27/05/2026
የተዘጋጀ ሥልጠና ነህ 1:1-11
የእግዚአብሔር_ቤት_ቅናት_ያለው_ወጣት
✅ነህምያ በምርኮ ዘመን በምርኮ አገር የተወለደ አይሁዳዊ ነው። እግዚአብሔር በፋርስ መንግሥት ውስጥ ከፍተኛ ሥልጣን እንዲያገኝ አደረገው። ነህምያ የንጉሡ ጠጅ አሳላፊ ነበር። ይህ ከፍተኛ የሥልጣን ስፍራ ባይመስልም፥ ጠጅ አሳላፊነት በጥንት ዘመን የንጉሡ ወዳጅ ለሆነና በከፍተኛ ደረጃ ታማኝነት ላለው ሰው የሚሰጥ ሥራ ነበር። ጠጅ አሳላፊ ታማኝ መሆን የነበረበት ሰዎች ንጉሡን የመግደል ሙከራ የሚያደርጉበት አንዱ መንገድ በሚበላው ወይም በሚጠጣው ነገር ላይ መርዝ በመጨመር ስለ ነበር ነው፤ ስለዚህ ይህ ማለት ነህምያ የፋርስ ንጉሥ የቅርብ አማካሪ ከሆኑት ሰዎች አንዱ ነበር ማለት ነው። ነህምያ በመንግሥት ዘንድ በጣም ጥሩ ሥራ ያለውና ጥሩ ኑሮን የሚኖር ቢሆንም፥ ወገኖቹንና ጨርሶ አይቷት የማያውቃትን ኢየሩሳሌምን አልረሳም። ነህምያ እግዚአብሔርን የሚወድ፥ ስለ እግዚአብሔር ክብርና ስለ ሕዝቡ በጣም የሚገደው ሰው ነበር። የኢየሩሳሌም ቅጥር ባለመሠራቱ የእግዚአብሔር ስም ተነቅፍ ስለ ነበረና ሕዝቡም ለጠላት ጥቃት ተጋልጠው ስለ ነበር ነህምያ ስለ ደኅንነታቸው ገደደውና የኢየሩሳሌምን ቅጥር በመሥራት እርሱን ይጠቀምበት ዘንድ እግዚአብሔርን ለመነ።
የእግዚአብሔር ቤት ቅናት
✅ቅናት ማለት ለአንድ አላማ ያለው ቁርጠኝነት፣ ዉሳኔ እና መሰጠት ማለት ነው ።
✅ በአላማ ፀንቶ መቆም ማለት ነው
✅ ለአላማ መጨከን ነው ።
✅ አንድ ነገርን ለማሳካት የሚደረግ ጥረት/ጉጉት ።
✔✔ ቅናት ያለባቸው ሰዎች በምድር ላይ መፍትሔውን ያመጣሉ።
✅ መነሳሳትን ያመጣል።
✅ ኃይልን ይሰጣል ።
✅ እምነትን ይሰጣል ።
✅ ከታሠረንበት ቦታ ጥሰን ለመሄድ ኃይልን ይሰጣል
ቅናት ለእግዚአብሔርና ለእግዚአብሔር ፍቅር በጉጉት ለመኖር ይጠቅመናል
“ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም ድረስ በፍርድና በጽድቅ ያጸናውና ይደግፈው ዘንድ በዳዊት ዙፋንና በመንግሥቱ ላይ አለቅነቱ ይበዛል፥ ለሰላሙም ፍፃሜ የለውም። የእግዚአብሔር ቅንዓት ይህን ያደርጋል።” ኢሳይያስ 9፥7
❤መንፈሳዊ ቅናት ራስህን ያስጥላል
❤መንፈሳዊ ቅናት #ምኞትን አያመጣም #ራዕይን ያመጣል
ለነህምያ #ሁለት ዓይነት ቅናት አለው
✔ ፦ማለት ሰዉ ነኝ ብሎ መነሳት፡- የኢየሩሳሌም ቅጥሮች የእግዚአብሔር ሕዝብ ያሉበት መንፈሳዊ ሁኔታ ምልክት ነበሩ። ቅጥሮቹ እስካልተሠሩ ድረስ እግዚአብሔር ስሙን ሊያኖርባትና ሊመለክባት ተስፋ ለሰጣት ለዚህች ከተማ በቂ ትኩረት እንደሌለ የሚያሳይ ነበር። እግዚአብሔር ሊመለክበት ባለው ስፍራ ስሙን ለማኖር ቃል ገብቶ ነበር። የእግዚአብሔር ከተማ የነበረችው የኢየሩሳሌም ውጫዊ ሁኔታ የእግዚአብሔርን ሕዝብ የልብ መንፈሳዊ አቋም የሚያንጸባርቅ ነበር። ሰውን እንደ ሰው መቆጠር ።
✔ ፦ ምንጩ ከመንፈስ ቅዱስ ነው።
✅መንፈሳዊ ቅናት ስለ እግዚአብሔር ቃልና ስለ ወንጌል ነው።
የነህምያ የመጀመሪያ አገልግሎት የኢየሩሳሌምን ቅጥር እንደገና መሥራት ነበር። ይህ ነገር በጣም አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው? ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነበሩ፡፡ የመጀመሪያው፥ በጥንት ዘመን ሕዝቦች ድንገት ከሚመጣ የጠላት ጦርና ከሚዘርፍ ወራሪ የሚከላከሉበት ዋናው መንገድ የከተማ መከለያ ቅጥር ነበር፤ ስለዚህ በኢየሩሳሌም ከተማ ዙሪያ ቅጥር እስከሌለ ድረስ የእግዚአብሔር ሕዝብ ሰላም ሊኖራቸውና የደኅንነት ዋስትና ሊያገኙ አይችሉም ነበር። ይልቁንም በማያቋርጥ ፍርሃት መኖር ዕጣ ፈንታቸው ነበር። ልክ ቅጥሩ እንደተሠራ ሕዝቡ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ላይ በማተኮር የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማትና ለመታዘዝ የነበራቸውን ፈቃደኝነት ማየት የሚያስገርም ነው።
✅በመንፈሳዊ ቅናት ያለው አገልጋይ ለእግዚአብሔርና ለራሱ ጠንካራና ትጉ ይሆናል።
?
