ማለት ቢሆንም የደኅንነታችን መጀመሪያ መሆን አልተቻለውም፡፡

ወመሠረተ ንጽሕነ አላት፡- ከነቢያተ እግዚአብሔር ወገን የሚሆን ኤልያስ በድንግልና በንጽሕና መኖሩ የሚታወቅ ነው፡፡ ነገር ግን ምንም ንጹሕ ድንግል ቢባል የንጽሕናችን መሠረት መሆን ግን አልተቻለውም፡፡
የመመኪያችን ዘውድ፣ የደኅንነታችን መጀመሪያ፤ የንጽሕናችን መሠረት ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፤” በማለት ተናግሯል፡፡ በእርሷ ምክንያትነት መድኀኒዓለም የሚፈጽምልንን ካሳ ነቢያትና የቀደሙ አበው ሁሉ የእርሷን መወለድ በናፍቆት ሲጠባበቁ ነበር፡፡ ከነቢያት አንዱ የሆነ ኢሳይያስም “የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ጎሞራም በመሰልነ ነበር፡፡” በማለት መናገሩ በእርሷ መገኘት ከጥፋት መዳናችንን ሲገልጽ ነው፡፡ ኢሳ. 1፥9

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትዉፊት መሰረት ሀና እና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደው በአድባረ ሊባኖስ ስር እመቤታችንን ወለዱ፡፡ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸዉ ‹‹ንፍሮና ጥራጥሬ›› ነበር፡፡ ይህንን ትውፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ውጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ ነገር ግን በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማውን ማስፈጸም የሚፈልገው ዲያቢሎስ በማር መካከል መርዝን ከሚጨምርባቸው መንፈሳዊ በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ (የእመቤታችን የልደት በዓል) ነው፡፡ በዚህ ዕለት አንዳንዶች ባለማወቅ ሌሎች ደግሞ በድፍረት ‹‹ለአድባር አውጋር ነው፤ ቆሌውን ለመለመን ነው›› እያሉ ለማያውቁት አምልኮ ንፍሮ የሚበትኑ፣ ቡና የሚረጩ፣ ቅቤ የሚቀቡ፣ የከብት ደም የሚያፈሱ አሉ፡፡ እውነታው እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸው፡፡ ስለሆነም ከእንደዚህ ዓይነቱ ባዕድ አምልኮ በመለየት ይህንን ታላቅ በዓል በተገባና በተረዳ ነገር ልናከብረው ይገባል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን በሠራችልን ሥርዓት መሰረት በቀናች በተዋሕዶ እምነት ሆነን፤ በምሕረቱ የጎበኘንን አምላካችንን ብቻ እያመለክን፤ የድኅነታችን ምክንያት የሆነችውን ድንግል ማርያምንም እያመሰገንን ልናከብረው ይገባል፡፡

ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት አባ ጽጌ ድንግልና አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታ በማሕሌተ ጽጌ የነገረ ማርያም መጽሐፋቸው ላይ:-
“ለንጉሠ ነገሥት ሰሎሞን ከመ ተፈሥሐ ልቡ
በዕለተ ወፃእኪ መርዓት ለአንበሳ ትንቢት እምግቡ
ማእከለ ማኅበር ፍሡሓን ተአምረኪ እንዘ እነቡ
እዜምር ለኪ ጽጌ ሐና ወፍኖተ ነፈርዐጽ እሌቡ
ከመ ጣዕዋ ሐሊበ ዘይጠቡ”
ትንቢት ከተነገረለት ከአንበሳ ጉድጓድ፤ ድንግል ሙሽራ በተገኘሽ ጊዜ የንጉሦች ንጉሥ የሰሎሞን ልቡ እንደተደሰተ፤ ደስ ባላቸው በመላእክት አንድነት ፊት ታምርሽን እየተናገርኊ የሐና አበባ ማርያም እዘምርሻለኊ፤ ወተትን ጠብቶ እንደሚዘልል እንቦሳም ዝለል ዝለል ይለኛል። በማለት ሰሎሞን ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት የተናገረው ትንቢት ፍጻሜውን አግኝቶ ታላቅ ደስታን ለኹላችን እንደሰጠን አብራርተው ገልጠዋል፡፡

