EECMY SCES Children-Ministry-Hawassa

EECMY SCES Children-Ministry-Hawassa የዚህ ገፅ ዓላማ ሁለንተናዊ ዕድገት ያለውን ትውልድ ማፍራት ላይ ያለመና ለዚህ ግብዐት የሚሆኑ ጠቃሚ መልዕክቶችን ማካፈል ታሳቢ ያደረገ ነው።

" ወዳጄ ኢየሱስ" በሚል ርዕስ ከ9-11 ዓመት ላሉ ልጆች የተዘጋጀ የክረምት መንፈሳዊ ስልጠና ።ትውልድ ለክርስቶስ
16/07/2025

" ወዳጄ ኢየሱስ" በሚል ርዕስ ከ9-11 ዓመት ላሉ ልጆች የተዘጋጀ የክረምት መንፈሳዊ ስልጠና ።ትውልድ ለክርስቶስ

Empowering Generation For Christየታዳጊ ወጣቶች ስልጠና ከጥር 26-30  ለተከታታይ አምስት ቀናት (5) ከ13-17 ዓመት ላሉት የተዘጋጀ ። ትውልድን ለክርስቶስ ማዘጋጀት፣...
27/01/2025

Empowering Generation For Christ
የታዳጊ ወጣቶች ስልጠና ከጥር 26-30 ለተከታታይ አምስት ቀናት (5) ከ13-17 ዓመት ላሉት የተዘጋጀ ። ትውልድን ለክርስቶስ ማዘጋጀት፣ማብቃት፣ማስታጠቅ የሁላችንም ሀላፊነት ነው።

የአከባቢ ባለ አደራነት በዚህ አገልግሎት የተሳተፍች ሁሉ ተባረኩ።
26/03/2024

የአከባቢ ባለ አደራነት በዚህ አገልግሎት የተሳተፍች ሁሉ ተባረኩ።

በታህሳስ 20/2016 ቅዳሜ ዕለት በጩኮ ከተማ  የኢ/ወ/ቤ/መ/ኢ ከሆማቾ ፣   ከጩኮ  ሰበካዎች እና ከጩኮ ከተማ ማ /ምዕመናን ከመጡ የልጆች አገልግሎት መምህራን ጋር ጥሩ  የስልጠና ጊዜ ...
30/12/2023

በታህሳስ 20/2016 ቅዳሜ ዕለት በጩኮ ከተማ የኢ/ወ/ቤ/መ/ኢ ከሆማቾ ፣ ከጩኮ ሰበካዎች እና ከጩኮ ከተማ ማ /ምዕመናን ከመጡ የልጆች አገልግሎት መምህራን ጋር ጥሩ የስልጠና ጊዜ አሳልፈናል።እግዚአብሔር ይመስገን።

የኢ/ወ/ቤ/መ/ኢ ማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጲያ ሲኖዶስ የህፃናትና የልጆች አገልግሎት መምሪያ በታህሳስ 13/4/2016 ዓ.ም ቅዳሜ ዕለት በስምጥ ሸለቆ አርሲ ነጌሌ ሰበካ እና በሻሸመኔ ከተማ እና...
24/12/2023

