ኦቻ የእናት ቃ/ህ/ቤት ክርስቲያን

ኦቻ የእናት ቃ/ህ/ቤት ክርስቲያን “የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።” 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥18

  የተዘጋጀ ሥልጠና ነህ 1:1-11የእግዚአብሔር_ቤት_ቅናት_ያለው_ወጣት✅ነህምያ በምርኮ ዘመን በምርኮ አገር የተወለደ አይሁዳዊ ነው። እግዚአብሔር በፋርስ መንግሥት ውስጥ ከፍተኛ ሥልጣን እን...
27/05/2026

የተዘጋጀ ሥልጠና ነህ 1:1-11
የእግዚአብሔር_ቤት_ቅናት_ያለው_ወጣት
✅ነህምያ በምርኮ ዘመን በምርኮ አገር የተወለደ አይሁዳዊ ነው። እግዚአብሔር በፋርስ መንግሥት ውስጥ ከፍተኛ ሥልጣን እንዲያገኝ አደረገው። ነህምያ የንጉሡ ጠጅ አሳላፊ ነበር። ይህ ከፍተኛ የሥልጣን ስፍራ ባይመስልም፥ ጠጅ አሳላፊነት በጥንት ዘመን የንጉሡ ወዳጅ ለሆነና በከፍተኛ ደረጃ ታማኝነት ላለው ሰው የሚሰጥ ሥራ ነበር። ጠጅ አሳላፊ ታማኝ መሆን የነበረበት ሰዎች ንጉሡን የመግደል ሙከራ የሚያደርጉበት አንዱ መንገድ በሚበላው ወይም በሚጠጣው ነገር ላይ መርዝ በመጨመር ስለ ነበር ነው፤ ስለዚህ ይህ ማለት ነህምያ የፋርስ ንጉሥ የቅርብ አማካሪ ከሆኑት ሰዎች አንዱ ነበር ማለት ነው። ነህምያ በመንግሥት ዘንድ በጣም ጥሩ ሥራ ያለውና ጥሩ ኑሮን የሚኖር ቢሆንም፥ ወገኖቹንና ጨርሶ አይቷት የማያውቃትን ኢየሩሳሌምን አልረሳም። ነህምያ እግዚአብሔርን የሚወድ፥ ስለ እግዚአብሔር ክብርና ስለ ሕዝቡ በጣም የሚገደው ሰው ነበር። የኢየሩሳሌም ቅጥር ባለመሠራቱ የእግዚአብሔር ስም ተነቅፍ ስለ ነበረና ሕዝቡም ለጠላት ጥቃት ተጋልጠው ስለ ነበር ነህምያ ስለ ደኅንነታቸው ገደደውና የኢየሩሳሌምን ቅጥር በመሥራት እርሱን ይጠቀምበት ዘንድ እግዚአብሔርን ለመነ።
የእግዚአብሔር ቤት ቅናት
✅ቅናት ማለት ለአንድ አላማ ያለው ቁርጠኝነት፣ ዉሳኔ እና መሰጠት ማለት ነው ።
✅ በአላማ ፀንቶ መቆም ማለት ነው
✅ ለአላማ መጨከን ነው ።
✅ አንድ ነገርን ለማሳካት የሚደረግ ጥረት/ጉጉት ።
✔✔ ቅናት ያለባቸው ሰዎች በምድር ላይ መፍትሔውን ያመጣሉ።
✅ መነሳሳትን ያመጣል።
✅ ኃይልን ይሰጣል ።
✅ እምነትን ይሰጣል ።
✅ ከታሠረንበት ቦታ ጥሰን ለመሄድ ኃይልን ይሰጣል
ቅናት ለእግዚአብሔርና ለእግዚአብሔር ፍቅር በጉጉት ለመኖር ይጠቅመናል
“ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም ድረስ በፍርድና በጽድቅ ያጸናውና ይደግፈው ዘንድ በዳዊት ዙፋንና በመንግሥቱ ላይ አለቅነቱ ይበዛል፥ ለሰላሙም ፍፃሜ የለውም። የእግዚአብሔር ቅንዓት ይህን ያደርጋል።” ኢሳይያስ 9፥7
❤መንፈሳዊ ቅናት ራስህን ያስጥላል
❤መንፈሳዊ ቅናት #ምኞትን አያመጣም #ራዕይን ያመጣል

ለነህምያ #ሁለት ዓይነት ቅናት አለው
✔ ፦ማለት ሰዉ ነኝ ብሎ መነሳት፡- የኢየሩሳሌም ቅጥሮች የእግዚአብሔር ሕዝብ ያሉበት መንፈሳዊ ሁኔታ ምልክት ነበሩ። ቅጥሮቹ እስካልተሠሩ ድረስ እግዚአብሔር ስሙን ሊያኖርባትና ሊመለክባት ተስፋ ለሰጣት ለዚህች ከተማ በቂ ትኩረት እንደሌለ የሚያሳይ ነበር። እግዚአብሔር ሊመለክበት ባለው ስፍራ ስሙን ለማኖር ቃል ገብቶ ነበር። የእግዚአብሔር ከተማ የነበረችው የኢየሩሳሌም ውጫዊ ሁኔታ የእግዚአብሔርን ሕዝብ የልብ መንፈሳዊ አቋም የሚያንጸባርቅ ነበር። ሰውን እንደ ሰው መቆጠር ።
✔ ፦ ምንጩ ከመንፈስ ቅዱስ ነው።
✅መንፈሳዊ ቅናት ስለ እግዚአብሔር ቃልና ስለ ወንጌል ነው።