ልሣንየ ላዕሌ ይሴብሑኪ
እግዝእትየ ዕብለኪ አዳም ንባብኪ
ወመሠረቱ ለዓለም አንቲ
ዕጓለ አንበሳ በከርሥኪ ፆርኪ
እምአንስት ቡርክት አንቲ
ለመሠረትኪ የኃትዎ ዕንቊ ክብር
አንቲ ውእቱ መንፈሳዊት ሃገር ንጽሕት ፀምር
ዘኃረያ ጸባዖት አማኑኤል !

ማርያም ማለት “ጸጋ ወሀብት” ማለት ነው፡፡
ቅዱስ ዳዊት (መዝሙር 126፥3) “ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው፡፡” ብሎ እንደተናገረ አባቷ ቅዱስ ኢያቄም እናቷ ቅድስት ሐና ከእግዚአብሔር የተሰጠችን ስጦታችን፣ ሀብታችን ናት ብለው “ማርያም” አሏት፡፡ ለጊዜው ለእናት እና ለአባቷ ስጦታ ሁና ትሰጥ እንጂ ለፍፃሜው ለፍጥረት ሁሉ እናት አማላጅ ሆና ከእግዚአብሔር የተሰጠች ናት።

ማርያም ማለት ፍፅምት( እንከንና ጉድለት የሌለባት) ማለት ነው፡፡ እመቤታችን ለጊዜው መልክ ከደምግባት ጋር አስተባብራ በመገኘቷ ፍፅምት ተብላለች፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በባሕርይው ቅዱስ ነው፡፡ (ዘሌ19፥2 ) ቅዱስ እና ንጹሐ ባሕርይ የሆነ እግዚአብሔር ዓለምን ለማዳን በወደደ ጊዜ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው እንደተናገረው “እግዚአብሔር በሰማይ ሁኖ ምሥራቁን እና ምዕራቡን ሰሜኑን እና ደቡቡን ዳርቻዎችን ሁሉ ተመለከተ እንዳንቺ ያለ አላገኝም የአንቺን መዓዛ ወደደ፤ ደም ግባትሽን ወደደ፤ የሚወደውን ልጁን ወደ አንቺ ሰደደ።” አለ።

ማርያም ማለት“ የሕያዋን እናት” ማለት ነው፡፡ (ዘፍ.3፥20) ላይ “አዳምም ለሚስቱ ሔዋን” ብሎ ስም አወጣ የሕያዋን ሁሉ እናት ናትና፡፡ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “ስለ ሔዋን የገነት ደጅ ተዘጋ ዳግመኛ ስለ ድንግል ማርያም ተከፈተልን” ብሎ እንደተናገረ።
ሔዋን ሕያዋንን ሁሉ አስጎዳች ዳግማዊት ሔዋን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ደግሞ ለሕያዋን ሁሉ እናት ሆና ፍጥረቱን ሁሉ ለማዳን ምክንያት ሆነች፡፡

ማርያም ማለት “መርሕ ለመንግሥተ ሰማያት” መንግሥተ ሰማያት መርታ የምታስገባ ማለት ነው፡፡ ዛሬ በዚህ አለም ለዕውር መሪ በትር እንዲሰጡት ሁሉ እርሷም በፍቅሯ፣ በጣዕመ ፍቅሯ የሰውን ሁሉ ኃጥያት ክፋት ፍቃ ከልጇ ከወዳጇ አስታርቃ፣ ከገሃነመ እሳት አውጥታ፣ መንግሥተ ሰማያት የምታስገባ ስለሆነች ስለዚህ መርህ ለመንግሥተ ሰማያት አሏት። የቀደመው ፍጥረት የታደሰባት ወደ ቀደመ ርስቱ ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ምክንያተ ድሂን የሆነችው እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት ዛሬም ያለው ፍጥረት ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባት የድንግል ማርያም ምልጃ ያስፈልገዋል፡፡

