Zedo Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Zedo, 04, Debre Birhan.

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩየቀድሞው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተ...
19/10/2025

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የቀድሞው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተገለፀ፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ወደ አኼራ ሄደዋል ሲል የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡

ጠቅላይ ምክርቤቱ በመግለጫው፤ "የሀገራችን ዋርካ እና የሁሉም አባት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ህልፈታቸው የመላው ሀገራችን ህዝብ ሀዘን ነው" ብሏል፡፡

"ሀገራችን ታላቅ አባት አጥታለች" ያለው ምክርቤቱ፤ "እኚህን ታላቅ አባት ላበርክቷቸው ሀገራዊና ሃይማኖታዊ አስተዋፆ በሚመጥን መልኩ ስርዓተ ቀብራቸው በመንግስት ደረጃ ኢስላማዊ ስነ ስርዓቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከናወን ጠቅላይ ምክር ቤቱ ኃላፊነቱን በመውሰድ የሚፈፅም መሆኑን" ጠቁሟል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በማረፋቸው የተሰማቸውን ሀዘን በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልፀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው፤ "ሐጂ ዑመር በአመራር ዘመናቸው የተለያዩ ወገኖች ወደ አንድነት እንዲመጡ እና የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሕግ ዕውቅና እንዲኖረው ያደረጉትን አስተዋጽዖ ሁሌም እናስታውሰዋለን" ብለዋል።

አክለውም ለቤተሰቦቻቸው እና ለመላ ኢትዮጵያ ሙስሊሞች መጽናናትን ተመኝተዋል።
https://t.me/Ayunews_2
https://t.me/Ayunews_2
‎‌‎

ዝግጁ ሀኗል‼"አየር ኃይል የትኛውንም ግዳጅ ለመፈፀም በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል" ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳአየር ኃይል የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ ለመፈፀም በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ...
15/10/2025

ዝግጁ ሀኗል‼

"አየር ኃይል የትኛውንም ግዳጅ ለመፈፀም በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል" ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ

አየር ኃይል የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ ለመፈፀም በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል አሉ የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ፡፡

የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለአየር ኦፕሬሽን በግዳጅ አፈጻጸም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ክፍሎች እውቅና ሰጥቷል፡፡

ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ በዚህ ወቅት÷ተቋሙ የሚሰጠውን ተልዕኮ እና ግዳጅ ለመፈፀም በከፍተኛ የዝግጁነት አቅም ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል ።

አየር ኃይል በአጭር ጊዜ ባከናወናቸው የለውጥ ሥራዎች አስደናቂ ስኬቶችን አስመዝግቧል ያሉት ዋና አዛዡ ይህም የአመራሩና የአባላቱ የጋራ ሥራ ውጤት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

አየር ኃይል ም/አዛዥ ለአየር ኦፕሬሽን ብ/ጄ ተስፋዬ ለገሰ በበኩላቸው÷ ክፍሉ የኢትዮጵያን የአየር ክልል በንቃት በመጠበቅ የተቋሙን የውጊያ ዝግጁነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ግዳጃቸውን በብቃት ለተወጡ ክፍሎች የእውቅናና የምስጋና ሰርተፍኬት መሰጠቱንም ፋና ዘግቧል።

አሁናዊ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/Ayunews_2
https://t.me/Ayunews_2
‎‌‎

ያልተጠበቀ ምላሽ‼አሜሪካ ለግብፅ ያልተጠበቀ ምላሽ መስጠቷ ተሰምቷል።ግብፅ የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲያደርግ እየጠየቀች ባለችበት ወቅት ያልተጠበቀ ምላሽ ከአሜሪካ እንዳገኘች...
14/10/2025

ያልተጠበቀ ምላሽ‼

አሜሪካ ለግብፅ ያልተጠበቀ ምላሽ መስጠቷ ተሰምቷል።

ግብፅ የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲያደርግ እየጠየቀች ባለችበት ወቅት ያልተጠበቀ ምላሽ ከአሜሪካ እንዳገኘች ታውቋል።

በቅርቡ በፕሬዝደንት ትረምፕ የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ተደርገው የተሾሙት ማሳድ ቦውሎስ ሀገራቸው ኢትዮጵያ እና ግብፅ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ድጋፍ እንደምታደርግ ገልፀው የህዳሴ ግድብ ውዝግብ ፖለቲካዊ ሳይሆን ቴክኒካዊ ምላሽ እንዲያገኝ አሳስበዋል።

"ሁላችንም ጉዳዩ እንዲፈታ እና ለሁሉም ተቀባይ እንዲሆን እንፈልጋለን፣ በተለይ ደግሞ በቴክኒክ በኩል፤ ምክንያቱም ጉዳዩ የቴክኒክ ስለሆነ ቴክኒካዊ ምላሽ ያስፈልጋል" ሲሉ አል አረቢያ ለተባለው ሚድያ ተናግረዋል።