የነህምያ የመጀመሪያ አገልግሎት የኢየሩሳሌምን ቅጥር እንደገና መሥራት ነበር። ይህ ነገር በጣም አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው? ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነበሩ፡፡ የመጀመሪያው፥ በጥንት ዘመን ሕዝቦች ድንገት ከሚመጣ የጠላት ጦርና ከሚዘርፍ ወራሪ የሚከላከሉበት ዋናው መንገድ የከተማ መከለያ ቅጥር ነበር፤ ስለዚህ በኢየሩሳሌም ከተማ ዙሪያ ቅጥር እስከሌለ ድረስ የእግዚአብሔር ሕዝብ ሰላም ሊኖራቸውና የደኅንነት ዋስትና ሊያገኙ አይችሉም ነበር። ይልቁንም በማያቋርጥ ፍርሃት መኖር ዕጣ ፈንታቸው ነበር። ልክ ቅጥሩ እንደተሠራ ሕዝቡ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ላይ በማተኮር የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማትና ለመታዘዝ የነበራቸውን ፈቃደኝነት ማየት የሚያስገርም ነው።
✅በመንፈሳዊ ቅናት ያለው አገልጋይ ለእግዚአብሔርና ለራሱ ጠንካራና ትጉ ይሆናል።
?
✅ግብዝና የሌለበት እምነት ያለው ሰው ነው
✅ብርቱ አገልጋይ ነው
✅ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት ያጠናከረ ወጣት
✅የሚጸልይ አገልጋይ እና የዉሳኔ ሰው ናቸዉ።
✔እንደ ነህምያ የእግዚአብሔር ቤት ቅናት ያለው ወጣት ማወቅ ያለበት ነገሮች
1. አንዲት ቤተ ክርስቲያን ልትገነባና ጤነኛ ልትሆን ከተፈለገ ተገቢ የሆኑ መሪዎች ያስፈልጓታል። እነዚህ መሪዎች ከሁሉ በፊት ተገቢ መንፈሳዊ መመዘኛዎችን ማሟላት አለባቸው። እግዚአብሔርን መውደድ አለባቸው፤ ለእግዚአብሔር ሕግ ሊገዳቸው ያስፈልጋል፤ ኃጢአትን ሊጠሉና የጸሎት ሰዎች ሊሆኑም ይገባል።
2. መሪዎች እግዚአብሔር ለቤተ ክርስቲያን የሰጣትን ሥራ እንዲሠሩና ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲፈጽሙ ለማድረግ በሚያስችል ሁኔታ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ሊያደራጁትና ሊያቅዱ ይገባል። ቤተ ክርስቲያን በሚገባ መደራጀት አለባት። እንዲሁም እያንዳንዱ የቤተ ክርስቲያን አባል የተሰጠውን መንፈሳዊ ስጦታ አካሉን ለማነጽ እንዲያውለው በተናጠል የተለየ ኃላፊነት ሊሰጠው ይገባል።
3. ቤተ ክርስቲያን ለእግዚአብሔር ልታደርግ የገባችውን ግዴታ ዘወትር ልታድስ ያስፈልጋታል። አይሁድ ኃጢአታቸውን በግልጥ እንደተናዘዙ እኛም ኃጢአታችንን በመናዘዝ ራሳችንን በግልና በቡድን ማንጻት አለብን። ለእግዚአብሔርም በመታዘዝ ግልጽ ቃል ኪዳን ማድረግ አለብን። ወደ ኃጢአት ላለመመለስም ጥንቃቄ ማድረግ አለብን። ለእግዚአብሔር የገባነውንም ግዴታ ያለማቋረጥ ልናድሰው ያስፈልጋል። የቤተ ክርስቲያን መሪዎች በተለይ የሕዝባቸውን የሕይወት ንጽሕና ለመጠበቅ ጠንቃቆች መሆን አለባቸው።
✅ነህምያ እግዚአብሔር ጸሎቱን እንደሚመልስ ስላመነ፥ በኢየሩሳሌም ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይና ሥራውን ለመሥራት ምን እንደሚያስፈልገው፥ ሄዶም ምን እንደሚሠራ ለንጉሡ ለመናገር ተዘጋጅቶ ነበር። ነህምያ የዕቅዱን ምንነት በሚመለከት ንጉሡ እስኪጠይቀው ድረስ አልጠበቀም፤ ነገር ግን በእምነት አስቀድሞ ዐቀደ። እግዚአብሔር በሮችን እስከሚከፍትለት ድረስም ጠበቀ። ጥሩ የቤተ ክርስቲያን መሪ ሁልጊዜ የእግዚአብሔርን ሥራ እንዴት እንደሚሠራ የሚያቅድ፥ ሥራውን ለማሻሻል ምን መደረግ እንዳለበትና እንዴት ማደረግ እንዳለበት የሚወስን የተግባር ሰው ነው።
ኦቻ የእናት ቃ/ህ/ቤት ክርስቲያን