ማርያም" ማለት ልዩ ከጣዖት፣ ክብርት እምፍጥረታት፣ ንጽህት እምሃጢአት፣ መልክ ከደም ግባት የተሰጣት ማለት ነው።
"ማርያም" ማለት ተፈስሂ ቤተ ይሁዳ ወተሃሠዪ ቤተ እስራኤል ማለት ነው።
አንድም ማርያም ማለት ሰረገላ ፀሃይ ማለት ነው።
አንድም ማርያም ማለት ተላኪተ እግዚአብሄር ወሰብእ ማለት ነው።
አንድም ማርያም ማለት ውብህት(ስጥዉት) ማለት ነው።
አንድም "ማርያም" ማለት:-
""ማ"" ማለት ማህደረ መለኮት:
""ር"" ማለት ርግብየ ይቤላ:
""ያ"" ማለት ያንቀዓዱ ኃቤኪ ኩሉ ፍጥረት:
""ም"" ማለት ምስሃል ወምስጋድ ወምስትሥራየ ኃጢያት ማለት ነው።

ማርያም — እመ አምላክ ናት
ንጉሥ ክርስቶስ አምላክ በመሆኑ የወለደችው እመ አምላክ ሆነች።
ማርያም— እመ ብርሃን ናት
ንጉሥ ክርስቶስ ብርሃን በእሱ ዘንድ የማይጨልም በመሆኑ የብርሃን እናት ሆነች ብርሃን የሆነውን ወልዳለችና፤
ማርያም — እመ አዶናይ ናት
ንጉሥ ክርስቶስ የዓለም ሁሉ አዳኝ መድኃኒት በመሆኑ የወለደችው እመ አዶናይ የመድኃኒት እናት ሆነች
ማርያም — የፍቅር እናት ናት
ንጉሥ ክርስቶስ አምላክ ሲሆን ሰው በመሆኑ ለሰው ያለውን ፍቅር በመስቀል ላይ በመግለፁ የወለደችው የፍቅር እናት ሆነች፤ ክርስቶስ ፍቅር ነውና እናቱ ደግሞ የፍቅር እናት ትባላለች።

ማርያምሰ ወሕልቀተ ትርሲት ለአጻብዒነ
ወአሣእነ መድኃኒት ለአእጋሪነ
ወአልባሲ ምክሕ ለዕርቃንነ
መሶበ ወርቅ እንተ መና ለረኃብነ
ወጽዋዐ ወርቅ እንተ ወይን ለጽምእነ
እንተ ታወፊ ሕይወተ ለምውታን
ወትጼጉ መድኃኒተ ለድውያን
ወትውህብ ብዕለ ለነዳያን
ወክብረ ለትሑታን።

ድንግል ማርያም ለጣቶቻችን የሽልማት ቀለበት
ለእግሮቻችንም የድኅነት ጫማ
ለራቁትነታችንም የመመካት ልብስ ናት
ለራባችን ጊዜም መና ያለባት የወርቅ መሶብ ናት።
ለመጠማታችንም ወይንን የያዘች የወርቅ ጽዋ ናት።
ለሞቱት ሕይወትን ትሰጣለች።
ለታመሙት ፈውስን ለተቸገሩትም ሀብትን ትሰጣለች።
ለተዋረዱትም ክብርን ታቀዳጃለች።

ሰላም ለልደትኪ እማኅጸነ ድክምት ሥጋ፤
ድኅረ ኃለፋ ውርዙት ወድኅረ ትክቶ ኃደጋ፤
ማርያም ሥመሪ ወጺሐኪ እንበለ ንትጋ፤
ለማየ ንጽሕኪ ትረስዪኒ ፈለጋ፤
እስመ ንጽሕ ይሁብ ሞገሰ ወጸጋ።

አምላካችን እግዚአብሔር ከእመቤታችን ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡ አሜን
በድጋሜ እንኳን ለ2032ኛው የእመቤታችን ቅድስተ ቅዱሳን፣ ንጽሒተ ንጹሐን የመመኪያችን ዘውድ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም የልደት ቀን አደረሰን አደረሳችሁ ‼

ምሥራቀ ምሥራቃት መፃአ ፀሐይ
እግዝእትነ ዘመና ሙዳይ
ተወልደት ዮም ዳግሚት ሰማይ።

ልደትሽ ልደታችን ነው ‼
Petros Ashenafi kebede

 !![የአምላክ እናት ልደት (ልደታ ለማርያም)]በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ ♥ ቀደምት የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት መተርጒማን እንዳስተማሩንና አበው በነገረ ማርያም ላይ እንደጻፉልን ሐና...
09/05/2025

!!

