ድምጸ ተዋሕዶ ሚዲያ Voice of Tewahedo Media

ድምጸ ተዋሕዶ ሚዲያ Voice of Tewahedo Media ይህ የድምጸ ተዋህዶ Page ነው።
ትምህርቶችን እንዲሁም ሊሎች ዝግጅቶችን 'Like' በማለት ይከታተሉ።

 #ብፁዕ አቡነ አብርሃም የትንሣኤ በዓልን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ✝️✝️✝️✝️​( #ሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም፤  #ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሚዲያ)✝️​የባሕር...
11/04/2026

#ብፁዕ አቡነ አብርሃም የትንሣኤ በዓልን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ
✝️✝️✝️✝️
​( #ሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም፤ #ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሚዲያ)

✝️​የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም፣ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሣኤ በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ።
✝️ብፁዕነታቸው “እንደተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ” (ማቴ 28፡6) የሚለውን የቅዱስ ወንጌል ቃል መነሻ አድርገው ባስተላለፉት መልእክት፤ በዓሉ ሞት በክርስቶስ ሞት ድል የተደረገበትና በጌታ ትንሣኤም የሰው ልጆች ሁሉ ትንሣኤ የታወጀበት ታላቅ ዕለት መሆኑን በዝርዝር አስረድተዋል።
✝️​ብፁዕነታቸው አያይዘውም ምዕመናን በዓሉን ሲያከብሩ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና ሕግ መሠረት ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም ደካሞችንና ችግረኞችን በማሰብ፣ ያላቸው ለሌላቸው በማካፈልና የተቸገሩትን በመርዳት በዓሉን በደስታ፣ በፍቅርና በመረዳዳት እንዲያከብሩ አጽንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።
@የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል

3ቀን ቀረው፩ ኛው ክብረ ተዋህዶ የኪነ ጥበብ መርሐ ግብር ነሐሴ 25 በሙሉ ዓለም የባህል ማዕከል   #ኦርቶዶክሳዊ አለባበስ በመልበስ ይገኙትኬቱን- በሰ/ት/ቤቱ ንዋዬ ቅድሳት መሸጫ- በታዬ ...
28/08/2025

3ቀን ቀረው
፩ ኛው ክብረ ተዋህዶ የኪነ ጥበብ መርሐ ግብር
ነሐሴ 25 በሙሉ ዓለም የባህል ማዕከል
#ኦርቶዶክሳዊ አለባበስ በመልበስ ይገኙ

ትኬቱን
- በሰ/ት/ቤቱ ንዋዬ ቅድሳት መሸጫ
- በታዬ ሞላ ስቴሽነሪ
- በየአካባቢያችን መንፈሳዊ አገልግሎት በቅንነት
በሚደግፉ የከታማችን ወጣቶች እጅ ያገኙታል።

02/08/2025
31/07/2025

ለ1ኛ ደረጃ ርዕሰ መምህር ፈተና የተመረጣችሁ ቅዳሜ በ26-11-2017 ዓም ከጥዋቱ 4:00 በመገኘት ፈተናችሁን እንድትወስዱ እናሳውቃለን።

ቱሪዝምና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  ቤተክርስቲያን ጥቅም በሚል ርእስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቱሪዝም ሚንስቴር  እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅርሳቅርስ መምሪያ ውይይት አደረጉ...
30/07/2025

ቱሪዝምና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጥቅም በሚል ርእስ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቱሪዝም ሚንስቴር እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅርሳቅርስ መምሪያ ውይይት አደረጉ።

