Hawassa Saint Rufael Sunday School-የሀዋሳ ደብረ ታቦር ቅዱስ ሩፋኤል ሰንበት ትምህርት ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Awassa
  • Hawassa Saint Rufael Sunday School-የሀዋሳ ደብረ ታቦር ቅዱስ ሩፋኤል ሰንበት ትምህርት ቤት

Hawassa Saint Rufael Sunday School-የሀዋሳ ደብረ ታቦር ቅዱስ ሩፋኤል ሰንበት ትምህርት ቤት በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜንǃǃǃⵆ

ይህ የሀዋሳ ደብረ ታቦር ቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስትያን ሰንበት ት∕ቤት ይፋዊ የፌስ ቡክ ገጽ ነውⵆ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከሀዲያና ስልጤ ሀገረ   ስብከት ጽ/ቤት የአደባባይ በዓላት አከባበርን በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ፤         በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ...
23/09/2021

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የአደባባይ በዓላት አከባበርን በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ፤

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የሆሳዕና ከተማ ጥምቀተ ባህርና የመስቀል ደመራ በዓላት ማክበሪያ ቦታ እንዲከበር ከ1974 ዓ.ም ጀምሮ ለመንግሥት እያቀረበ ባለው ጥያቄ መሰረት መንግሥት ቦታው ለቤተ ክርስቲያኒቱ እንዲከበር የተለያዩ ውሳኔዎችን ቢሰጥም ጉዳዩ በውሳኔው መሰረት ሊፈጸምልን ያልቻለና ቦታው ለሌላ የማህበራዊ አገልግሎት (ለገበያ )እንዲውል በመደረጉ የበዓላት ማክበሪያው ቦታ በገበያተኛ መሃል የተከበበና በቆሻሻ ክምችት የተበከለ ቦታ ስለሆነ ለአምልኮተ እግዚአብሔርና ለቤተ-ክርስቲያኒቱ እንዲሁም ለሕዝበ ክርስቲያኑ ክብር ሲባል ቦታው ተከብሮ ቤተ-ክርስቲያኒቱ ለምትፈልገው አገልግሎት ምቹ እስከሚሆን ድረስ በቦታው ላይ በዓደባባይ የሚከበሩ የጥምቀትና የመስቀል ደመራ በዓላትን ላለማክበር ቀደም ሲል መስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም እና ጥር 9 ቀን 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መሰረት የ2013 ዓ.ም የመስቀል ደመራና የጥምቀት በዓላት ሳይከበሩ መቅረታቸው ይታወቃል ።

አሁንም ቢሆን ሀገረ ስብከቱና በጉዳዩ ላይ የተቋቋመው ኮሚቴ የቤተ-ክርስቲያኒቱን ተቋማዊና የህዝበ ክርስቲያኑን ነጻና ሰላማዊ በሆነ ቦታ ላይ የማምለክ ሕገ መንግሥታዊ መብት ለማስከበር በየደረጃው ለሚገኙ የመንግሥትን አካላት ጥያቄውን በማቅረብ ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ ለሚደረገው ጥረት በሀዲያ ዞን አስተዳደርና በደ/ብ/ብ/ክ/መንግሥት በኩል በርካታ በጎ ምላሾችን ቢያገኝም እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ አሁንም በአፈጻጸም ችግር ምክንያት ጉዳዩ ሊፈጸም ያልቻለና በቦታው ላይ ያሉ ችግሮች በዘላቂነት ሊቀረፉ ያልቻለ ስለሆነ የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ቀደም ሲል መስከረም 8 ቀን 2013 ዓ.ም እና ጥር 9 ቀን 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መሰረት የ2014 ዓ.ም የአደባባይ በዓላቶችን ማክበር የማንችል መሆኑን እየገለጽን መንግሥት ለጉዳዩን ዘላቂ መፍትሔ እስከሚሰጥና የመጨረሻውን ዕልባት እስክናገኝ ድረስ መላው የሆሣዕና ከተማ ምዕመናን በፀሎትና በትዕግስት እንድትጠባበቁ በአክብሮት እንገልጻለን ።
መስከረም 13 ቀን 2014 ዓ/ም
ሆሣዕና

17/09/2021
ለማህበረ ካህናት ወምእመናንእንኳን ከዘመነ ቅዱስ ማቴዎስ ወደ ዘመነ ቅዱስ ማርቆስ በሰላምና በጤና አሻገረን አሻገራችሁ፡፡‹‹ወትባርክ አክሊለ ዓመተ ምሕረትከ፡፡ ወይጸግቡ ጠላተ ገዳም፡፡ ወይረ...
10/09/2021

ለማህበረ ካህናት ወምእመናን
እንኳን ከዘመነ ቅዱስ ማቴዎስ ወደ ዘመነ ቅዱስ ማርቆስ በሰላምና በጤና አሻገረን አሻገራችሁ፡፡
‹‹ወትባርክ አክሊለ ዓመተ ምሕረትከ፡፡
ወይጸግቡ ጠላተ ገዳም፡፡ ወይረውዩ አድባረ በድው››
‹‹በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፡፡
ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል፡፡ የምድረ በዳ ተራሮች ይረካሉ›› መዝ 64፣11