✅ግብዝና የሌለበት እምነት ያለው ሰው ነው
✅ብርቱ አገልጋይ ነው
✅ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት ያጠናከረ ወጣት
✅የሚጸልይ አገልጋይ እና የዉሳኔ ሰው ናቸዉ።
✔እንደ ነህምያ የእግዚአብሔር ቤት ቅናት ያለው ወጣት ማወቅ ያለበት ነገሮች
1. አንዲት ቤተ ክርስቲያን ልትገነባና ጤነኛ ልትሆን ከተፈለገ ተገቢ የሆኑ መሪዎች ያስፈልጓታል። እነዚህ መሪዎች ከሁሉ በፊት ተገቢ መንፈሳዊ መመዘኛዎችን ማሟላት አለባቸው። እግዚአብሔርን መውደድ አለባቸው፤ ለእግዚአብሔር ሕግ ሊገዳቸው ያስፈልጋል፤ ኃጢአትን ሊጠሉና የጸሎት ሰዎች ሊሆኑም ይገባል።
2. መሪዎች እግዚአብሔር ለቤተ ክርስቲያን የሰጣትን ሥራ እንዲሠሩና ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲፈጽሙ ለማድረግ በሚያስችል ሁኔታ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ሊያደራጁትና ሊያቅዱ ይገባል። ቤተ ክርስቲያን በሚገባ መደራጀት አለባት። እንዲሁም እያንዳንዱ የቤተ ክርስቲያን አባል የተሰጠውን መንፈሳዊ ስጦታ አካሉን ለማነጽ እንዲያውለው በተናጠል የተለየ ኃላፊነት ሊሰጠው ይገባል።
3. ቤተ ክርስቲያን ለእግዚአብሔር ልታደርግ የገባችውን ግዴታ ዘወትር ልታድስ ያስፈልጋታል። አይሁድ ኃጢአታቸውን በግልጥ እንደተናዘዙ እኛም ኃጢአታችንን በመናዘዝ ራሳችንን በግልና በቡድን ማንጻት አለብን። ለእግዚአብሔርም በመታዘዝ ግልጽ ቃል ኪዳን ማድረግ አለብን። ወደ ኃጢአት ላለመመለስም ጥንቃቄ ማድረግ አለብን። ለእግዚአብሔር የገባነውንም ግዴታ ያለማቋረጥ ልናድሰው ያስፈልጋል። የቤተ ክርስቲያን መሪዎች በተለይ የሕዝባቸውን የሕይወት ንጽሕና ለመጠበቅ ጠንቃቆች መሆን አለባቸው።
✅ነህምያ እግዚአብሔር ጸሎቱን እንደሚመልስ ስላመነ፥ በኢየሩሳሌም ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይና ሥራውን ለመሥራት ምን እንደሚያስፈልገው፥ ሄዶም ምን እንደሚሠራ ለንጉሡ ለመናገር ተዘጋጅቶ ነበር። ነህምያ የዕቅዱን ምንነት በሚመለከት ንጉሡ እስኪጠይቀው ድረስ አልጠበቀም፤ ነገር ግን በእምነት አስቀድሞ ዐቀደ። እግዚአብሔር በሮችን እስከሚከፍትለት ድረስም ጠበቀ። ጥሩ የቤተ ክርስቲያን መሪ ሁልጊዜ የእግዚአብሔርን ሥራ እንዴት እንደሚሠራ የሚያቅድ፥ ሥራውን ለማሻሻል ምን መደረግ እንዳለበትና እንዴት ማደረግ እንዳለበት የሚወስን የተግባር ሰው ነው።
ኦቻ የእናት ቃ/ህ/ቤት ክርስቲያን
ኦቻ የእናት ቃ/ህ/ቤት ክርስቲያን
ኦቻ የእናት ቃ/ህ/ቤት ክርስቲያን