15/06/2026
እንኳን ደህና መጡልን......
ረውዷና የሁጃጆች መስተንግዶ በደማቅ አሻራ የተመዘገበ ልፋትና በስኬት የተቋጨ አማና!
بسم الله الرحمن الرحيم
የዘንድሮው የሐጅ ጉዞ የብዙዎችን ልብ በደስታና በእርካታ የሞላ ታላቅ ስኬት ሆኖ ተጠናቋል። ለዚህ ደግሞ ሌት ተቀን የደከሙ፣ አማናን በተግባር ያሳዩ መሪዎች ሚና የላቀ ነበር።
ከእነዚህ የላቁ መሪዎች መካከል የሃጅ ቡሽራ የነሸይኽ ገትዮች የልጅ ልጅ የሆኑት፣ የሃርቡው እንቁ፣ የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የዳዕዋ፣ ትምህርት፣ ማህበራዊ፣ ፈታዋና ብቃት ማረጋገጫ ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት ተወዳጁሸይኽ አወል አብደላህ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ናቸው። በእሳቸው የተመራውና የተስተባበረው ስራ ታሪክ የማይረሳው ትልቅ ስኬትን አስመዝግቧል!
የረውዷ ጉብኝት ስነ-ስርዓትን በማስተባበር በኩል
ገና ከሐጁ ስነ-ስርዓት አስቀድሞ፣ እያንዳንዱ ሙስሊም በጉጉት በሚጠብቀው የረውዷ ጉብኝት ላይ የታየው ዝግጅት እጅግ አስደናቂ ነበር። ሸኽ አወል አብደላህ መዲናንና ሐረምን ብሎም ከመዲና በፊት የእስልምና ታሪክ ያላትን ሃበሻን በሚመጥን መልኩ፣ ታይቶ በማይታወቅ ስነስርዓት የኢትዮጵያውያንን ሁጃጆች በክብርና በደስታ ከውዱ ነቢያችን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ጋር አገናኝተዋል።
የሁጃጆቻችን ፊት ላይ የነበረው የእርካታ ፈገግታ የእሳቸውና የቡድናቸው ልፋት ውጤት የሚያሳይ ነበር።
መልፋትና መትጋት ወትሮውንም መለያቸው የሆኑት እኚህ ታላቅ ሸኽ፣ የረውዷን ኃላፊነት ስላጠናቀቁ ብቻ እጃቸውን አላጣጠፉም። ይልቁኑ መስተንግዶና እገዛ በአስፈለገበት ቦታ ሁሉ እጃቸው ቀዳሚ ነበር።
• ሚና ኢስቲቅባሉ ላይ የተሰራው ልፋት ፣ የአረፋ ተራራም በተመሳሳይ እንቅልፍ የታጣባት በልፋት ላብ የተደከመበት ፍሬ የመጣበት ሁነት ሆኖ አልፏል ... ያ አስቸጋሪ በረሃ አፍ አውጥቶ ቢናገር ኖሮ፣ ለሁጃጆች የዋሉትን ውለታና ያሳዩትን ተቆርቋሪነት በምስክርነት በነገረን ነበር!
እንደ ውዷ ሃገራችን ኢትዮጲያ የዘንድሮው የ1447ኛው የሐጅ ስኬት የላቀና ጉልህ ድርሻ ለእሳቸውና ለቡድናቸው የሚሰጥ ነው የተገኘውም ሽልማት ለሃጅና ዑምራ ዘርፉ የሚገባ ነው።
ሁጃጆች ሽኝት ላይ የካርጎና መሰል ስራዎችን በተመለከተ አዳዲስ ለውጦች ታይተዋል የሃጅን የመስተንግዶ ችግር ለመቅረፍና ለማዘመን ብቻ ሳይሆን ለኺድማ የተመደቡት ሰዎች ሸይኽ አወልን ጨምሮ ለአላህ ብለው በየቂን የለፉት ልፋት ለዛሬው የሃጅና ዑምራ ሽልማት ትልቁን ድርሻ ይይዛል።
አማናን እንደ ክብር መቁጠር!
ለሸኽ አወል አብደላህም ሆነ አሁን ላለው ለአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አመራሮች ስራ ማለት 'አማና' (አደራ) ነው። አደራን በታማኝነት መወጣትና ለህዝብ መልፋትን እንደ ትልቅ ክብርና ጸጋ ነው የሚቆጥሩት።
አላህ ኸይር ስራቸውን ይቀበላቸው! ለዲናቸውና ለህዝባቸው ያበረከቱትን መልካም አሻራ በዱንያም በአኺራም የደስታ ምንጭ ያድርግላቸው። 🤲
8/10/28
Dhuʻl-Hijjah 29, 1447 AH
Amhara Region Islamic Affairs Higher Council/የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council