[የአምላክ እናት ልደት (ልደታ ለማርያም)]

በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
♥ ቀደምት የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት መተርጒማን እንዳስተማሩንና አበው በነገረ ማርያም ላይ እንደጻፉልን ሐናና ኢያቄምንም “ወክልኤሆሙ ኄራን ወሥሙራን እሙንቱ ወየሐውሩ በሕገ እግዚአብሔር እስመ እግዚአብሔር ኀረዮሙ ወአፍቀሮሙ ትካት” ይላቸዋል እግዚአብሔርን የሚወድዱ በሕጉ የሚኖሩ ደጋጎችና አምላክም የመረጣቸው ነበሩ።

❤ ሐና መካን በመኾኗ ምክንያት ኹለቱም ወደ ቤተ እግዚአብሔር ዕለት ዕለት በመኼድ ለዐይናቸው ማረፊያ ለልባቸው ተስፋ የሚኾን ልጅ እንዲሰጣቸው ይለምኑ እንደነበር፤ “Protoevangelium of James” (ፕሮቶቫንጊሊዩም ኦፍ ጀምስ) የሚለው ያዕቆብ የጻፈው ጥንታዊዉ መጽሐፍ በስፋት ይገልጻል፡፡

♥ ከዕለታት ባንደኛው ሲያዝኑ ሲጸልዩ ውለው ሲመለሱ “ወርእዩ አርጋበ እንዘ ይትፌሥሑ ምስለ ውሉዶሙ” ይላል ርግቦች ከልጆቻቸው ጋር ደስ ብሏቸው ሲጫወቱ አይተው ሐና “አቤቱ ጌታዬ ግዕዛን ለሌላት እንስሳ ልጅ የሰጠኽ አምላክ ምነው ለኔ ልጅ ነሣኸኝ” ብላ ምርር ብላ አለቀሰች፤ ወዲያው ሱባዔ ይገባሉ፤ ኢያቄም ወደ በረሓ ኼዶ ሲጸልይ ሐና ደግሞ በቤቷ ዙሪያ ባለው የተክል ቦታ ሱባዔ ያዘች።

♥ በሱባዔያቸው ፍጻሜ ኹለቱም ራእይ አይተው ተነጋግረዋል፡፡ “ይቤላ ኢያቄም ለሐና ብእሲቱ እንዘ ይትረኀዉ ሰብዐቱ ሰማያት ዖፍ ጸዐዳ መጽአ ኀቤየ ወነበረ ዲበ ርእስየ” ይላል ሰባቱ ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ዎፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየኊ ብሎ የተገለጸለትን ለሐና ነግሯታል።

♥ ይኸውም የራእዩ ምስጢር፡- ወፍ የተባለው አካላዊ ቃል ክርስቶስ ሲኾን፤ ነጭነቱ ንጽሐ ባሕርዩ ነው፤ ከላይ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየኊ ማለቱ የኢያቄምን ባሕርይ ባሕርይ እንደሚያደርግ ሲያጠይቅ ሲኾን፤ ሰባቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ምልአቱ፣ ስፍሐቱ፣ ርቀቱ፣ ልዕልናው፣ ዕበዩ ናቸው፡፡

♥ ሐናም ተገልጾላት “ትቤሎ ሐና ለኢያቄም ብእሲሃ አነኑ ርኢኩ በሕልምየ ርግብ ጸዐዳ መጽአት ኀቤየ ወነበረት ዲበ ርእስየ ወቦአት ውስተ እዝንየ ወኀደረት ውስተ ከርሥየ” ይላል ለባሏ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ በዦሮዬ ገብታ በማሕፀኔ ስትተኛ አየኊ ብላዋለች።

