15/06/2022
የእሁድ አምልኮ ፕሮግራም
አቅራቢ ፦ ፓስተር ሀብታሙ ለገሰ ( ፒና )
ቀን ፦ 05 - 10 - 2014
ርዕስ፦ ሰዋልኝ።
የቃል ክፍል፦ ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 22
እግዚአብሔር አብርሃምን አንድ ጊዜ ተናገረዉ እርሱም ሰምቶ ታዘዘ ፤ ከአባት ቤት ዉጣ ካለዉ ጊዜ አንስቶ እስከ ህይወት ፍፃሜዉ አብርሃም አምላኩን እግዚአብሔርን ልጁን ለመሰዋት እስከመፍቀድ ታዟል።
በዚህ የቃል ክፍል የሚከተሉትን መልካም የህይወት መርሆዎች ከእምነት አባታችን ከአብርሃም እንማራለን።
1ኛ፦ አብርሃም የተዘጋጀ ማንነት ነበረዉ
(ኦሪት ዘፍጥረት 22:1)
" ከእነዚህም ነገሮች በኋላ እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው፥ እንዲህም አለው። አብርሃም ሆይ። አብርሃምም። እነሆ፥ አለሁ አለ።"
አብርሃም እነሆ አለሁ ሲል አምላኩ እግዚአብሔርን ለምትለኝ ነገር ለመታዘዝ ዝግጁ ነኝ ማለቱ ነዉ።
ለእግዚአብሔር ቤት መሪዎች እና ለእግዚአብሔር ቃል መታዘዝ በህይወታችን የስኬት መሰረት ነዉ ፤ ስለዚህ መንፈስ ቅዱስን ከእኛ ምን እንደሚፈልግ ልንጠይቀው ይገባል።
2ኛ፦ አብርሃም የእምነት ህይወት ያለዉ ሰዉ ነበር።
(ኦሪት ዘፍጥረት 22:5)
" አብርሃምም ሎሌዎቹን አላቸው። አህያውን ይዛችሁ ከዚህ ቆዩ፤ እኔና ልጄ ወደዚያ ሄደን እንሰግዳለን፥ ወደ እናንተም እንመለሳለን።"
(ኦሪት ዘፍጥረት 22:8)
" አብርሃምም። ልጄ ሆይ፥ የመሥዋዕቱን በግ እግዚአብሔር ያዘጋጃል አለው፤ ሁለቱም አብረው ሄዱ። "
አብርሃም ምንም እንኳን ልጁን ለመሰዋት እየሄደ ቢሆንም እግዚአብሔር ልጁን መልሶ እንደሚሰጠዉ ያምን ነበር።
3ኛ፦ አብርሃም እግዚአብሔርን ይፈራ ነበር
እግዚአብሔርን መፍራት ማለት ለእርሱ እዉቅና መስጠት ፤ በየትኛውም ስፍራ እና ሁኔታ እርሱን ሰምተን መታዘዝ ነዉ።
የእግዚአብሔር ቃል ስለ እየሱስ ሲናገር እግዚአብሔርን በመፍራቱ ፀሎቱ ተሰማለት ይላል።
እግዚአብሔርን የመፍራት ህይወት እንዲኖረን እራሳችንን ማለማመድ አለብን።
4ኛ፦ አብርሃም የመታዘዝ ህይወት ነበረዉ
(ኦሪት ዘፍጥረት 22:12)
" እርሱም። እነሆኝ አለ። እርሱም። በብላቴናው ላይ እጅህን አትዘርጋ፥ አንዳችም አታድርግበት፤ አንድ ልጅህን ለእኔ አልከለከልህምና እግዚአብሔርን የምትፈራ እንደ ሆንህ አሁን አውቄአለሁ አለ።"
በዚህ ክፍል " አንድ ልጅህን ለእኔ አልከለከልህምና " የሚለዉ አብርሃም ለአምላኩ ለእግዚአብሔር ቃል ልጁን እስከመስጠት እንደታዘዘ ያሳያል ፤ የአብርሃም የመታዘዝ ህይወት የሚጀምረዉ የአባቱን ቤት ትቶ እግዚአብሔር ወደ አሳየዉ ምድር በመሄድ ነዉ።
እግዚአብሔር በሚታዘዝ ማንነት ዉስጥ በረከቱን ይለቃል
" እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ፥ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ "
(ትንቢተ ኢሳይያስ 1:19)
የእግዚአብሔር መንግስት አንደኛ! መልካም ሳምንት
ለበለጠ መረጃ፦ 0916 - 82 23 55
0911 - 43 53 16