ይህ የቅዱስ ዳዊት ቃል የአምላካችን የአግዚአብሔርን ድንቅ መጋቢነት የሚያስረዳ ነው፡፡ የዘመናት ባለቤት ቅዱስ አግዚአብሔር ምድር በበረከት እንድትሞላ የሚያደርግ ሁሉን ያለ አድልኦ የሚመግብ ነው፡፡ በበጋ ደርቀው የተሰነጣጠቁ የምድር ክፍሎች በክረምት በሰማይ በረከት ረክተው በልምላሜ ሲሞሉ እንዴት የምድራችን ገጽታ እንደሚቀየር መመልከት አዲሱ ዘመን ሲመጣ ሁሌም የምናልፍበት ተፈጥሯዊ ሂደት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ዓመታትን ለሚያቀዳጀው፤ ምድርንም በልምላሜ ለሚያስጌጠው እንዲሁም የምድረ በዳ ተራሮችንም ለሚያረካው ለእግዚአብሔር ምስጋና ለማቅረብ የአዲሱን ዓመት መጀመሪያ ርእሰ አውደ ዓመት ወይም ቅዱስ ዮሐንስ በሚል ስያሜ ታከብራለች፡፡ ምክንያቱም የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ተግባር ለዘመነ ወንጌል በር ወይም መነሻ እንደሆነ ሁሉ መስከረም አንድም ለአዲስ ዓመት መግቢያ ነውና፡፡
ዘመን መለወጫ መስከረም ወር የሆነበት ምክንያት ብርሃናት (ፀሐይ፣ ጨረቃ እና ከዋክብት) የዓመት ዑደታቸውን በጳጒሜን ወር ጨርሰው በመስከረም ወር ስለሚጀምሩ ነው፡፡ ዘመን መለወጫ በሚለው አግባብ ዘመኑ አዲስ እየተባለ ቢጠራም አዲስ መሆን ያለበት ወርና ወቅቱ ብቻ ሳይሆን የእኛ የክርስቲያኖች አኗኗር እንደሆነ ቅዱሳት መጻሕፍት ያስረዳሉ፡፡ ‹‹አሮጌውን ሰውነት ከእናንተ አርቁ፡፡ ልቡናችሁን በእውቀት አድሱ፤ በእውነት፣ በጽድቅና በንጽሕና እግዚአብሔርን ለመምሰል የተፈጠረውን አዲሱን ሰውነት ልበሱ” (ኤፌ. 4÷22-24)፡፡ በዚህ የቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት ያለፈው ዘመን በአሮጌ ሰውነት ተመስሏል፡፡ አሮጌ ሰውነት መገለጫው ደግሞ ኃጢአት፣ መለያየት እንዲሁም በክፋት መቆሸሽ ነው፡፡ አዲሱ ሰውነት ደግሞ መተሳሰብ፣ አንድነት፣ ቅድስናን ገንዘብ ማድረግ መገለጫው ነው፡፡ ስለዚህ በኃጢአት፣ በተንኮል፣ በክፋት የቆሸሸው ሰውነታችን በንስሓ፣ በቅዱስ ቊርባን፣ በመልካም ተግባር አዲስ ካላደረግነው አዲስ ዓመት ብለን ማክበራችን ትርጉም አልባ ይሆንብናል፡፡ ያለፈውን ዓመት ክፋት ወደ አዲሱ ዓመት ለማሻገር መጣር መጨረሻው ውድቀት ነው፡፡ ዘመነ ቅዱስ ማርቆስን ስንቀበል በዘመነ ቅዱስ ማቴዎስ የተከናወኑ መልካም ነገሮች የሚቀጥሉበት እንዲሁም ድካሞች የሚሻሻሉበትና በአዲስ ጥንካሬ የተሻለ መልካም ፍሬ ለማፍራት በጸሎት እንዲሁም በመልካም ሥራ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቼ፡- ዘመነ ቅዱስ ማርቆስ በሀገራችንና በመላው ዓለም ሁሉ ሰላም አንዲሰፍን የምንጸልይበትና በትጋት የምንሠራበት፣ በሀገራችን የተከሰተው ጦርነት ተወግዶ ሰላም የሚሰፍንበት፣ ያለንን ለሌሎች የምናካፍልበት፣ አንድነታችንን የምናጠናክርበት፣ የኮቪድ 19ን ወረርሽኝ በመጸለይና በመጠንቀቅ የምናሸንፍበት ዘመን ያድርግልን፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን አዲሱን ዘመነ ቅዱስ ማርቆስን የሰላም፣ የዕድገትና የጤና ዘመን ያድርግልን፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያን ይባርክ!!!
አባ ዮሴፍ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የሲዳማ ክልል፣ ጌዴኦ ዞን አማሮና
ቡርጂ ወረዳዎች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ፣ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ዘተናገረ በበዓ...
10/09/2021