ኦቻ የእናት ቃ/ህ/ቤት ክርስቲያን

ኦቻ የእናት ቃ/ህ/ቤት ክርስቲያን

  ዎሳ ኬቴ ሳባይ ቤንጌ ቤንጌ ዎሳ ኬቴ ዎልቃይ ቤንጌ ሐች እጣጌዛረትድ ያንዴ ባሶሑዋ ስማንዴኑ አይፌ በኣንዴ ሔጋ በእን ኑ ላይታይ ዉራንዴዛረትድ ያንዴ ባሶሑዋ ስማንዴኑ አይፌ በኣንዴ ሔጋ ...
24/05/2026



ዎሳ ኬቴ ሳባይ ቤንጌ ቤንጌ
ዎሳ ኬቴ ዎልቃይ ቤንጌ ሐች እጣጌ

ዛረትድ ያንዴ ባሶሑዋ ስማንዴ
ኑ አይፌ በኣንዴ ሔጋ በእን ኑ ላይታይ ዉራንዴ
ዛረትድ ያንዴ ባሶሑዋ ስማንዴ
ኑ አይፌ በኣንዴ ሔጋ በእን ኑና ሐይቄይ ወራንዴ

ኑ አዋቱ ዎልቃይ ዮ ዮ ጦሶ ኑ ዮ
ዎሳ ኬቴ ቦንቾይ ስሞ ዮ ዮ ጦሶ ኑ ዮ
ከእርሱም የተነሣ አካል ሁሉ እያንዳንዱ ክፍል በልክ እንደሚሠራ ፥ በተሰጠለት በጅማት ሁሉ እየተጋጠመና እየተያያዘ ፥ ራሱን በፍቅር ለማነጽ አካሉን ያሳድጋል ።” ኤፌ. 4 ፡ 16 ።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የቤተ ክርስቲያን ራስ ነው ። ራስ አካል ፣ ሙሽራም ሙሽራይት አሉት ። ጌታችንም አካሉ የሆነች ቤተ ክርስቲያን ፣ ሙሽራይት የሆነች ምእመን አለችው ። ራስ አካሉን ይንከባከባል ። ጌታችንም አካሉ የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን በጸጋ ፣ በምሥጢራት ፣ በአገልጋዮች ይንከባከባታል ። ራስ አካሉን ያድናል ፣ ጌታችንም አካሉ የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን አድኗታል ። ራስ የአካሉ ሕመም ይሰማዋል ፣ ጌታችንም የቤተ ክርስቲያን ነገር ገና ከጀርባው ያልወረደ መስቀሉ ነው ። ራስ ከአካሉ አይለይም ፣ ጌታችን ቤተ ክርስቲያንን ለዘላለም ወዷታል ። ራስ አካሉን ይሸፍናል ፣ ጌታችንም ለቤተ ክርስቲያን ማጌጥ በአደባባይ ተራቁታል ። ራስ አካሉን ያፈቅራል ፣ ጌታችን ቤተ ክርስቲያንን በአጋፔ ፍቅር ወዶአታል ። ሰው እጁን የሚወደው ስለ ሠራ ፣ እግሩን የሚወደው በሩጫ ድል ስላመጣለት አይደለም ። አካሉ ስለሆነ ያለ ቅድመ ሁኔታ ይወደዋል ። ጌታችንም ቤተ ክርስቲያንን እንዲሁ ወዶአታል ። ራስ አካሉን ያነጻል ፣ ጌታችንም ቤተ ክርስቲያንን በደሙ ቀድሶአል ። ቤተ ክርስቲያን የተባለችም የዳነች የምእመናን ስብስብ ፣ ሕያዊት አካል ናት ።

ጌታችን ሙሽራይት አለችው ። ሙሽራ ነውና ። ደቀ መዛሙርትም በአማኝነታቸው ሙሽራይት ፣ በአገልጋይነታቸው ሚዜዎች ናቸው ። ሙሽራ የሰርጉን ቀን ይናፍቃል ፣ ጌታችንም ዳግም እስኪወስደን ቀጠሮ ሰጥቶናል ። ሙሽራ ሚዜዎች ያዘጋጃል ፣ ጌታችንም አገልጋዮችን ሾሞልናል ። ሙሽራ ሽማግሌ ይልካል ፣ ጌታችንም የልባችንን ደጃፍ ያንኳኳል ። በ40 እና በ80 ቀን ስንጠመቅም ለቤተሰቦቻችን ሽማግሌ እንደላከ ማሳያ ነው ። ወላጆች “ልጄን ለልጅህ” ይላሉ ። እንዲሁም አማኝ ሲሆኑ “ልጄን ለክርስቶስ” በማለት ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና ያሰጣሉ ። ሙሽራ ሁሉን አዘጋጅቶ ሙሽራይትን ይጠብቃል ፣ ጌታችንም ስፍራ ሊያዘጋጅ ወደ ሰማይ ሂዷል ። ሙሽራ ወደ አባቱ ቤት ሙሽራይትን ይዞ ይመጣል ፣ ጌታችንም በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ ብሎ ለምእመን ነግሮአታል ። ሙሽራ ማጫ ያመጣል ፣ ጌታችንም ለወንጌል ሙሽራይት ኦሪትን ማጫ አድርጎ ሰጥቷል ። ሙሽራ የሰርግ ቀን አለው ፣ ጌታችንም በዳግም ምጽአት ታላቅ እራት አዘጋጅቷል ። ሙሽራ ለሙሽራይት ራሱን ይሰጣል ፣ ጌታችንም ለምእመን በአደባባይ ተሰቅሏል ። አንድ ሙሽራ አንዲት ሙሽራይት አለችው ፣ ጌታችንም አንዲት ቤተ ክርስቲያን አለችው ። ሙሽራይትም አንድ ሙሽራ አላት ፣ ቤተ ክርስቲያንም አንድ ጌታ አላት ። ሙሽራ ሲመጣ ዜማው በሩቅ ይሰማል ፣ ጌታችንም የመምጣቱ ደወል እየተሰማ ነው ። ሙሽራ ሙሽራይትን ከወላጆችዋ ቤት ወስዶ ወላጅ ይሆናታል ፣ ጌታችንም ቤተ ክርስቲያንን ከምድራዊ ኑሮ ፣ ከሥጋ ስሌት አድኗታል ። ሙሽራ ሙሽራይቱን ይቀልባታል ፣ ጌታችንም ቤተ ክርስቲያንን ለምትበይው ለምትጠጭው አትጨነቂ ብሏታል ። ሙሽራ ጓዙን አስቀድሞ እርሱ ይመጣል ፣ ጌታችንም የዘመን ምልክቱን አስቀድሞ ይመጣል ።
ሙሽራ ሙሽራይትን ያበላል ፣ ጌታችንም ሥጋና ደሙን ለምእመን ሰጥቷል ።