♥ ይኽ የራእይ ምስጢር፡- ርግብ የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስትኾን፤ ነጭነቷ ንጽሕናዋ፣ ቅድስናዋ፣ ዘላለማዊ ድንግልናዋ ነው፤ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ ወደ ዦሮዬ ገብታ በማሕፀኔ ስትተኛ አየኊ ማለቷ ብሥራተ ገብርኤልን በዦሮዋ ሰምታ በግብረ መንፈስ ቅዱስ አምላክን የምትፀንሰውን ንጽሕት ርግብ የተባለችውን እመቤታችንን የምትወልድ መኾኗን ሲያጠይቅ ነው፡፡

♥ ኢያቄምና ሐናም ይኽነን ራእይ ሐምሌ ፴ ቀን ካዩ በኋላ “ወንድ ልጅ ብንወልድ ወጥቶ ወርዶ ይርዳን አንልም ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ይኾናል፤ ሴትም ብንወልድ ለቤተ እግዚአብሔር መጋረጃ ፈትላ ትኑር” ብለው ስእለት ከተሳሉ በኋላ ራእይ አየን ብለው ዕለቱን አልተገናኙም፤ አዳምንና ሔዋንን “ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሏት” ብሎ የተናገረው አምላክ ለእኛም ይግለጽልን ብለው ዕለቱን አልጋ ምንጣፍ ለይተው እስከ ሰባት ቀን ድረስ እየብቻቸው ሰነበቱ።

♥ ነሐሴ በባተ በሰባተኛው ቀን “ከሰው የበለጠች ከመላእክት ኹሉ የከበረች ልጅ ትወልዳላችኊ" ብሎ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለሐና ነግሯት በፈቃደ እግዚአብሔር በብሥራተ መልአክ እመቤታችን ነሐሴ ሰባት እሑድ ተፀንሳለች፤ በእናቷ ማሕፀን ሳለችም “መንፈስ ቅዱስ ዐቀባ እምከርሠ እማ” እንዲል እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጥንተ አብሶ ባመጣው መርገም እንዳትያዝ ጠብቋታል፡፡

♥ ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም መፀነስ ከሊቃውንት መኻከል አባ ጽጌ ድንግልና አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታ በማሕሌተ ጽጌ መጽሐፋቸው ላይ፦

✍ “ሚ ቡርክት ወቅድስት ይእቲ
ሰዓተ ትፍሥሕት ሐና ዘጸገየተኪ ባቲ
ወፈረየኪ ለሕይወት ኢያቄም መዋቲ
እሴብሕ ተአምረኪ ርግብየ አሐቲ
ወድኀኒተ ኲሉ ዓለም እስመ ኮንኪ አንቲ”

♥ (ሐና አንቺን የፀነሰችባት የደስታ ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ናት፤ ሟች ኢያቄምም ለሕይወት አንቺን ያፈራባት ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ናት፤ አንዲቱ ርግቤ ማርያም አንቺ የዓለሙ ኹሉ መድኀኒት ኾነሻልና ታምርሽን አመሰግናለኊ) በማለት ዓለምን ኹሉ በደሙ ፈሳሽነት ያዳነ ንጉሣችን፣ ፈጣሪያችን ክርስቶስን በድንቅ ተአምር ማኅተመ ድንግልናዋ ሳይለወጥ የወለደችልን ምክንያተ ድኂን ርግበ ሰሎሞን የተባለች የቅድስት ድንግልን የመፀነሷን ነገር በአድናቆት ገልጸዋል፡፡