"አሁን ግድቡ ስለተጠናቀቀ እውን የሆነ ጉዳይ ነው፣ በዚህ መሬት ላይ ባለ እውነታ ዙርያ መፍትሄ ያስፈልጋል:ግድቡ ስላለቀ ፖለቲካ አታድርጉት" በማለት አሜሪካዊው ዲፕሎማት መናገራቸው ተዘግቧል።

አሁናዊ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/Ayunews_2
https://t.me/Ayunews_2
‎‌‎

ትንታኔ፡ የ  #ኢትዮጵያና  #ሶማሌላንድ ስምምነት – ያልተሟላ ቃልኪዳንና የፕሬዝዳንት አብዱላሂ የአዲስ አበባ ጉብኝት አንድምታየሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን መሐመድ አብዱላሂ እ.ኤ.አ ...
14/10/2025

ትንታኔ፡ የ #ኢትዮጵያና #ሶማሌላንድ ስምምነት – ያልተሟላ ቃልኪዳንና የፕሬዝዳንት አብዱላሂ የአዲስ አበባ ጉብኝት አንድምታ

የሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን መሐመድ አብዱላሂ እ.ኤ.አ ኅዳር 2024 ከተመረጡ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል።

የፕሬዝዳንት አብዱራህማን ጉብኝት የሚከናወነው ከዜና አርዕስት የዘለለ ለውጥ ያላስገኘውን ጥር 2024 የተፈረመውን የኢትዮጵያ–ሶማሌላንድ የጋራ መግባቢያ ስምምነት (MoU) ተከትሎ ነው።

የቀድሞው የሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ በታኅሣሥ ወር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ ከአፍሪካ ኅብረት፣ ከአረብ ሊግ እና “ከዋና ዋና ዓለም አቀፍ አጋሮች” እየጨመረ የመጣው ግፊት የጋራ መግባቢያ ስምምነቱ እንዲቋረጥ ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሃመድ በቅርቡ ከአል አረብያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ በቀይ ባሕር ዳርቻ የሚገኙ ሀገራት ሉዓላዊነትን በማክበር እና ቀጠናዊ ግጭትን ሊያባብሱ የሚችሉ ድርጊቶችን በማስወገድ ውይይትና ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። ነገር ግን ፕሬዝዳንቱ በቀይ ባሕር ዙሪያ ያሉ ውጥረቶችን ለመቆጣጠር "ሰላማዊ ውይይት እና የግዛት አንድነት መከበር" አስፈላጊ መሆኑን በአጽንዖት ገልጸዋል። “የትኛውም ሀገር የሌላን ሀገር ሉዓላዊነት ሊጥስ አይገባም” ሲሉም ተናግረዋል።
https://t.me/Ayunews_2
https://t.me/Ayunews_2
‎‌‎

የትራምፕ ጅንጀና ወይስ ሙገሳ❤️❤️❤️ትራምፕ ለጣልያኗ መሪ መሎኒ ፡ 'አንቺ ቆንጆ ነሽ። ይሄንን ብልሽ ቅር አይልሽም አይደል?'" አሉ "እዚህ ወጣት ሴት አለችን። ይሄን እንድል አልተፈቀደል...
14/10/2025

የትራምፕ ጅንጀና ወይስ ሙገሳ❤️❤️❤️

ትራምፕ ለጣልያኗ መሪ መሎኒ ፡ 'አንቺ ቆንጆ ነሽ። ይሄንን ብልሽ ቅር አይልሽም አይደል?'" አሉ

"እዚህ ወጣት ሴት አለችን። ይሄን እንድል አልተፈቀደልኝም – በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ይሄንን ማድረጉ ብዙውን ጊዜ ስራን እስከማጣት ያደርሳል – ግን አደጋውን እወስዳለሁ፡ እሷ ወጣት፣ ቆንጆ ሴት ነች። እዚህ መሆን ፈልጋለች፣ አስገራሚ ነው። በጣሊያን በጣም የተሳካላት ፖለቲከኛ ነች። ቆንጆ ነሽ ብልሽ ቅር አይልሽም? ምክንያቱም በእውነት ቆንጆ ነሽ።"

የአሜሪካው መሪ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመካከለኛው ምስራቅ የሰላም ጉባኤ ላይ ከጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ መሎኒ ጋር ባደረጉት ንግግር የተናገሯቸው ቃላት ናቸው።
https://t.me/Ayunews_2
https://t.me/Ayunews_2
‎‌‎