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ፣ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዐውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወዐርባዕቱ ዓመተ ምሕረት፡፡
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !
- በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትገኙ፤
- ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ፤
- የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
- በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤
- እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ
ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት
ሰማይንና ምድርን፣ በውስጣቸው የሚገኙ ፍጥረታትን የሚታዩትንና የማይታዩትን የፈጠረ እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ከዘመነ ማቴዎስ 2013 ዓመተ ምሕረት ወደ ዘመነ ማርቆስ ወንጌላዊ 2014 ዓመተ ምሕረት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ ፡፡
#ዘይሔድሳ ለምድር በበረከቱ$
‹እግዚአብሔር አምላክ ምድርን በበረከቱ ያድሳታል /ድጓ/›
ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚነግሩን እኛም እንደምንገነዘበው እግዚአብሔር አምላክ በፍጡራን አእምሮ ሊመጠን በማይችል በረከቱ ምድርንና በውስጧ ያሉትን ፍጥረታት ሁሉ በማያቋርጥ ሒደት እያደሰ ይኖራል ፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ፍጥረታት እየታደሱ እንዲተካኩ በማድረጉ የቀደመው ሲያልፍ አዲሱ ሲተካ የሕይወት ጉዞ የማያቋርጥ ሆኖ እንዲቀጥል አድርጎአል ፡፡
ከጌታችን ከአምላካችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በፊት የነበረው አሮጌ ዘመን ዓመተ ፍዳ፣ ዓመተ ኩነኔ በእርሱ መሥዋእትነት ሲያሳልፍ ከልደተ ክርስቶስ ጀምሮ ያለውንም የምሕረት ዘመን ብሎ አድሶታል ፡፡
ወደፊትም በዳግም ምጽአቱ ሰማይንና ምድርን በማሳለፍ የተሻለ ሕይወት ለሰው ልጆች መስጠቱ የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ከቅዱስ ወንጌል ተምረናል፡፡ (ማቴ. 24-25)
በመሆኑም ፍጥረታትን የማሳለፉ ተግባር የእግዚአብሔር ቀዋሚ ሥራ ሆኖ እናገኘዋለን ፡፡
እግዚአብሔር አምላካችን በባህርዩ ማርጀትና ኅልፈት የሌለበት ነው፤ በመጻኢው ዓለም ለሰው ልጆች ያዘጋጀው ሕይወትም ማርጀትና ኅልፈት የሌለበት፣ ሁል ጊዜ ሐዲስ ሆኖ የሚኖር ነው፡፡
የሃይማኖታችን ጽኑ ተስፋም በአዲሱ ዓለም ላይ የተመሠረተ ነው፡፡
ይሁንና ወደ አዲሱ ዓለም ለመድረስ በየዘመኑ አዳዲስ ሥራዎችን በመሥራት እግዚአብሔርንና ፍጡራኑን በትጋት ማገልገል ያስፈለጋል፡፡
በዚህ ዓለም በፍጡራን ዓቅም ሊታደስ የማይችል ነገር ቢኖር ሃይማኖት ብቻ ነው፡፡ ከሃይማኖት በቀር ሌላው ሁሉ ለሰው ልጅ በሚጠቅም መንገድ ሊሻሻል፣ ሊስተካከልና ይበልጥ ሊጠቅም የሚችልበትን ዘዴ ተከትሎ ማሻሻል ተገቢ ይሆናል ፡፡
ዓለም ከተፈጠረ፣ ዘመን ከተቆጠረ አንሥቶ እስካሁን ባለበት ብቻ ቆሞ የኖረበት ዘመን የለም፤ በየጊዜው አዳዲስ የአሠራር ስልቶች እየተፈጠሩ፣ በቀጣይም በሌላ አዲስ ስልት እየተተኩ ይኖራሉ፤ ይህም ቀዋሚ የሆነ የእግዚአብሔር ጸጋ ነው ፡፡
ከዚህ አኳያ በተሰናባቹ በ2013 ዓመተ ምሕረት ማብቂያና በአዲሱ 2014 ዓ.ም. መግቢያ ላይ ቆም ብለን ልናስበው የሚገባ ነገር አለ ፡፡
ይኸውም በተሰናባቹ ዓመት የነበረንን አጠቃለይ ሥጋዊና መንፈሳዊ ተግባር መመርመር ሲሆን ያልሠራንባቸው አጋጣሚዎች ካሉም በአዲሱ ዘመን አካክሰን በመሥራት ያመለጠንን ሁሉ በእጥፍ ሠርቶ ለመተካት ጠንክሮ መሥራት ያስፈለጋል ፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅድስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት፦
አዲሱ ዓመት ሲመጣ የደስታና የተሐድሶ ልቡና ዘመን እንዲሆንልን ከመመኘቱ ጋር በብሩህ ተስፋ መቀበላችን መልካም ነው፤ ይሁንና የሰላምና የእድገት ምኞታችን ወደ ተጨባጭ ፍሬ ሊደርስ የሚችለው በሥራ ብቻ ነው ፡፡
በዓለማችን፣ እንዲሁም በአካባቢያችን የምናያቸው ውብና ድንቅ ነገሮች ሁሉ የሥራ ውጤት መሆናቸውን ለአንድ አፍታ እንኳ ቢሆን ልንዘነጋው አይገባም ፡፡
እግዚአብሔር እኛን የፈጠረ ለሥራ እንጂ እንድንተኛ አይደለም፤ በሥራ ላይ ቸልተኛነትን የምናሳይ ከሆነ ኑሮአችን መመሰቃቀል ብቻ ሳይሆን በእግዚአብሔር ፊት መክሊት ቀባሪ ተብሎ መጠየቅም እንዳለ ማሰብ ይገባናል ፡፡ እንደሚባለውም ‹‹ሰው ለመብላት አይኖርም፤ ለመኖር ይበላል እንጂ፤ እንዲሠራ፡፡››
ለሥራ ክብርን አለመስጠት፣ እግዚአብሔር እኛን የፈጠረበትን ዓላማ እንደመዘንጋት የሚያስቆጥር ይሆናል፤ ይህ ደግሞ ለእኛ የሚበጅ አይደለም ፡፡ (ዘፍ. 1፡3)
እግዚአብሔር ከበረከቱ ያጎደለብን አንዳችም ነገር የለም፤ በየጊዜው አዲስ የሆነ ራዕይ፣ አዲስ የሆነ አሠራር፣ አዲስ የሆነ ጥበብ፣ አዲስ የሆነ ዘመን፣ አዲስ የሆነ ጤንነት ወዘተርፈ ከመስጠት ያቋረጠበት ጊዜ የለም ፡፡
ይሁንና እርሱ የሰጠንን አዲስ የዘመን ስጦታ በአዲስ አስተሳሰብና አሠራር ተቀብለን ካልተጠቀምንበት አዲስ ዘመን ማለቱ ብቻ ከምኞትና ከቃላት ያለፈ ትርጉም ሊኖረው አይችልም፡፡
ዘመኑ አዲስ ሊሆን የሚችለው እኛ በምናበረክተው ሥራ እንጂ ዘመን በራሱ አዲስ ሊሆን አይችልምና እግዚአብሔር አምላክ የሚወዳችሁና እግዚአብሔርን የምትወዱ ልጆቻችንና ወገኖቻችን በሙሉ አዳዲስ ሥራዎችንና አሠራሮችን በመፍጠር አዲሱን ዓመት በሁለመናው አዲስ አድርገን እናክብረው ፡፡
እግዚአብሔር አምላካችን በዓሉን የደስታና የጤና፣ዘመኑን የምሕረትና የሰላም ያድርግልን፡፡ ለሀገራችንና ለመላው ዓለም ሰላምን ይስጥልን፡፡ሕዝባችንን በፍቅርና በአንድነት ያጽናልን፡፡ የተዘራውን ዘር፣ የተተከለውን ተክል ይባርክልን፡፡የተወለዱትን ሕፃናት ያሳድግልን፡፡
መልካም የሥራ ዘመን ያድርግልን !!
እግዚአብሔር አምላካችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ ይቀድስ፤
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም፤
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
መስከረም 1 ቀን 2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ

 #​​ፈታሔ_ማሕፀን+++++++🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼+++++++ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ " የዘለዓለም ሕይወትን እንዲወርሱ ቅዱሳን መላእክት ምእመናን ለመርዳት ለማገልገል ከእግዚአብሔር የሚላኩ ረቂቃን ፍ...
07/09/2021

#​​ፈታሔ_ማሕፀን
+++++++🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼+++++++
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ " የዘለዓለም ሕይወትን እንዲወርሱ ቅዱሳን መላእክት ምእመናን ለመርዳት ለማገልገል ከእግዚአብሔር የሚላኩ ረቂቃን ፍጥረታት አይደሉምን? ( ዕብ ፩÷፲፬) ብሏል። ቅዱስ ዮሐንስም "የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ"( ራእዩ ለዮሐንስ ፰÷፬) በማለት ተናግሯል።

ቅዱሳን መላእክት ያለማያቋረጥ ለፈጣሪያቸው ምስጋና የሚያቀርቡ ረቂቃን ፍጥረታት ናቸው። በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ለተልእኮ ይፋጠናሉ። የሰውን ጸሎትና ልመና ወደ እግዚአብሔር ያደርሳሉ፤ የእግዚአብሔርን ቸርነትና ምሕረት ወደ ሰው አድርሰው በእምነት ያጸናሉ። "በእግዚአብሔርም ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ፥ ሰባትም መለከት ተሰጣቸው" (ራእ. ፰÷፪) የሚለው የሚያስረዳን ለተልእኮ መፋጠናቸውን ነው። ሄኖክም “በሰው ሰውነት ላይ የተሾሙ ከከበሩ ፯ቱ ሊቃነ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል አንዱ ነው” (ሄኖ.፮÷፩-፵፪) ብሏል።

የሰዎችን ልመና ወደ እግዚአብሔር፣ የእግዚአብሔርን ምሕረት እና በረከት ወደ ሰው የሚወርድባት ዕለት"ርኅወተ ሰማይ” ትባላለች። ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት፣ አራተኛው መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት፣ ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ስለሆነች "ርኅወተ ሰማይ-ሰማይ የሚከፈትባት ቀን" ትባላለች። እንዲህ የሚባለው በሰማይ መዘጋት መከፈት ኑሮበት አይደለም። የሰው ልጆችን ልመና ቅዱሳን መላእክት የሚያሳርጉበት፣ አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የጸሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለሆነ እንጂ።

ቅዱስ ሩፋኤል ልቡናን ደስ የሚያሰኝ፣ ባለ መድኃኒት፣ የጸሎት መዝገብ መክፈቻ ቍልፍ የተሰጠው፣ የሴቶችን ማሕጸን የሚፈታና ሳይጨነቁ እንዲወልዱ ምጥን የሚያቀል መልአክ ነው። "ለሰብእ ወለእንሰ ፈታሔ ማሕጸኖሙ አንተ" እንዲል። የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረና ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነትም ከሚያገቡ ከከበሩ መላእክት መካከል አንዱ እኔ ሩፋኤል ነኝ "(ጦቢያ ፲፪÷፲፭) የሚለው የሚያስገነዝበው ተራዳኢነታቸውን፣ ባለሟልነታቸውን፣ አማላጅነታቸውን ነው።

ጸሎትህና ምጽዋትህ በእግዚአብሔር ፊት ለመታሰቢያ እንዲሆን ዐረገ"(ሐዋ. ፲÷፬) የሚለው የመላእክትን አገልግሎት የሚገልጥ ነው። መላእክት ሰዎችን ይራዳሉ፣ የሰውን ጸሎት ያሳርጋሉ፣ ያማልዱሉ፣ ሰዎችን ከመከራ ነጥቀው ያወጣሉ። "የእግዚአብሔርም መልአክ መልሶ። አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ እነዚህን ሰባ ዓመት የተቈጣሃቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተሞች የማትምራቸው እስከ መቼ ነው? አለ፣ እግዚአብሔርም መልሶ ከእኔ ጋር ይነጋገር ለነበረው መልአክ በመልካምና በሚያጽናና ቃል ተናገረው። ስለዚህም ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክ እንዲህ አለኝ። ስበክ እንዲህም በል። የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል (ዘካ፣ ፩÷፲፪÷፲፬) የሚለው አማላጅነታቸውን የሚገልጥ የማጽናኛ ቃል ነው።