♥ “ወእምድኅረ ስድስቱ አውራኅ ተዐውቀ ፅንሳ ለሐና” ይላል፤ ከስድስት ወርም በኋላ የሐና ፅንሷ እየታወቀ ሲመጣ ጎረቤቶቿ መፅነሷን ይረዱ ዘንድ በአድናቆት ማሕፀኗን ይዳስሱ ነበር፤ በተለይም ዐይኗ የታወረ የሐና ዘመዷ የአርሳባን ልጅ የምትኾን አንዲት ሴት የሐናን ማሕፀን ዳስሳ ዐይኗን ብትነካው በርቶላት በታላቅ ደስታ ኾና “ብፅዓን ለኪ ኦ ሐና እስመ እም ፍጥረተ ዓለም አልቦ ዘከማኪ ዘይፌውስ በከርሡ አዕይንተ ዕውራን” (ሐና ሆይ ብፅዓን ይገባሻል ዓለም ከተፈጠረ ዠምሮ እንዳንቺ በማሕፀኑ የዕውራንን ዐይን የሚያበራ የለምና) በማለት አመስግናታለች፤ ከዚኽ በኋላ ዝናዋ በሀገሩ ኹሉ ተሰምቶ ሕሙማን ኹሉ ማሕፀኗን እየዳሰሱ ይፈወሱ ነበር፡፡

♥ አባ ጽጌ ድንግልና አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታ በማሕሌተ ጽጌ መጽሐፋቸው ላይ ይኽነን ሲገልጹ፦
✍ “ጸግይየ ሣዕረ ዘኪሩቤል ልሳነ
ተአምረኪ በነጊር እመ ኢፈጸምኩ አነ
ባሕቱ አአኲት ማርያም ዘጾረተኪ ማሕፀነ
እንዘ ሀለወት ፀኒሳ ኪያኪ ርጢነ
ለለገሰስዋ ላቲ ትፌውስ ዱያነ”

♥ (ሳርን የኾንኊ እኔ የኪሩቤል አንደበትን ገንዘብ አድርጌ ታምርሽን በመንገር በማስተማር ባልፈጽምም ነገር ግን ማርያም የተሸከመቺሽን ማሕፀን አመሰግናለኊ፤ መድኀኒት አንቺን ፀንሳ ሳለች ርሷን የዳሰሷትን ድዉያንን ኹሉ ትፈውስ ነበር) በማለት እመ መድኅነ ዓለም ገና ሳትወለድ የተሠራውን ድንቅ ተአምር አመስግነዋል፡፡

♥ ይኽ የቅድስት ድንግል ማርያም የፅንሰት በዓል በመላው ዓለም የሚታወቅ ሲኾን ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት የኾነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን የአምላክ እናት የተፀነሰችበት ይኽነን በዓል ነሐሴ ፯ ቀን በታላቅ ድምቀት በማሕሌት፣ በቅዳሴ የምታስበው ሲኾን በዓሉም “ፅንሰታ ለማርያም” በመባል ይታወቃል።

♥ በዓለም ላይ ያሉ ክርስቲያኖች ደግሞ በዓሉን “The conception of the Theotokos” (የአምላክ እናት መፀነስ) በማለት ሲያከብሩት ወሩን ግን የልደት በዓልን ለማክበር በሚዘጋጁበት በታኅሣሥ አድርገው በ፱ኛው ቀን “December 9” ላይ ያስቡታል ፡፡

♥ በእጅጉ የሚደንቀው ደግሞ “ሳሚናስ ወልደ ጦሊቅ ዘይነብር ውስተ ቤተ ዶይቅ” ይላል ሳሚናስ የሚባል የጦሊቅ ልጅ ከኤዶቅ ካጐቱ ቤት ኼዶ ሞተ፤ ሐናም በሀገራቸው ልማድ የአልጋውን ሸንኮር ይዛ እየዞረች ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ፈጥኖ ተነሥቶ “ሰላም ለኪ ኦ ሐና እምሔውቱ ለዘገብረ ሰማየ ወምድረ” (ሰማይና ምድርን ለፈጠረው አምላክ አያቱን የተባልሽ ሐና ሰላም ላንቺ ይኹን) አላት።