ሐምሌ ፳፫/፳፻፲፯ ዓ/ም ድምጸ ተዋህዶ ሚዲያ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅርሳቅርስ ፣የቤተመጻሕፍት ፣ወመዘክር ሙዚየም እና የቱሪዝም መምሪያ ዋና ኃላፊ ክቡር በኩረ ትጉሃን ምትኩ ከንቲባ እና በመምሪያው ሥር የቱሪዝም ዋና ክፍል ኃላፊት ክብርት ወ/ሮ ምንታምር ባየው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በቱሪዝም ዘርፍ ልማት ላይ ያላትን ከፍተኛ ሚና እና በተጠቃሚነቱ ረገድ ያላትን ሁኔታ መሠረት በማድረግ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቱሪዝም ሚንስቴር ሚንስትር ከክብርት ወ/ሮ ሰላም ካሳ (አፀደ ማርያም) ሰፊ ውይይት አደረጉ።

በውይይቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ ጥንታውያን አድባራትና ገዳማት በኪነ-ሕንፃቸው ፣ ድንቅ የሆኑ የግድግዳና የጣሪያ ላይ ሥዕላቶቻቸው፣ እድሜ ጠገብ የብራና መጻሕፍት ስብስቦቻቸው።፣ የቀደምት ነገሥታት እና የቤተክርስቲያን መሪዎች አልባሳቶቻቸው እና መገልገያ ቁሳቁሶቻቸው እንዲሁም የዝማሬ መሣሪያዎቻቸው ሁሉ የቱሪስት መስህቦቿ መሆኑ የሚታወቅ ነው።


እነዚህ የቱሪስት መስኅቦችን ለመመልከት የሚመጡ ብዙ የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ገንዘባቸው በሀገራችን የሚገኙ ሆቴሎችን እና መሰል ጉዳዮች ከማበልፀግ ከማድመቅ ባሻገር የመስኅቦቹን ባለቤት ቤተክርስቲያንን የበይ ተመልካች ያደረጉ ጉዳዮች ከሆኑ ዋል አደር ማለቱ በውይይቱ አጽንኦት ተሰጥቶታል።

የተከበረው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እስከአሁን የነበረው እንዳለ ሆኖ በቀጣይ ለሚደረጉ የቱሪዝም ልማት እንቅስቃሴ ከተሳታፊነት እስከ ተጠቃሚነት ቤተክርስቲያንን ያማከለ ሥራ እንዲሠራ እና የልምድ ልውውጦችን እንዲሁም ስልጠናዎች ላይም የጋራ ተሳትፎ እንዲያደርግ በውይይቱ ተጠይቋል።
ክብርት ሚንስትሯም የቤተክርስቲያኒቱን ጥያቄ በበጎ ጎኑ በመቀበል ጥያቄው ወቅቱን የጠበቀና ሚንስቴር መሥሪያ ቤቱ ከሃይማኖት ተቋማት ጋር ሊሠራው ያቀደውን ሥራ በሚያረቅበት ጊዜ በመሆኑ በጋራ ለመሥራት የማይቸገሩ መሆኑን ገልፀዋል።

በተለይም የቱሪዝም መስኅቦችን ማራኪ ለማድረግና በቱሪዝም ዘርፍ ያሉ እንቅስቃሴዎችን ለማሳደግ ቁረጠኞች መሆናቸውን ገልፀው ለዚህም እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተከርስቲያን በባለቤትነት ለመሥራት የሚመጡ አጋር አካላት ለሥራው መቃናት ሚናቸው ትልቅ መሆኑን አውስተዋል።
በመሆኑም በበጀት ዓመቱ ዘርፉን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ላይ ቤተክርስቲያን የሥራው አካል እንድትሆን እንሠራለን ብለዋል።

በመጨረሻም ቤተክርስቲያን ከቱሪዝም ሚንስቴር ጋር ለመሥራት የሚያስችላትን ይሁንታ ለማግኘት በደብዳቤ ስትጠይቅ ቤተክርስቲያኗን የሚመጥን አቀባበል ስለተደረገልን ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ኦረቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅርሳቅርስ መምሪያ ዋና ኀላፊ መናገራቸውን
የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅርሳቅርስ መምሪያ ገልጿል።

©የኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በቅርብ ቀን በፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል ሰንበት ትምህርት ቤት
29/07/2025

