17/10/2025
ማህበረ ቅዱሳን ይለያል!!!
********************
#በ44ኛው የሰበካ አጠቃላይ ጉባኤ የማኅበረ ቅዱሳን ሪፖርት‼️
👉ማኅበረ ቅዱሳን በዩኒቨርሲቲና በኮሌጆች በሚሰጠው አገልግሎት ከ200ሺ በላይ የግቢ ጉበኤ ተማሪዎችን በሀገር ዉስጥና በውጭ ሀገራት በተለያዩ ቋንቋዎች እያተማረ እንደሚገኝ አስታውቋል።
👉ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 27,524 ተማሪዎች ደግሞ ባላቸው ሙያ ቤተ ክርስቲያንን እንዲያገለግሉ መሰማራታቸው ተገልጿል።
👉ሪፖርቱ 8,418 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎችን የአብነት ትምህርት በማስተማር 146ቱ ሥልጣነ ክህነት አንዲቀበሉ ማድረጉንም ጠቅሷል።
👉ማኅበሩ በሚሰጠው የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ከ41ሺ በላይ አዳዲስ አማኒያንን ማስጠመቁ የተገለጸ ሲሆን በካህናት እጥረት የተዘጉ 34 አብያተ ክርስቲያናት ካህናት በመቅጠር አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረጉን ተገልጿል።
👉በስበከተ ወንጌልና በሐዋርያዊ አገልግሎት 58,673,518,00 ብር ወጪ በማድረግ 31 መጽሐፍትን በ94,544 ቅጅ በተለያዩ ቋንቋዎች አሳትሞ አሰራጭቷል።
👉በ173 የአብነት ትምህርተ ቤት ለሚገኙ ትምህርተ ቤቶች 239 መምህራንና ለ2,220 ደቀ መዛሙርት 10,713,090,00 ብር ወጪ በማድረግ ወርኃዊ ድጎማ አድርጎዋል።
👉ስለማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎት በ44ተኛ የሰባካ አጠቃላይ ጉባኤ ላይ በቀረበው ሪፖርት በአባ ጊዎርጊስ ዘ ጋስጫ በሚሰጠው ነጻ የትምህር እድል 37 ተማሪዎችን በማስተማር 427,945,00 ብር ወጪ በማድረግ ድጎማ ያደረገ ሲሆን በሀገራችን በተከሰተ ወቅታዊ ችግር ምክንያት በትግራይና በሌሎች አካባቢ ለሚገኙ ገዳማትና የአብነት ትምህርት ቤቶች 6,834,100,00 ድጋፍ ተደርጓል ተብሏል።
👉በአብነት ትምህርት ቤት ግንባታ በምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት 8,870,407 ብር፣ በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት 23,021,025 ብር፣ በምዕራብ ኢትዮጵያ ቡኖ በደሌ ሀገረ ስበከት 16,671,804, ,53 ብር ወጪ በማድረግ የአብት ትምህርት ቤቶችና የገዳማት ገቢ ማስገኛ ሕንጻዎችን ማስገንባቱ በ44ተኛው የሰባካ ሆባኤ ላይ በቀረበው ሪፖርት ተገልጿል።