ጦቢያና መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ወደ ራጉኤል ቤት በደረሱ ጊዜ ሣራ ተቀብላ ደስ አሰኘቻቸው። መልአኩም ለጦቢያ አባትህ ከዘመዶችህ ወገን አግባ ያለህን ቃል አስብ አለው። ራጉኤልም ልጁ ሣራን ለጦቢያ አጋባት። ተመግበውም ከጨረሱ በኋላ ጦቢያን ወደ እርሷ አገቡት፤ ወደ እርሷም በገባ ጊዜ የመልአኩ የቅዱስ ሩፋኤልን ነገር አሰበ፤ የዕጣን እራሪ ወሰደ፤ ከዚያም ዓሣ ከልቡና ከጉበቱ ጨምሮ አጤሰው። ሽታውም ያን ጋኔን በሸተተው ጊዜ እስከ ላይኛው ግብፅ አውራጃ ድረስ ሸሸ። መልአኩም ጋኔኑን አሰረው( ጦቢ ፰÷፩) የተባለው የሚያስረዳን የመላእክትን ተራዳኢነት ነው።

ጦቢያ የሰርጉን በዓል በጨረሰ ጊዜ ወደ አባቱ ቤት ከሚስቱ ከሣራና ከመልአኩ ከቅዱስ ሩፋኤል ጋር ተመለሱ። ሩፋኤልም አለው፥ "ያባትህ ዐይኖች እንዲበሩ አውቃለሁ፤ አንተ ግን ያን ሐሞት ያባትህ ዓይን ኳለው፤ በተኳለም ጊዜ ብልዙ ከአይኑ ይወጣል በደህናም ያያል። ጦቢያም የአባቱን አይን ኳለው ዓይኑም በራለት”( ጦቢ ፲፩÷፮) ተብሎ እንደተነገረው እግዚአብሔር ከዚህ ክፉ ወረርሽኝ ጠብቆን በሰላም በጤንነት ለሚመጣው ዓመት ያድርሰን። የጦቢትን ዓይን ያበራውን የቅዱስ ሩፋኤልን ዓመታዊ በዓል አክብረን በረከት ለማግኘት ያብቃን።አሜን!!

© ዲ/ን ተመስገን ዘገየ

06/09/2021

🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼

የጳጉሜን ወር ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበት ወር ነው በቅድስት ቤተክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ በዚህ በጳጉሜ ወር የምንጾመው የፈቃድ ጾም ነው፡፡

ጳጉሜን ማለት ጭማሪ ማለት ነው፡፡ ይህም በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን የምትመጣ ናት፡፡ በአራት ዓመት አንዴ ማለትም በዘመነ ሉቃስ ጳጉሜን ስድስት ቀን ይሆናል፡፡ በዚህም ሐገራችን ኢትዮጵያ የአስራ ሦስት ወራት ጸጋ /Thirty months of sunshine/ በመባል ትታወቃች ትለያለች፡፡ ጳጉሜን በዘመነ ዮሐንስ መግቢያ በዘመነ ሉቃስ ማብቂያ ስድስት በምትሆንበት ጊዜ ጾመ ነቢያት /የገና ጾም/ ህዳር 15 ቀን ይገባና ታህሳስ 28 ቀን ጾሙ ተፈቶ የልደት በዓል ይከበራል፡፡

በቅድስት ቤተክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ በዚህ በጳጉሜን ወር የምንጾመው የፈቃድ ጾም ነው፡፡ ይህም ጾመ ዮዲት በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ግን እንደ አንደኛው የፈቃድ ጾም /ጽጌ ጾም/ በብዙዋኑ ዘንድ የታወቀ አይደለም፡፡ የዮዲት ጾም የሚባለውም እርሷ ስለ ጾመችው ነው፡፡ እዚህ ላይ ዮዲት ተብላ የተጠቀሰችው በቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት ላይ በጥፋት ሥራዋ በተደጋጋሚ የምትጠቀሰው ዮዲት ጉዲት እንዳልሆነች ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ ወደ ታሪኩ ስንመለስ የፋርስ ንጉስ ናቡከደነጾር በሠራዊቱ ተመክቶ ሹም ጠላት አጥፋ ድንበር አስፋ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበልህ ያላመነውን እያሳመንህ ና ብሎ ለጦር አበጋዙ ለሆሎፎርኒስ ትዕዛዝ ሰጠ፡፡ ዮዲ 2፥2-7፡፡ እርሱም እንደታዘዘው በኃይላቸው የታመኑ 12ሺህ እግረኞችንና በፈረስ የተቀመጡ 12ሺህ ጦረኞችን እየመራ ዘምቶ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበለ ያላመነውን እያሳመነ ብዙ ሀገሮችን እያጠፋ ሲሔድ ከአይሁድ ከተማ ደረሰ በዚህም ብዙ ጥፋ በመድረሱ የእስራኤል ልጆች አለቀሱ፡፡ ዮዲት ባሏ ሞቶባት ከወንድ ርቃ ንጽሕናዋን ጠብቃ በጾም በቀኖና በሀዘን ተወስና ትኖራለች በተፈጠረው ጥፋት ህዝቡ ላይ ለመጣው መከራ ማቅ ለብሳ በራስዋ ላይ ትብያ ነስንሳ ወደ እግዚአብሔር አለቀሰች፡፡