♥ ከዚያ የነበሩ አይሁድም በመደናገጥ “ሳሚናስ ምን አየኽ? ምን ትላለኽ?” አሉት፤ ርሱም “ከዚች ከሐና ማሕፀን የምትወለደው ሕፃን ሰማይ ምድርን የፈጠረ አምላክን ትወልዳለች እያሉ መላእክት ኹሉ ሲያመሰግኗት ሰማኋቸው፤ እኔንም ያነሣችኝ ርሷ ናት” አላቸው፤ እነርሱም ይኽነን በሰሙ ጊዜ እግዚአብሔርን ከማመስገን ይልቅ በቅናትና በክፋት ተመልተው ሐና በማሕፀን ባለ ፅንሷ ካዳነች በኛ ላይ ልትሠለጥን አይደለምን? “ንዑ ንገሮሙ ለሐና ወለኢያቄም” ሳትወልድ አስቀድመን ሐናና ኢያቄምን በድንጋይ ወግረን እንግደላቸው ብለው ተነሣሡባቸው።

♥ ያን ጊዜ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለኢያቄም ተገልጾ ሐናን ሊባኖስ ወደሚባል ተራራ እንዲወስዳት ነገረው፤ ጠቢቡ ሰሎሞን በመንፈሰ እግዚአብሔር ተቃኝቶ እመቤታችን በሊባኖስ ተራራ እንደምትወለድ ተገልጾለት፡-
✍“ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ ንዒ ወተወፅኢ እምቅድመ ሃይማኖት እምርእሰ ሳኔር ወኤርሞን አምግበበ አናብስት ወእምአድባረ አናምርት” (ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ነዪ ከሊባኖስ ነዪ ከአማና ራስ ከሳኔር ከኤርሞን ራስ ከአንበሶች መኖሪያ ከነብሮችም ተራራ) በማለት የተናገረው ትንቢት ሊፈጸም ቅድስት ድንግል ማርያም በሊባኖስ ተራራ ተወልዳለች (ማሕ ፬፥፲)፡፡

♥ ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት አባ ጽጌ ድንግልና አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታ በማሕሌተ ጽጌ የነገረ ማርያም መጽሐፋቸው ላይም፦
“ለንጉሠ ነገሥት ሰሎሞን ከመ ተፈሥሐ ልቡ
በዕለተ ወፃእኪ መርዓት ለአንበሳ ትንቢት እምግቡ
ማእከለ ማኅበር ፍሡሓን ተአምረኪ እንዘ እነቡ
እዜምር ለኪ ጽጌ ሐና ወፍኖተ ነፈርዐጽ እሌቡ
ከመ ጣዕዋ ሐሊበ ዘይጠቡ”

♥ (ትንቢት ከተነገረለት ከአንበሳ ጉድጓድ፤ ድንግል ሙሽራ በተገኘሽ ጊዜ የንጉሦች ንጉሥ የሰሎሞን ልቡ እንደተደሰተ፤ ደስ ባላቸው በመላእክት አንድነት ፊት ታምርሽን እየተናገርኊ የሐና አበባ ማርያም እዘምርሻለኊ፤ ወተትን ጠብቶ እንደሚዘልል እንቦሳም ዝለል ዝለል ይለኛል) በማለት ሰሎሞን ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት የተናገረው ትንቢት ፍጻሜውን አግኝቶ ታላቅ ደስታን ለኹላችን እንደሰጠን አብራርተው ገልጠዋል፡፡

♥ ይኽ የእመቤታችን ልደት ለሰማያውያን መላእክትና ለደቂቀ አዳም ደስታ ሲኾን አካላዊ ቃል ክርስቶስ ከርሷ ተወልዶ ዲያብሎስ ፭ሺሕ፭፻ ዘመን በሲኦል ያኖራቸውን ነፍሳት ወደ ገነት የሚያስገባቸው ነውና፤ ሰይጣን በተቃራኒው ልደቷ እንዳላስደሰተው ሲገልጹ፦

✍ “ተፈሥሐት ምድር ወሰማይ አንፈርዐጸ
በዕለተ ጸገዩኪ አብላስ ወአውጽኡ ሠርጸ
ተአምረ ሕይወት ማርያም ዘአልብኪ ቢጸ
እስከ ፈርሀ መልአከ ሞት ወሰይጣን ደንገጸ
ዜና ልደትኪ ነጐድጓድ እስከ (ውስተ) ሲኦል ደምፀ”