የኢ/ወ/ቤ/መ/ኢ ማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጲያ ሲኖዶስ የህፃናትና የልጆች አገልግሎት መምሪያ በታህሳስ 13/4/2016 ዓ.ም ቅዳሜ ዕለት በስምጥ ሸለቆ አርሲ ነጌሌ ሰበካ እና በሻሸመኔ ከተማ እና ዙሪያዋ ሰበካ ስልጠና ተሰጥቷል። በዕለቱም የማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጲያ ሲኖዶስ ፕረዝደንት ቄስ ኢያሱ ጠግቾ የሉቃስ ወንጌል 2:52 እና ዕብ 11:23 መነሻ በማድረግ የልጆች አገልግሎት መምህራን ይበልጥ ዘመኑን አውቀን እንድንነቃ እና ልጆች ደግሞ እግዚአብሔርን እንዲያውቁ ፣በሞገስና በጥበብ፣ እግዚአብሔርን በመፍራት እንዲያድጉ፣ የአለምን ክብርና ዝና እንቢ እንዲሉ የልጆችን አቅም ማጎልበት ይጠበቅብናል በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ፕሮግራሙንም በፀሎት ከፍተዋል ። በመቀጠልም የልጆች አገልግሎት አያያዝ፣ የቤተሰብ ክፍተት በልጆች አስተዳደግ ላይ፣ የቤተክርስቲያን ክፍተት በትውልድ ላይ እና መፍትሄዎቻቸው እንዲሁም ልጆችን የማስተማር ዘዴዎችም በቀኑ ስልጠና ውስጥ ተካቷል።
እግዚአብሔር በነገር ሁሉ መከናወንን ስለሰጠን ስሙ ይባረክ።

የኢ/ወ/ቤ/ክ/መ/ኢ ማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ  ሲኖዶስ የህፃናትና የልጆች አገልግሎት መምሪያ።ከሰበካ/ ማ/ም ከልጆች አገልግሎት እና የሙሉ ጊዜ አገልጋዮች ጋር የተደረገ  የፀሎትና የምክክር ...
26/11/2023

የኢ/ወ/ቤ/ክ/መ/ኢ ማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ የህፃናትና የልጆች አገልግሎት መምሪያ።

ከሰበካ/ ማ/ም ከልጆች አገልግሎት እና የሙሉ ጊዜ አገልጋዮች ጋር የተደረገ የፀሎትና የምክክር ጊዜ ።

በህዳር 15-3-2016 ዓ.ም በማዕከላዊ ደቡብ ኢ/ያ ሲኖዶስ ከልጆች አገልግሎት አስተባባሪዎች እና ከሙሉጊዜ አገልጋዮች ጋር ድንቅ የፀሎትና የምክክር ጊዜ ተደርጎአል።
[ ] በዕለቱም የማዕከላዊ ደቡብ ኢ/ያ ሲኖዶስ ፕረዝደንት ቄስ ኢያሱ ጠግቾ ለአገልጋዮች የእንኳን ደህና መጣችሁ ሰላምታ በማቅረብ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።በማከልም ገላ 4:17-19 በማንበብ የሚከተለውን መልዕክት አስተላልፈዋል፦

[ ] ልጆችን ማብቃት፣ለእግዚአብሔር ገንዘብ ማድረግ፣ከልጅነታቸው ከጌታ ጋር ማጣበቅ፣ ወንጌልን በልጆች ማስቀጠል፣በሁሉ አቅጣጫ ተፅኖ ፈጣሪዎች እንዲሆኑ መርዳት፣ ዘመን ተሻጋሪ ትውልድ መፍጠር፣ ጌታን በውስጣቸው መሳል የቤተሰብና የቤተክርስቲያን ድርሻ በመሆኑ ወላጆችና የልጆች አገልጋዮች ትልቅ ትኩረት በመስጠት አገልግሎቱን በይበልጥ ማጠናከር እንዳለብን አሳስበዋል።
በመቀጠልም የአ.አበባ ቦሌ መካነ ኢየሱስ ቄስ የሆኑት ቄስ ዳዊት ዮሐንስ ቦታው ላይ በመገኘት
2ጢሞ 1:1-7 መሰረት በማድረግ የእግዚአብሔርን ቃል ያካፈሉ ሲሆን በመጨረሻም ከየሰበካው/ ማ/ም ከመጡት አገልጋዮች ጋር አገልግሎቱ ን በቀጣይ ለማጠናከር እንዲቻል ከሲኖዶሱ የህፃናትና የልጆች አገልግሎት መምሪያ ጋር ለመስራት አቅጣጫ ተቀምጧል።

26/11/2023

Address

Sidama
Awassa
0000

Telephone

+251976141546

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EECMY SCES Children-Ministry-Hawassa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to EECMY SCES Children-Ministry-Hawassa:

Share