የመንፈሳዊ ዕድገት ልኩ ክርስቶስ ነው ። እንደ እገሌ ሳይሆን ክርስቶስን ለመምሰል ተጠርተናል ። ክርስቶስን የምንመስለው በአምላክነቱ ሳይሆን አርአያ ሁኖ ያሳየንን የኑሮ ልክ ለዓለም መግለጥ አለብን ። ለዚህች ዓለም ተጨማሪ ችግር ሳይሆን መፍትሔ ልንሆን ይገባናል ። ለጨለማው ዓለም ብርሃን ፣ ለአልጫው ዓለም ጨው አድርጎናል ። እርሱ አባቱን ለማክበር እንደኖረ እኛም ለእርሱ ክብር መኖር አለብን ። ሕይወታችን ለእግዚአብሔር ምስጋና የሚያመጣ መሆን አለበት ። በሠራናቸው ጥቃቅን መልካምነቶች የምንረካ ከሆነ የዕድገታችን ልኩ ክርስቶስ ነውና እስከ ዘላለም በዕድገት ውስጥ ነን ። መቼም ቢሆን ክርስቶስን አንመስልምና ። ክርስትና ሁልጊዜ ተማሪነት ፣ ሁልጊዜ ነዋሪነት ነው ። ወደ ዕድገት የምንወጣበት መሰላልም እውነትን በፍቅር መያዝ ነው ። እውነትን በፍቅር ስንይዝ መሆን ያለብንን እየሆንን እንመጣለን ።

እኛ ሁላችን የአካሉ ክፍል ስንሆን እያንዳንዳችን የአካሉ ክፍልፋይ ነን ። በአንድ ራስ ሥር ፣ ብዙ የአካል ክፍሎች አሉ ። የተለያየ ስም ፣ ክፍል ፣ ግብር ያላቸው የአካል ክፍልፋዮች በራሱ አንድ እንደሆኑ እኛም በክርስቶስ አንድ ነን ። እጅ የእጅነት ድርሻን ሳይጨነቅም ሳይሳነፍም መያዝ ግዴታው ነው ። ሁሉም የልኩን ከሠራ ተግባር ሙሉ ይሆናል ። ጅማትም አካልን እንደሚያስተሳስር ፣ የአካልም ሕያውነት በጅማቱ በሚመጣው የተጣራ ምግብና አየር ሕያው እንደሚሆን የምእመናን ማስተሳሰሪያው የተመሠረቱበት እውነትና የሚያድጉበት ፍቅር ነው ። ተነጣጥሎ የሚኖር የአካል ክፍል የለም ፤ አንድ ጡብ ያለ ሌላው በራሱ ቤት መሆን አይችልምና ኅብረት ያስፈልገናል ። በክርስትና ኅብረት ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው ።

ፍቅር ቀዝቅዞ ፣ ኅብረት ወደ ቡድን ተለውጦ ፣ አብሮ የጸለየ ተራርቆ እየተወራወረ ፣ አብሮ ያስቀደሰ በዘር በቋንቋ እየተናቆረ ነውና እውነትን በፍቅር ለመያዝ ጊዜው አሁን ነው ።

ኦቻ የእናት ቃ/ህ/ቤት ክርስቲያን

 #ደረሰ  #ደረሰ   እነሆ ከፊታችን ከግንቦት 19/2018 ዓ/ም ዕለት ዕሮብ ከቀኑ 2:30🕓 ጀምሮ ለ25ቱ አ/ቃ/ህ/ቤተ/ያን ወጣቶች እና መዘመራን የስልጠና ጊዜ በኦቻ ዙሪያ ላሉት አጥቢያ...
22/05/2026

#ደረሰ #ደረሰ

እነሆ ከፊታችን ከግንቦት 19/2018 ዓ/ም ዕለት ዕሮብ ከቀኑ 2:30🕓 ጀምሮ ለ25ቱ አ/ቃ/ህ/ቤተ/ያን ወጣቶች እና መዘመራን የስልጠና ጊዜ በኦቻ ዙሪያ ላሉት አጥቢያዎች በሕብረቱ በኩል ተዘጋጅቷል።
✍️ ልብ በሉ ከፊታችን ዕሮብ መቅረት አይታሰብም።
ወጣቶች አገልጋዮች መጽሐፍ ቅዱስ፣የማስታወሻ ደብተር እና እስክርቢቶ እንዳይረሳ።
የስልጠና ቦታ ማሪ ከ/አ/ቃ/ህ/ቤተ/ያን ቅጥር ግቢ ውስጥ

ርዕስ   2 ዜና 20:21 ከሕዝቡም ጋር ተማክሮ በሠራዊቱ ፊት የሚሄዱትን፦ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ የሚሉትንም፥ ጌጠኛ ልብስም ለብሰው የሚያመሰግኑትን፥ ለእግዚአብሔርም...
17/05/2026

ርዕስ
2 ዜና 20:21 ከሕዝቡም ጋር ተማክሮ በሠራዊቱ ፊት የሚሄዱትን፦ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ የሚሉትንም፥ ጌጠኛ ልብስም ለብሰው የሚያመሰግኑትን፥ ለእግዚአብሔርም የሚዘምሩትን መዘምራን አቆመ። ዝማሬውንና ምስጋናውንም በጀመሩ ጊዜ ይሁዳን ሊወጉ በመጡት በአሞንና በሞዓብ ልጆች በሴይርም ተራራ ሰዎች ላይ እግዚአብሔር ድብቅ ጦርን አመጣባቸው፤ እነርሱም ተመቱ።ዘጸአት 15¹¹ አቤቱ፥ በአማልክት መካከል እንደ አንተ ያለ ማን ነው? በምስጋና የተፈራህ፥ ድንቅንም የምታደርግ፥ በቅድስና የከበረ እንዳንተ ያለ ማን ነው? ቀኝህን ዘረጋህ፥ ምድርም ዋጠቻቸው።በቸርነትህ የተቤዠሃቸውን ሕዝብህን መራህ፤ በኃይልህ ወደ ቅዱስ ማደሪያህ አገባሃቸው። አሕዛብ ሰሙ፥ ተንቀጠቀጡም፤ በፍልስጥኤም የሚኖሩትን ምጥ ያዛቸው። የዚያን ጊዜ የኤዶም አለቆች ደነገጡ፤ የሞዓብን ኃያላን መንቀጥቀጥ ያዛቸው፤ በከነዓን የሚኖሩ ሁሉ ቀለጡ። አቤቱ፥ ሕዝብህ እስኪያልፍ ድረስ፥ የተቤዠኸው ሕዝብ እስኪያልፍ ድረስ፥ ፍርሃትና ድንጋጤ ወደቀባቸው፤ በክንድህ ብርታት እንደ ድንጋይ ዝም አሉ።
?
1,በምስጋና ድል ስለምገኝ“ምስጋና የሚሠዋ ያከብረኛል፤ የእግዚአብሔርን ማዳን ለእርሱ የማሳይበት መንገድ ከዚያ አለ።” መዝሙር 50፥23
2, ትዕዛዝ ስለሆነ 1ኛ ተሰሎንቄ 5¹⁶ ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።
3, ምስጋናው ዝግ ደጆችን ይከፈታል ሐዋርያት 16²⁶ ድንገትም የወኅኒው መሠረት እስኪናወጥ ድረስ ታላቅ የምድር መንቀጥቀጥ ሆነ፤ በዚያን ጊዜም ደጆቹ ሁሉ ተከፈቱ የሁሉም እስራት ተፈታ። የወኅኒውም ጠባቂ ከእንቅልፉ ነቅቶ የወኅኒው ደጆች ተከፍተው ባየ ጊዜ፥ እስረኞቹ ያመለጡ መስሎት ራሱን ይገድል ዘንድ አስቦ ሰይፉን መዘዘ።
4, እስራትን ይፈታል

16/05/2026

#ተጋብዛችኋል

 “የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።...
15/05/2026



“የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።”
— 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥16-17
በኦሞ ጎጀብ ቀጠና ቃል ሕይወት ቤተክርስቲያን ኦቻ እና ዙሪያ አ/ህብረት ለ25ቱ አ/ቤተክርስቲያን ወጣት መሪዎች እና መዘምራን በመሉ ለ2ኛ ዙሪ ስልጠና በቀን 19/09/2018 ዓ.ም ዕለት ሪቡዕ ስለተዘጋጀ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።

 #በድል  #ተጠናቀቀ ርዕስ  #የቤተክርስቲያን  #ስርዓትአማኞች ወደ አዲሱ የኑሮ ስርአት በመሸጋገራቸው የሚፈጥሩት ሕብረት የቅዱሳን ሕብረት (ቤተ-ክርስቲያን) ተብሎ ይጠራል::ቤተ-ክርስቲያን...
19/04/2026