በቅርብ ቀን በፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል ሰንበት ትምህርት ቤት

ሦስተኛው የአህጉረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር ተከናወነ። (ድምጸ ተዋህዶ ሚዲያ) ሐምሌ 21 / 11 / 2017 ዓ.ምሦስተኛው የአህጉረ ስብከቶች...
28/07/2025

ሦስተኛው የአህጉረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር ተከናወነ።

(ድምጸ ተዋህዶ ሚዲያ) ሐምሌ 21 / 11 / 2017 ዓ.ም

ሦስተኛው የአህጉረ ስብከቶች የሰ/ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ተከናውኗል። በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅና የሸገር ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የምስካየ ኅዙናን ገዳም የበላይ ጠባቂ እና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤጲፋኒዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ ፣ ዲ.ን ስንታየሁ ምስጋናው የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሓላፊዎች ፣ መምህራነ ወንጌል ፣ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሥራ አመራር አባላት ተገኝተዋል።

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ባስተላለፉት መልእክት "ጌታችን በመዋዕለ ሥጋዌው ለ3 ዓመት ከ3 ወር ሐዋርያትን ከተለያየ ግብርና ክፍል መርጦ ካስተማራቸው በኋላ ሂዱና አስተምሩ በሀገር ሁሉ ቋንቋ አስተምሩ ብሎ እንዳዘዛቸውና አልጫ የሆነውን ዓለም በማስተማር እንዳጣፈጡ ሁሉ እናንተም በተማራችሁት ትምህርት ሄዳችሁ እንድታስተምሩ ፣ እንድታሰለጥኑ ፣ ፍሬ እንድታፈሩ" በማለት አባታዊ ምክርና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል።

ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም እንዲሁ "ከእግዚአብሔር የተላከ ከእግዚአብሔር የተመረጠ የአምላኩ የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል" በሚል ኃይለ ቃል ተነስተው እርሱን ለማገልገል የሚጠራ ማንኛውም አገልጋይ የእግዚአብሔርን ዓላማ ፣ ሐሳብ የእርሱን ዕቅድና እርሱ ለሰው ያለውን አምላካዊ ጥበብ ፣ መግቦት በፍጥረቱም ላይ እንዴት እንደሚሠራና ጥልቅ የሆነውን ፍቅሩን ሁሉ ይናገራል። ብለው ወደ መጣችሁበት ስንቃችሁን ያዛችሁ በመሄድ በሚገባ አገልግሎታችሁን እንድትፈጽሙ ይሁን በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈው ቋጭተዋል።

በዕለቱ ሌላኛውን አባታዊ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም እንዲሁ "በአባቶች ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ" የሚለውን የልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ቃል መነሻ አድርገው እናንተም በአባቶቻችሁ ፈንታ የተተካችሁ እንደመሆናችሁ አባቶቻችሁን መስላችሁ ቤተ ክርስቲያንን ልታገለግሉ ይገባል በማለት ለተመራቂ መምህራን የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ "መጻሕፍት እግዚአብሔርን ወደ ማድነቅ ልብህን ይመሩታልና" በሚል ኃይለ ቃል በመነሣት የማደራጃ መምሪያውን መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ዲያቆን ስንታየሁ ምስጋናው በሥልጠናው ጊዜ አጠቃላይ የተከወኑ ተግባራትና በቀጣይ እንዲሠሩ የሚፈለጉ ጉዳዮች ላይ ገለጻ አድርገዋል። ሠልጣኝ መምህራኑም የነበራቸውን የ15 ቀን ቆይታ የተመለከተ ዘገባ እና አቋማቸውንም እንዲሁ በተወካያቸው በኩል አቅርበው ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እጅ የዕውቅና የምስክር ወረቀታቸውን ተቀብለው የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።