(በለሶች (ኢያቄምና ሐና) ቡቃያ አንቺን ባስገኙሽ ጊዜ ምድር ደስ አላት ሰማይም ደስ አለው፤ ጓደኛ (ምሳሌ) የሌለሽ የድኅነት ምልክት ማርያም፤ መልአከ ሞት እስከ ፈራና ሰይጣንም እስከ ደነገጠ ድረስ የመወለድሽ ዜና እስከ ሲኦል ድረስ (በሲኦል) ተሰማ) በማለት አስተምረዋል፡፡

♥ ጠቢቡ ሰሎሞን አስቀድሞ በመንፈሰ እግዚአብሔር ተቃኝቶ በማሕልይ 6:10 ላይ “መኑ ይእቲ ዛቲ እንተ ትሔውጽ ከመ ጎሕ ሠናይት ከመ ወርኅ ወብርህት ከመ ፀሓይ” (ይኽቺ እንደ ማለዳ ብርሃን የምትጐበኝ እንደ ጨረቃ የተዋበች፤ እንደ ፀሓይም የጠራች ዐላማ ይዞ እንደተሰለፈ ሰራዊት የምታስፈራ ማን ናት?) በማለት እንደ ፀሓይ የሞቀ እንደ ጨረቃ የደመቀ ንጽሕናዋና ቅድስናዋ የመልኳ ደም ግባት በነቢያት ትንቢት አስቀድሞ የተጐበኘላት የእውነት ፀሓይ የክርስቶስ እናት የቅድስት ድንግል ማርያምን ክብርና ደም ግባቷን እንደተናገረ በሊባኖስ ተራራ በግንቦት ፩ በተወለደች ጊዜ ፊቷ በእጅጉ ያበራ ነበር፤ መዐዛዋም ከሽቱ ኹሉ ይበልጥ ነበር፡፡

♥ የፈጣሪያችን እናት ቅድስት ድንግል የተወለደችበትን ግንቦት አንድን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን “ልደታ ለማርያም” በማለት ከጥንት ዠምሮ በታላቅ መንፈሳዊ ሐሤት በቅዳሴ፣ በማሕሌት የምታከብርላት ሲኾን፤ በተለያዩ ክፍላተ ዓለማት ያሉ ክርስቲያኖችም ይኽነን በዓል “The Nativity of the blessed Virgin Mary” (የተባረከችው የድንግል ማርያም ልደት (መወለድ)) በማለት ያስባሉ።

♥ በጥንት ምሥራቃውያን (እንደ ቤዛንታይን ባሉ) ዘንድ ዐዲሱ ዓመት ልክ እንደኛ መስከረም ወር “September” ላይ ይውል ስለነበር መስከረም ፰ (September 8) ያከብሩት የነበረ እንደነበር ታሪክ ሲያስረዳ ይኽነን ይዘው በዚኽ ዕለትም የሚያከብሩት ብዙዎች የዓለማት ሀገራት አሉ፡፡
✍ ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ [በድጋሚ ፓስት የተደረገ]
[ነገረ ማርያም በሐዲስ ኪዳን፤ ነገረ ማርያም በሊቃውንት ክፍል አንድ ከሚለው መጽሐፌ የተወሰደ]

👉 እኔ ታናሽ አገልጋይሽም እመቤቴ ወላዲተ አምላክ ሆይ የፀሐይ መገኛ ሰማይ፤ የመና እናት መሶብ፤ የፍሕም እናት ማዕጠንት፤ የብርሃን እናት መቅረዝ፤ የጠል እናት ፀምር ተገኝተሻልና በልደትሽ ደስ ብሎናል። እናቴ ሆይ እንኳን ተወለድሽ እላለሁ።

👉 እናንተም አንባብያን ሆይ በአስተያየት መስጫው ላይ የእመቤታችንን ልደቷን አስመልክታችሁ የደስታ መፍሰሻ ለሆነች ለእመቤታችን ልደቷን አስመልክታችሁ ደስታችሁን ግለጹላት።

Address

Debre Mark'os

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ገዳም አስቄጥስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም - ደብረማርቆስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share