#በድል #ተጠናቀቀ
ርዕስ #የቤተክርስቲያን #ስርዓት

አማኞች ወደ አዲሱ የኑሮ ስርአት በመሸጋገራቸው የሚፈጥሩት ሕብረት የቅዱሳን ሕብረት (ቤተ-ክርስቲያን) ተብሎ ይጠራል::
ቤተ-ክርስቲያን የሚለው ቃል የተተረጎመው ‹‹ኤክሌሽያ›› ከሚለው የግሪክ ቃል ሲሆን የቃሉ ሐሳብ ‹‹ማሕበር›› ወይም ‹‹ጉባኤ›› ተብሎ ሊገለጽ ይችላል::
በጉባኤው የሚገኙ የክርስቶስ ተከታዮች ስለሆኑ እግዚአብሔርን ለማምለክ ሲሰበሰቡ ቤተ-ክርስቲያንን ይመሰርታሉ:: ስለዚህ ቤተክርስቲያን ማለት ከአለም ተጠርተው የወጡና ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝ መሆኑን አምነው ለእርሱ የሚገዙና ስለ እርሱ የሚመሰክሩ ሰዎች የሚሰበሰቡበት ሕብረት ማለት ነው::
#ለክርስቲያኖች የተሰጡ ስያሜዎች
✅ወንድሞች (ሐዋ9-:-30)
✅አማኞች (ሐዋ4-:-32)
✅ቅዱሳን (ፊል1-:-1)
✅የተመረጠ ትውልድ (1ጴጥ2-:-9-10)
✅ደቀመዝሙር (ማቴ28-:-18-20,ሐዋ9-:-19)
✅ክርስቲያን (ሐዋ11-:-26,1ጴጥ4-:-16)
#ለቤተክርስቲያን የተሰጡ ስሞች
✔የክርስቶስ አካል (1ቆሮ12-:-12-27,ኤፌ1-:-1-23)
✔የእግዚአብሔር ቤተ-መቅደስ (1ጴጥ2-:-5-6,1ቆሮ3-:-16-17)
✔የክርስቶስ ሙሽሪት (2ቆሮ11-:-2,ኤፌ5-:-25-27,ራዕ19-:-7)
#የቤተክርስቲያን አይነት
➢ የማትታየውና ሕዋ አቀፏ (ኤፌ5-:-23,3-:-20-21,ማቴ16-:-18) በድል አድራጊነት በክብር ላይ የምትገኝ
➢ የምትታየውና በአንድ አካባቢ የምትገኝ ገና በጦርነት ላይ ያለችው አጥቢያ ቤተ-ክርስቲያን (ሐዋ20-:-28,ራዕ1-:-11,ማቴ18-:-17,ሐዋ14-:-23,ዮሐ16-:-33)
#የቤተክርስቲያን ዓላማና ተልዕኮ
✅አምልኮን ለእግዚአብሔር ማካሄድ (ዮሐ4-:-23-24,ዕብ13-:-15)
✅ወንጌልን (የምስራች ቃልን) ላላመኑ ማብሰር (ማር16-:-15,ሐዋ1-:-8)
✅ምዕመናንን በመንፈሳዊ ሕይወት ማሳደግ (ማስተማር) (2ጴጥ3-:-18,2ጢሞ3-:-14-17,ኤፌ4-:-11-13)
✅በማህበራዊ ኑሮ እርስ በእርስ መደጋገፍና መረዳዳት (ሐዋ6-:-1-6,2-:-42-47)
✅ስርአቶቹን ሁሉ እየፈጸመች የጌታን ምጻት መጠበቅ (ዘጸ15-:-26,ራዕ16-:-15,ማቴ25-:-1-46)
#የአጥቢያ ቤተክርስቲያን ምዕመናን ተግባር
✔✔ለኢየሱስ ጌትነት መገዛትና ጌታ መሆኑን ለሌሎች መመስከር(ሐዋ4-:-33)
✔✔በውሃ ጥምቀት ከኢየሱስ ሞትና ትንሳኤ ጋር መተባበርን መመስከር (ሐዋ2-:-41,ሮሜ6-:-1-4,ቆላ2-:-11-12)
✔✔በመንፈስ ቅዱስ ተጠምቆ በልሳን በመናገር በእግዚአብሔር ኃይል ማገልገል(ሐዋ1-:-8,2-:-1-4,ኤፌ5-:-18)
✔✔የጌታን እራት መካፈል(1ቆሮ11-:-23-26)
✔✔በቤተክርስቲያን ሕብረት መታቀፍ፣ በጸሎት መትጋት፣ ቃሉን መመገብ (ሐዋ2-:-41-42)
✔✔መሪዎቻቸውንም እንዲወዷቸው፣ እንዲታዘዙላቸውና እንዲደግፏቸው ያስፈልጋል::(1ተሰ5-:-12,1ጢሞ5-:-17,ዕብ13-:-7,ገለ6-:-6)
#የክርስቶስና የቤተክርስቲያን ግንኙነት ምሳሌዎች
✅ራስና አካል (ኤፌ1-:-23)
✅ግንድና ቅርንጫፍ (ዮሐ15-:-1)
✅ሙሽራና ሙሽሪት (ኤፌ5-:-25-32)
✅አዛዥና ሰራዊት (2ጢሞ2-:-4)
✅እረኛና መንጋ (ዮሐ10-:-16,ዕብ13-:-20)
#የቤተ-ክርስቲያን አስተዳደር
✅የአባላት ሁሉ ተሳትፎ
✔ለአባላት ሁሉ መንፈስ ቅዱስ እንደሚፈቅድ የጸጋ ስጦታን ይሰጣቸዋል:: (1ቆሮ12-:-11-31)
✔አባላት ቤተክርስቲያንን በጸሎት ይደግፋሉ::(ሐዋ12-:-5)
✔አባላት መሪዎቻቸው በእግዚአብሔርና በእነርሱ ፊት ተጠሪ መሆናቸውን ያውቃሉ::(2ቆሮ8-:-21)
✔አባላት ቤተክርስቲያንን ገንዘብ በማዋጣት ያደራጃሉ ይረዳሉ:: (2ቆሮ9-:-11-13)
✔አባላት ለመሪዎች መታዘዝና መጸለይ ይገባቸዋል::(ቆላ4-:-3-4,ኤፌ6-:-18-20)
✅የተሾሙ መሪዎች
➢ክርስቶስ ለቤተ-ክርስቲያን አገልጋዮች ሰጠ::(ኤፌ4-:-11-13)
➢መሪዎች በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ይሾማሉ::(ሐዋ20-:-28)
➢መሪዎች በእግዚአብሔር ቃል መመዘኛ ይሾማሉ::(1ጢሞ3-:-1-7)
➢መሪዎች እንደ ጥሪያቸውና እንደ ስጦታቸው ይሾማሉ::(ሐዋ13-:-1-4)
➢መሪዎች ለእግዚአብሔርና ለሰውም ተጠሪነታቸውንና ተጠያቂነታቸውን ተረድተው ይሾማሉ::(1ጢሞ5-:-17)
#የአጥቢያ ቤተ-ክርስቲያን አስተዳደር
➢እያንዳንዱ አጥቢያ ቤተ-ክርስቲያን የራሱ አስተዳደር አለው::(ሐዋ14-:-23)
➢እያንዳንዱ አጥቢያ ቤተ-ክርስቲያን የራሱ እረኞች ይኖሩታል::(1ጴጥ5-:-2)
➢እያንዳንዱ አጥቢያ ቤተ-ክርስቲያን በራሱ ወጪ የአገልግሎት ኃላፊነቱን ይወጣል::(1ቆሮ16-:-1-2)
➢እያንዳንዱ አጥቢያ ቤተ-ክርስቲያን የወንጌል ባለራዕይና ባለአደራ ሆኖ ለሕብረተሰቡ ወንጌልን ያሰራጫል::(ሐዋ1-:-8)
➢እያንዳንዱ አጥቢያ ቤተ-ክርስቲያን በመጽሀፍ ቅዱስ ላይ በተመሰረተ ትምህርት አባላቱን ያሳድጋል:: እምነቱንም ይጠብቃል::(ይሁዳ ቁ20,ቲቶ1-:-9)
❤❤ለማሰርና ለመፍታት ስልጣን ያላት ቤተ-ክርስቲያን ዋና ተስፋዋ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚያድን፣ እንደሚፈውስና ነፃ እንደሚያወጣ፣ እንደሚባርክ፣ በመንፈስ ቅዱስ እንደሚያጠምቅና ተመልሶም እንደሚመጣ ዕለት በዕለት ማወጅ ይገባታል (ዮሐ20-:-21-23,ማቴ16-:-19,18-:-18)፡፡ ለዚህ አዋጅ ይረዳት ዘንድ በቃሉ መኖርን፣ አምልኮን፣ ጸሎትን፣ የጽድቅና የቅድስና ሕይወት ማጎልበትን፣ በመንፈስ ቅዱስ ስጦታ መገልገልን፣ በቃል ኪዳን መባረክንና ወንጌል ማሰራጨትን መሰረቷ ታደርጋለች::