የፍጥረቱን ጥፋት የማይሻ እግዚአብሔር አምላክም ሕዝቡን የሚያድኑበትን መንገድ ለመጠየቅ ሱባኤ በገባች በሦስተኛው ቀን ገለፀላት፡፡ ዮዲ 8፥2፡፡ ከዚህ በኋላ ጠላታቸውን በዮዲት ምክንያት እስራኤላውያን እስከ ዮርዳኖስ እየተከተሉ አጥፍተዋቸዋል፡፡ ዮዲት ጠላቷን ለማጥፋት የቻለችው በጾምና በጸሎት ከእግዚአብሔር አምላክ ኃይል አግኝታ ነው፡፡ ስለዚህ ምዕመናን ጥንተ ጠላታችን ሰይጣንን ፈቃደ ሥጋን ለማሸነፍ በጾም ከፈጣሪያችን ኃይልን መጎናጸፍ አለብን ብለው ጳጉሜን በፈቃድ ይጾማሉ፡፡

የጳጉሜን ወር ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበትም ወር ነው፡፡ ይህም ጳጉሜ የዓመታት መሸጋገሪያ ጨለማው የክረምት ወቅት ወደ ማብቂያው የምናልፍባት እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ነውና ነው፡፡

+++++++የበረከት ጾም ያድርግልን+++++++

06/09/2021

እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችኁ፡፡ አደረሰን። ጳጉሜን ሦስት ቀን የሚከበረውን የሊቀመላእክት የቅዱስ ሩፋኤል የሌሊት ሥርዓተ ማህሌት፣ ወረብ እና ዚቅ እንዲህ ለማዘጋጀት ተሞክሯልና ቀጸል ቀጸል አድርጋችኁ ሌሊት ማኅሌቱ ላይ ተገኙ።

መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለመታክፍቲክሙ መሠረተ ዓለም እለፆሩ፣
ኖትያተ ኖኅ ሥላሴ ወዕፀወ ዐባይ ሐመሩ፣
ዲበ መንበርክሙ ሰብአ ሶበ አምላክ ነጸሩ፣
ኪሩቤል ወሱራፌል ታህተ እገሪሁ ገረሩ፣
እስመ ለሊሁ አዘዘ ወእሉ ተፈጥሩ፡፡

ዚቅ
እሉ ኪሩቤል ወሱራፌል የዐርጉ ሎቱ ስብሐተ እንዘ ይብሉ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ አንተ እግዚአብሔር አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ።

ነግስ
ሰላም ለክሙ ሚካኤል ወገብርኤል፣
ሱራፌል ወኪሩቤል፣ ዑራኤል ወሩፋኤል፣ ሱርያል ወፋኑኤል፣ አፍኒን ወራጉኤል ወሳቁኤል፣
ሊቃናተ ነድ፣ ዘሰማያዊት ማኅፈድ፣
በዕንተ በግዑ ዕቀብዋ ለዛቲ አፀድ፡፡

ወረብ
ለዛቲ አፀድ በእንተ በግዑ ዕቀብዋ ለዛቲ አፀድ፣
ሊቃናተ ነድ ሊቃናተ ነድ ነድ ሊቃናተ ነድ።

ዚቅ
መላእክተ ምሕረት እለ ድልዋን ለሣህል ሰአሉ አስተምሕሩ ለነ እስመ በጸሎተ ትንብልናክሙ ትድኅን ወኢትማስን ሀገር።

መልክአ ሚካኤል
ሰላም ለአእናፊከ መዓዛ አርያም እለ ተመልዑ፣
ሱራፌል ምስሌከ ጊዜ ይሠውዑ፣
ሚካኤል አንተ ለያዕቆብ ኖላዊ ዘርዑ፣
በሎሙ ለአብያጺከ ለሐውፆ አርክየ ንዑ፣
እስመ በአሐዱ ፍቁር ይሰሐብ ካልዑ፡፡

ዚቅ
እኲት ወስቡሕ፣ ዕቀብ ኩልነ ኖላዊ ትጉህ፣ ሐውፀነ በምህረት ብዙኅ።

ወረብ
ኖላዊ ትጉህ ኖላዊ ትጉህ፣
ሐውፀነ በምህረት ብዙኅ።

ነግሥ
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፣
ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፣
መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፣
ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፣
እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኰት ስሙ፡፡

ዚቅ
መላእክት በልሳነ እሳት ይሴብሑኪ፣ መላእክት በአክናፈ ብርሃን ይኬልሉኪ፣ ማርያም እምነ፣ ወእሙ ለእግዚእነ፣ መላእክት በቀለመ ወርቅ ይጽሕፉ ውዳሴኪ፣ እስከ ዳግም ምጽአቱ ለበኲርኪ።

ወረብ
እሳት በአክናፈ እሳት ይኬልሉኪ ማርያም፣
መላእክት በቀለመ ወርቅ ይጽሕፉ ውዳሴኪ።

መልክአ ሩፋኤል
ሰላም ለዝክረ ስምከ ተጸውዖ ዘቀደመ፣
በአፈ አምላክ አዳም እንበለ ይሰመይ ስመ፣
ሩፋኤል ምልዓኒ ወወስከኒ ዳግመ፣
መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ ፣
ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡

ዚቅ
ሀበነ እግዚኦ አዕይንተ አእምሮ ወትረ ኪያከ ይርአያ፡ ወአዕዛንነሂ ቃለ ዘባሕቲትከ ይስምዓ።

ወረብ
ሀበነ እግዚኦ አእምሮ አዕይንተ አእምሮ ወትረ ኪያከ ይርአያ፣
ወአዕዛንነሂ ቃለ ዘባሕቲትከ ይስምዓ።

መልክአ ሩፋኤል
ሰላም ለቃልከ ዘይደምፅ እመብረቅ፣
ለእስትንፋስከኒ እስትንፋሰ መንፈስ ረቂቅ፣
ሩፋኤል ሐዋርያ ወመልአከ ጽድቅ፣
ይጸንሑከ እግዚኦ ዕሡራነ በዓል በጻሕቅ፣
ነዓ ነዓ እምሕላዌከ ምጡቅ፣
ውስተ ቤትከ ዛቲ ክርስቶሳዊት ምርፋቅ፡፡

አመላለስ
ሩፋኤል ሐዋርያ ወመልአከ ጽድቅ።

ዚቅ
ሩፋኤል ግሩም፣ በመንፈስ ቅዱስ ሕቱም፣ መዓዛ ቅዳሴከ ጥዑም፣ ከመ ጽጌ ገዳም፣ ነዓ ነዓ ማዕከሌነ ቁም፣ በበዓልከ ባርከነ ዮም።

ወረብ
ነዐ ነዐ ማዕከሌነ ቁም፣
በበዓልከ ባርከነ ዮም።

መልክአ ሩፋኤል
ሰላም ለገበዋቲከ ስርግዋነ ምንትው አክናፍ፣
ለከርሥከሂ ሕሩመ ሲሲት ዘዘልፍ፣
ሩፋኤል አሐዱ ሊቀ አዕላፍ፣
አብሥረኒ ነገረ ሣህል ለወልደ ላሜህ ፍልሱፍ፣
ከመ ሕጸተ ማይ አብሠረቶ የዋሂት ዖፍ፡፡

አመላለስ
ሩፋኤል አሐዱ ሊቀ አእላፍ።

ዚቅ
ውእቱ ሊቆሙ ወመልአኮሙ፣ ሩፋኤል ስሙ፣ ዐይኑ ዘርግብ ልብሱ ዘመብረቅ ሐመልማለ ወርቅ።

ወረብ
ውእቱ ሊቆሙ ወመልአኮሙ ስሙ ሩፋኤል፣
ሐመልማለ ወርቅ ልብሱ ዘመብረቅ ዐይኑ ዘርግብ ሊቀ መላእክት።

መልክአ ሩፋኤል
ተወኪፈከ እግዚኦ ዘንተ አምኃየ፣
ዘአቅረብኩ ለከ መጠነ ክሂል ዘብየ፣
ሩፋኤል ባዕል እንተ ታብዕል ነዳየ፣
ዕስየኒ ለፍቁርከ ዕሤተ ሠናየ፣
ዘዕዝነ መዋቲ ኢሰምዐ ወዘዐይን ኢርእየ፡፡

ዚቅ
ወሰሚአ ሀገር ከልሃት ሎቱ ወትቤ ተወከፈኒ አንተ መልአክ ቅዱስ ገብረ እግዚአብሔር።

ወረብ
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር፣
ገብረ እግዚአብሔር ተወከፈኒ አንተ መልአክ።

አስመ ለዓለም
ዑራኤል ወሩፋኤል፣ አስተምሕሩ ለነ በስኢል፣ ወበትህትና ኀበ ውእቱ ነበልባል፣ ኃይል አመ ይመጽእ በክብር፣ ምስለ ብዙኅ ስብሐት ወኃይል፣ ንርከብ ድኅነተ በዘአሜሃ ቀመር፣ በዐውዱ ፍጹም ዘኢይትነገር፣ ንዕርር ፍሥሐ በሐዳስ ምድር።

ወረብ
ዑራኤል ወሩፋኤል፣
አስተምሕሩ ለነ በስኢል ወበትህትና ኀበ ውእቱ ነበልባል።

አንገርጋሪ
ሃሌ ሉያ ይሰግዱ በብረኪሆሙ፡ ወያሌዕሉ ኅሊናሆሙ፡ በጥንቃቄ ወበኃሢሥ፡ ኀበ እግዚኦሙ ንጉሥ፡ ቀዋምያን ለነፍሳት፡ እሙንቱ ሊቃናት፡ ዑራኤል ወሩፋኤል፡ ይትፌነዉ ለሣህል፡ እምኀበ ልዑል።

ወረብ
ቀዋምያን ለነፍሳት እሙንቱ ሊቃናት ዑራኤል ወሩፋኤል፣
አስተምሕሩ ለነ በስኢል ወበትህትና ኀበ ጽርሐአርያም እምልዑል።

ከመልአኩ ረድኤት፣ ምልጃና በረከት ያድለን። አሜን ወአሜን። መልካም በዓል።

05/09/2021

ጳጉሜን በዓለ ቅዱስ ሩፋኤል ሥርዓተ ዋዜማ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

ሃሌ ሉያ ትጉሃን እለ ኢይነውሙ መላእክት በበስርአቶሙ፤ ሱራፌል በግርማሆሙ፤ ወኪሩቤል በውዳሴሆሙ፤ ኪያከ አበ ይሴብሑ፤ ኪያከ ረዳዔ ኪያከ መጋቤ፤ ስቡሕ በውስተ ቅዱሳን
አመላለስ፦
ኪያከ ረዳዔ ኪያከ መጋቤ/2/
ስቡዕ በውስተ ቅዱሳን/4/

