14/08/2026
#ማንኛውም አገልግሎት(ራዕይ )መድረሻና ፍፃሜ አለው።
ይህ ባይሆን ግን የመጀመሪያውን እርምጃ ባልጀመርን ነበር።ሁልጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል አጥብቀን ይዘን እግዚአብሔር በዚህ ምድር ላይ ለእኛ ያዘጋጀውን ለመቀበል መትጋት ይኖርብናል።
“እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን።”
— ሮሜ 8፥28
#በህይወት ጉዞ ላይ መሰናክሎች ያሉ ቢሆኑም የችግሮቹን ዘላቂ የሆነ ተግዳሮት
የምንወስነው ግን እኛ እንሆናለን።ምን እንኳን የተጠራን
ቢሆንም ተስፋ ሊያስቆርጡንና ራእያችንን ሊያመክኑ ከሚላኩ የክፋት መንፈሳዊ ኃይሎች ጋር ውጊያው አይቀሬ ነው።የሚረዱን የእግዚአብሔር መላእክቶች በዙሪያችን ቢኖሩም ፍፃሜያችንን ለማጠናቀቅ የምናደርገው ጦርነት የራሳችንን ኃላፊነት የሚጠይቅና ያለጥርጥር ማሸነፍ
የሚገባን ውጊያ ነው።
“በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን።”
— ሮሜ 8፥37
ሰናይ ጊዜ ይሁንላቹ የአባቴ ብሩካን!!
MELESE MARKOS
OF EPIKAIZO INT /CHURCH
OF EPIKAIZO TV CHANNEL