ኦቻ የእናት ቃ/ህ/ቤት ክርስቲያን

  !  “ ሁሉ ተፈቅዶልኛል  : ሁሉ ግን አይጠቅምም። ሁሉ ተፈቅዶአል :በእኔ ላይ አንድ ነገር እንኳን አይሰለጥንብኝም። 1ቆሮ6፤12   የተፈቀደ  ሁሉ ....አይጠቅምም የተፈቀደ ቢሆን እን...
17/04/2026

!

“ ሁሉ ተፈቅዶልኛል : ሁሉ ግን አይጠቅምም። ሁሉ ተፈቅዶአል :በእኔ ላይ አንድ ነገር እንኳን አይሰለጥንብኝም።
1ቆሮ6፤12
የተፈቀደ ሁሉ ....አይጠቅምም
የተፈቀደ ቢሆን እንኳን ካልጠቀመን .. አናድርገው
የተፈቀደ ቢሆን እንኳን ..የሚሰለጥንብን ከሆነ አናድርገው

✅" ሁሉ ተፈቅዶልኛል ሁሉ ግን የሚጠቅም አይደለም ፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል : ነገር ግን ሁሉ የሚያንፅ አይደለም።
1ቆሮ10፤23
የተፈቀደ ሁሉ ..አያንፅም ማያንፅ ከሆነ : ይጎዳናል። !

✅" በመዝሙር በዝማሬ በመንፈሳዊ ቅኔ በፀጋው በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ "
ቆላ3፤16 ኤፌ5፤19
✅ በዘፈን ለሰው ፣ ለሀገር ዝፈኑ ..አላለንም .. በልባችንም ይሁን በአንደበታችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ ነው የተባልነው

አለምንና በአለም ያሉትን አትውደዱ
1ዩሐ2፤15-17
በአለም ካሉት አንዱ ዘፈን መስማትም መዝፈንም ነው !
አትውደዱ ፣ አትስሙ ፣ አትዝፈኑ ነው የተባልነው። የአለም ዘፈን የእግዚአብሔርን ፍቅር ከውስጣችን ያጠፉል።

✅" የስጋ ስራም የተገለጠ ነው ...
ገላ5፤19
አንዱ ዘፈንና ዘፉኝነት ዘፈንን ሰሚነትም ነው "

✅" ማናቸውንም ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉ"
1ቆሮ10፤31
በመዝፈናችሁ ዘፈን በመስማታችሁ ለእግዚአብሔር ክብር
ይሆናል ወይ። እግዚአብሔር ይመሰግንበታል ወይ !

