11/04/2026
#ብፁዕ አቡነ አብርሃም የትንሣኤ በዓልን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ
✝️✝️✝️✝️
( #ሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም፤ #ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሚዲያ)
✝️የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም፣ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሣኤ በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ።
✝️ብፁዕነታቸው “እንደተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ” (ማቴ 28፡6) የሚለውን የቅዱስ ወንጌል ቃል መነሻ አድርገው ባስተላለፉት መልእክት፤ በዓሉ ሞት በክርስቶስ ሞት ድል የተደረገበትና በጌታ ትንሣኤም የሰው ልጆች ሁሉ ትንሣኤ የታወጀበት ታላቅ ዕለት መሆኑን በዝርዝር አስረድተዋል።
✝️ብፁዕነታቸው አያይዘውም ምዕመናን በዓሉን ሲያከብሩ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና ሕግ መሠረት ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም ደካሞችንና ችግረኞችን በማሰብ፣ ያላቸው ለሌላቸው በማካፈልና የተቸገሩትን በመርዳት በዓሉን በደስታ፣ በፍቅርና በመረዳዳት እንዲያከብሩ አጽንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።
@የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል