21/10/2025
#አቡነ ሐራ ድንግል
ወር በገባ በ11 የአባታችን የአቡነ ሐራን ድንግል ወርሐዊ መታሰቢያቸው ነው፡፡አባታችን አቡነ ሐራ ድንግል ያደረጉት ተአምር ይህ ነው፡፡ ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ከሕዝበ ክርስቲያን ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
#አምስት መነኮሳያት ከአባታች ሐራ ድንግል ገዳም ወደ ዳውንት ወደ ሚባል ሀገር ሄዱ አነርሱም ለምግባቸውና ለልብሳቸው የሚሆናቸውን ገንዘብ ከሀገሩ ሰዎች ይለምኑ ዘንድ ወደ ዳውንት ደረሱ፡፡
☞ወደዚያም በደረሱ ጊዜ በድንገተኛ በሽታ የታመመ አንድ ሰውና በከብት በሽታ የታመመ አንድ በሬ አገኙ የሀገሩ ሰዎችም እነዚያን መነኮሳያት በሀገራችን ሁለት በሽተኞች አሉ አንዱ ሰው ነው አንዱም በሬ ነው ለእነዚህ መድኃኒት የሚሆናቸው ምንድነው አሏቸው፡፡
☞መነኮሳያቱም ለጠየቋቸው ሰዎች የአባታችን ሐራ ድንግል ከሚሉት ከጻድቁ አባታችን መቃብር ያመጣነው አፈር አለ ሁለቱንም እንቀባቸዋለን አሏቸው፡፡
☞የሀገሩ ሰዎችም እናንተ እንዳችሁ ይሁን አሏቸው ወዲያውም ሰውየውንም በሬውንም ቀቧቸው ሁለቱም በአባታችን ሐራ ድንግል የረድኤት ኃይል ከደዌያቸው ተፈወሱ፡፡
☞የጻድቁ አባታችን የአቡነ ሐራ ድንግል የጸሎታቸው በረከቱ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኑ ጋር ይሁን፡፡
☞(ገድለ አቡነ ሐራ ድንግል )