ሥልጠናው ከሐምሌ 7 እስከ ሐምሌ 20 ቀን ድረስ በተከታታይ ለ15 ቀናት የተሰጠ ሲሆን በሥልጠናውም ላይ ከ30 አህጉረ ስብከት የተወጣጡ 209 መምህራን ተከታትለው አጠናቅቀዋል። ከነዚህም መካከል 106 ቀሳውስትና ዲያቆናት እንዲሁም 8 ሴቶች ይገኙበታል።

(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)

በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራ ልዑክ የቅዱስ ገብርኤል በዓልን ለማክበር ወደ ቁልቢ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተጓዘ።********************ሐምሌ ፲፯ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ...
24/07/2025

በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራ ልዑክ የቅዱስ ገብርኤል በዓልን ለማክበር ወደ ቁልቢ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተጓዘ።
********************
ሐምሌ ፲፯ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም
"""""""""""""""""""""""""""""""""""""

በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲ
ያን ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣የደቡብ ምዕራብ
ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሚመራ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልዑክ ዓመታዊውን የቅዱስ ገብርኤል በዓልን ለማክበር ዛሬ ማለዳ ወደ ድሬዳዋ ተጉዟል።

በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራው ልዑክ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስን፣ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅን ፣ብፁዕ አቡነ ቶማስን፣ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕን፣ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስን፣ክቡር ንቡረዕድ ኤልያስ አብርሃን፣ሊቀ ሊቃውንት ኃይለሥላሴ ዘማርያምን፣መልዐከ ሕይወት አባ ወልደኢየሱስ ሰይፉንና ሊቀ ስዩማን እስክንድር ገብረ ክርስቶስን ያካተተ ሲሆን በዛሬው ዕለት በቁልቢ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በመገኘት የበዓሉን የቅድመ ዝግጅት ሥራን የሚመለከት ከመሆኑም በላይ በገዳሙ የሚከናወኑ የልማት ስራዎች አፈጻጸምንና በቀጣይ በሚከናወኑ ሥራዎች ዙሪያ መመሪያን የሚሰጥ ይሆናል።

በተጨማሪም በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት የሥራ ጉብኝት የሚያደርገው ልዑኩ በሀገረ ስብከቱ የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውሮ ይመለከታል ተብሎ ይጠበቃል። ልዑኩ በድሬዳዋ ሆኅተ ሰማይ ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሁለ ገብ የልማት ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ይመረቃል።

በነገው ዕለት በድሬዳ መልካ ጀብዱ ጌቴሴማኒ ገዳም በመገኘት በገዳሙ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማትና የሰብዐዊ አገልግሎት ሥራዎችን የሚመለከተው ልዑኩ በዚያ ለሚገኙ እጓለመውታ ሕጻናት ትምህርተ ወንጌል፣ቃለ ቡራኬና ቃለ ምዕዳን በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የሚሰጥ ይሆናል።

የልዑኩን የድሬዳዋ ሀገረ ስብከትና የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳምን ቆይታ ዝርዝር መርሐ ግብሮችን በተመለከተ ተከታታይ መረጃዎችን የምናደርስ ይሆናል።

ከተመሰረተ አጭር ጊዜ ያስቆጠረው አቡነ ቴዎፍሎስ አካዳሚ በተሻለ የትምህርት ጥራት የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን በመገንባት ላይ ነው ።በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን በሁለቱም ግ...
23/07/2025

ከተመሰረተ አጭር ጊዜ ያስቆጠረው አቡነ ቴዎፍሎስ አካዳሚ በተሻለ የትምህርት ጥራት የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን በመገንባት ላይ ነው ።

በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን በሁለቱም ግቢዎች በመቀበል ላይ ይገኛል።

ቁጥር አንድ ቀበሌ 14 አውስኮድ ፊት ለፊት
ቁጥር ሁለት ልደታ ቤተክርስቲያን ጀርባ

ይፍጠኑ ይመዝገቡ ያስመዝግቡ አቡነ ቴዎፍሎስ አካዳሚ

Address

Bahir Dar
Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ድምጸ ተዋሕዶ ሚዲያ Voice of Tewahedo Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share