❗ሩሲያ በዩክሬን ሰላማዊ እልባት ለማግኘት ዝግጁ ብትሆንም አማራጮች ባለመኖራቸው በልዩ ወታደራዊ ዘመቻዋ ቀጥላለች - ክሬምሊን ዲሚትሪ ፔስኮቭ የሰጧቸው ሌሎች ቁልፍ መግለጫዎች፦ 🟠 የፕሬዝዳን...
14/10/2025

❗ሩሲያ በዩክሬን ሰላማዊ እልባት ለማግኘት ዝግጁ ብትሆንም አማራጮች ባለመኖራቸው በልዩ ወታደራዊ ዘመቻዋ ቀጥላለች - ክሬምሊን

ዲሚትሪ ፔስኮቭ የሰጧቸው ሌሎች ቁልፍ መግለጫዎች፦

🟠 የፕሬዝዳንት ትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ውጤታማ ተደራዳሪነታቸውን አረጋግጠዋል፤ ክሬምሊን የማደራደር ብቃታቸው ለዩክሬን እልባት አስተዋጽኦ ማድረጉን እንደሚቀጥል ተስፋ ያደርጋል።

🟠 ክሬምሊን አሜሪካ የዩክሬንን ግጭት ለመፍታት የምታደርጋቸውን ጥረቶች በደስታ ትቀበላለች።

🟠 ሩሲያ በአንድም በሌላ ጥቅሞቿን በማረጋገጥ በልዩ ወታደራዊ ዘመቻው የተቀመጡ ግቦችን ታሳካለች።

🟠 ሩሲያ በዩክሬን ጉዳይ ለሰላማዊ ውይይት ዝግጂ ሆና ትቀጥላለች።

አሜሪካ ለኪዬቭ ማቅረብ የምትችለው ከ20 እስከ 50 የሚደርሱ ቶማሃውክ ሚሳኤሎች ብቻ ነው ተባለይህም ሀገሪቱ በአጠቃላይ 4 ሺህ 150 ያህል የቶማሃውክ ሚሳኤሎች ቢኖሯትም እንደሆነ የቀድሞ የ...
14/10/2025

አሜሪካ ለኪዬቭ ማቅረብ የምትችለው ከ20 እስከ 50 የሚደርሱ ቶማሃውክ ሚሳኤሎች ብቻ ነው ተባለ

ይህም ሀገሪቱ በአጠቃላይ 4 ሺህ 150 ያህል የቶማሃውክ ሚሳኤሎች ቢኖሯትም እንደሆነ የቀድሞ የፔንታጎን ባለሥልጣን ለመገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።

አቅርቦቶቹ በዩክሬን ግጭቱ ያለበትን ሁኔታ በጉልህ እንደማይለውጡትም በዘገባው ተመላክቷል፡፡

ይህ ግምገማ ፑቲን በጥቅምት ወር መጀመሪያ የተናገሩትን ግምት የሚያስተጋባ ነው።

👉 የቶማሃውክ ሚሳኤሎች ለኪዬቭ ከተላለፉ ሩሲያ የአየር መከላከያ ስርዓቶቿን ታጠናክራለች ሲሉ የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቀደም ሲል ተናግረዋል። በተጨማሪም የእነዚህ ሚሳኤሎች አጠቃቀም ቀጥተኛ የአሜሪካ ወታደራዊ ተሳትፎ ከሌለ የማይቻል እንደሆነና ይህም የሞስኮ እና ዋሽንግተንን ግንኙነት ይበልጥ ውጥረት ውስጥ እንደሚከተው አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
https://t.me/Ayunews_2
https://t.me/Ayunews_2
‎‌‎

የሶማሊላንድ አዲሱ ተመራጭ ፕሬዚዳንት ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ እየመጡ ነው። ፕሬዝዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ ግብዣ የቀረበላቸው በጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ...
14/10/2025

የሶማሊላንድ አዲሱ ተመራጭ ፕሬዚዳንት ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ እየመጡ ነው።

ፕሬዝዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ ግብዣ የቀረበላቸው በጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ (ዶ/ር) መሆኑ ታውቋል።

ከሰሞኑ የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐመድ አዲስ አበባ እንደነበሩ ይታወሳል።
https://t.me/Ayunews_2
https://t.me/Ayunews_2
‎‌‎

ኢትዮጵያ የኒክሌየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር ዛሬ ሾመችየኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዛሬ (ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ/ም) ጀምሮ አቶ ሳንዶካን ደበበን የኢትዮጵያ  #ኒው...
14/10/2025

ኢትዮጵያ የኒክሌየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር ዛሬ ሾመች

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዛሬ (ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ/ም) ጀምሮ አቶ ሳንዶካን ደበበን የኢትዮጵያ #ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር አድርገው መሾመዋል።

‎‌‎https://t.me/Ayunews_2
https://t.me/Ayunews_2

Address

04
Debre Birhan

Telephone

+251963464262

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zedo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Zedo:

Share