✅(በዘፈን የሚገባባችሁ አእምሮን የሚቆጣጠር፣ የሀዘን ፣ የሴሰኛ፣ በሀሳብ መደንዘዝ፣ የበቀል ከፉፉይ መንፈስ ነው፣ በር ይከፍታል ለሰይጣን)
ዘፈን መዝፈንም የተዘፈነን መስማትም እኩል ነው !!
✅ከማንኛውም ዘፈን ጀርባ የአጋንንት መንፈስ ስላለ ዘፈንን መፅሀፍ ቅዱስ አይነቱን ሳይለይ ስለሚቃወም የምሰማው ዘፈን እግዚአብሔርን ስለማያከብር የምንሰማው ዘፈን ወደ ፅድቅ ፣ ወደ ፈርሀ እግዚአብሔር ወደ ፍቅር ፣ ወደ እምነት ስለማይመራኝ ዘፈን አእምሮን ፣ስሜትን ተቆጣጥሮ ከመንፈሳዊ የፀሎት ፣ የአምልኮ ፣ የቅድስና ሀሳብ አውጥቶ ስለሚያደክም ምላሴ የእግዚአብሔርን ፅድቅና ምስጋናውን እንድናገር እንጄ እንድዘፍንበት ስላልተሰጠኝ እስትንፉስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን እንጂ ስለ ሴትና ዳሌና ፣ወደ ሴሰኝነት የሚወስድ አድናቆት እንዳደንቅ ስላልሆነ ።

✅የእግዚአብሔር መንፈስ ሳይሆን የአጋንን መንፈስ ነው ያለው ከዘፈን ጀርባ ያለው።ዘፈን መንፈስ ቅዱስን አያስገባብንም ዘፈን ለአጋንንት አለም ነፍሳቸውን በሸጡ፣ መንፈሳቸው ባልዳነ (በአጋንንት ፈቃድ ስር) ባሉ ሰዎች ነው የሚዘፈነው። ከነሱ የምቀዳው ቅዱስ መንፈስ የለም፤እርኩስ መንፈስ እንጂ:- ለዘፈን የተነሱ ተቀሰፉ በእግዚአብሔ : ስለዚህ እግ/ር አይደግፈውም ማለት ነው። መፅሀፍ ቅዱስ በግልፅ አስተምሮአል። በፈለጋችሁት መንገድ ለራሳችሁ ፍላጎት አጣማችሁ አትተርጉሙ፣ አታስተምሩ፣ ጌታን ፍሩ።! ! !
❤-በዘፈን መስዋእት አምልኮ የሚቀበሉት አጋንንቶች ናቸው
❤-በዘፈን ውስጥ የሚተላለፍ የዝሙት ፣ የሴሰኝነት መንፈስ
❤-በዘፈን የሚተላለፍ የሀዘን ፣ የፀፀት፣ የበቀል መንፈስ ነው
❤-በዘፈን በመርካት በገባበት መንፈስ ምክንያት ነበር ዮሀንስን ለማረድ የተነሳው ንጉሱ።

✔ ለተቃራኒ ፃታም ፣ ለሀገርም ፣ ለተፈጥሮም ፣ ለፓለቲካም ፣ ይሁን ለምንም ዘፈን ዘፈን ነው።
✔ ትውልድ ሆይ የአጋንንትን ፅዋ አትጨልጡ፣ አእምሮአችሁን ፣ መንፈሳችሁ ፣ ስሜታችሁን ለአጋንንት መንፈስ ባሪያ አታድርጉ፣ አጋንንትን አታስገቡ በራሳችሁ ፈቃድ ።

በውስጣችሁ ያለው ቅዱሱ መንፈስ አይታነፅበትም ዘፈን ባለመስማቴ የጎደለብኝ ነገር የለም ደስታዬ በጌታ ሙሉ ነው !!!!

ኦቻ የእናት ቃ/ህ/ቤት ክርስቲያን

     #ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው።ከራስ እስከ ጢም እንደሚፈስስ፥ እስከ አሮን ጢም፥ በልብሱ መደረቢያ እንደሚወርድ ሽቱ ነው። መዝ 133:1ታላቅ...
13/04/2026



#ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው።ከራስ እስከ ጢም እንደሚፈስስ፥ እስከ አሮን ጢም፥ በልብሱ መደረቢያ እንደሚወርድ ሽቱ ነው። መዝ 133:1
ታላቅ የምስራች #ለኦቻና አከባብዉ በሙሉ እነሆ _ህብረት_በኦቻ_እናት አ/ቃ/ህ/ቤ/ያን #ከቀን 08/8/2018-11/8/2018 ዓ.ም ድረስ የመንፈሳዊ ኮንፈረንስ ስለተዘጋጀ ሁላቹም የበረከቱ ተካፋዮች ይሁኑ።

የጌታችንና የመዳንታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋና ሰላም ይብዛላቹ ።

13/04/2026

Address

ኦቻ እናት ቃ/ህ/ቤ/ክ/ያን
Awassa
1015

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኦቻ የእናት ቃ/ህ/ቤት ክርስቲያን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share