ለእግዚአብሔር ምድር በምላዕ፦
ትጉሃን እለ ኢይነውሙ መላእክት በበስርአቶሙ ትጉሃን እለ ኢይነውሙ

እግዚአብሔር ነግሰ፦
ይቤሎ ለጦቢያ አነ ውእቱ ሩፋኤል መልአክ አሀዱ እም ተስአቱ ሊቃነ መላእክት ዘተፈኖኩ ኀበ ጦቢት

ይትባረክ፦
ትጉሃን እለ ኢይነውሙ መላእክት በበስርአቶሙ ኪያከ አበ ይሴብሑ

ሰለስት፦
ትጉሃን እለ ኢይነውሙ መላእክት በበስርአቶሙ፤ ሱራፌል በግርማሆሙ፤ ወኪሩቤል በውዳሴሆሙ፤ ኪያከ አበ ይሴብሑ

ሰላም፦
በ 4 ሃሌታ-
ጥበበ ኩሉ ኃይል ለኩሉ ወብዙኃ ሣህል ንስእል ወናስተበቁዕ ኪያከ መጋቤ ኩሉ ከመ ተሀበነ ተምኔተነ በሰላም ንፈጽም ንብረተነ ንጉሠ ሠራዊተ ሰማያት ዘዲቤሆሙ የዓርፍ በበማኅበሮሙ ኪያከ ይሴብሑ ስብሐት ለከ የዓርጉ

አመላለስ፦
በበማኅበሮሙ ኪያከ ይሴብሑ/2/
ስብሐት ለከ የዓርጉ/4/

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ  በህንድ ማላንካራን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ዕረፍት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለፁ !!!ቅዱስነታቸው በዛሬው ዕለት ለሕንድ ማላን...
13/07/2021

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ በህንድ ማላንካራን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ዕረፍት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለፁ !!!

ቅዱስነታቸው በዛሬው ዕለት ለሕንድ ማላንካራ ኦርቶዶክስ ሶርያዊ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጻፉት ደብዳቤ በቅዱስ ቶማስ ፣ በማላንካ ሜትሮፖሊታን እና በሕንድ ኦርቶዶክስ ማላንካራ ቤተ ክርስቲያን የበላይ አካል ሐዋርያዊ ዙፋን ላይ የተሾሙት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ማርቶማ ጳውሎስ ዳግማዊ ዕረፍታቸውን የሰማነው ሀዘን ነው ሲሉ ገልፀዋል።

ለቅዱስ ሲኖዶስ ፣ ለህንድ እህታችን ማላንካራን ኦርቶዶክስ ሶርያዊ ቤተክርስትያንአማኞች ሁሉ የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ እና በራሴ ስም እገልፃለሁ ብለዋል ቅዱስነታቸው።

ቅዱስነታቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አማኞችን ለ3 ገዜያት ጎብኝተው ባርከዋል ለሀገራችን ኢትዮጵያ ያላቸውንም እውነተኛ ፍቅር በጥልቀት የሚያሳይ ጉብኝት ነው ብለዋል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

በቅዱስ ባስልዮስ ማርቶማ ጳውሎስ ዳግማዊ ሐዋርያዊ ጉብኝቶቻቸው ወቅት ኢትዮጵያዊያን ምእመናን ቅዱስነታቸውንም በደስታ ተቀብለዋል በረከታቸውንም በርካቶች ተቀብለዋል ያሉ ሲሆን በተለይም በመስከረም ወር 2017 (እ.ኤ.አ) በቅዱስ መስቀሉ በዓል ላይ ነውተገኝተው በዓሉን ያከበሩ መሆኑ እና በአጠቃላይ መንፈሳዊ አገልግሎታቸው ቅዱስነታቸው ሁልጊዜም ከልባችን አይጠፉም ሲሉ ገልፀዋል።

12/07/2021

✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

❖ ሐምሌ ፭ ❖

✞✞✞✝ እንኩዋን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን #ዼጥሮስ #ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞✝

=>ፍጡር ቢከብር ከእመ ብርሃን ቀጥሎ የእነዚህን ቅዱሳን ያህል የሚከብር አይኖርም:: ለቤተ ክርስቲያን ያልሆኑላት ምንም ነገር የለምና እርሷም "ብርሃኖቼ: ዐይኖቼ: ዕንቁዎቼ" ብላ ትጠራቸዋለች::

+" ✝ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት✝ "+

=>የዮና ልጅ ስምዖን ዼጥሮስ (ኬፋ) የተባለው በጌታችን ንጹሕ አንደበት ነው:: ይሔውም ዓለት (መሰረት) እንደ ማለት ነው::

¤በቤተ ሳይዳ ከወንድሙ እንድርያስ ጋር ዓሳ በማጥመድ አድጐ

¤ሚስት አግብቶ ዕድሜው 56 ሲደርስ ነበር ጌታችን የተቀበለው:: በዕድሜውም ሆነ በቅንዐቱ: በአስተዋይነቱም መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ተብሏል:: ለሐዋርያትም አለቃቸው ሆኗል:: (ማቴ. 16:17, ዮሐ. 21:15)

+ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተያዘባት ሌሊት ለሰራው ስሕተት ንስሃ ገብቶ ምሳሌም ሆኗል:: ቅዱስ ዼጥሮስ እንደ እረኝነቱ ሐዋርያትን ጠብቆ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሲያበቃ ከበዓለ ሃምሳ በሁዋላም ለሁሉም ሃገረ ስብከት አካፍሏል:: ምንም የርሱ ክፍል ሮሜ ብትሆንም አርድእትን ስለ ማጽናት በሁሉም አሕጉራት ዙሯል::

+በስተእርጅናው ብዙ መከራዎችን ተቀብሏል:: አሕዛብ ግብራቸው እንደ እንስሳ ነውና በአባታችን ላይ ቀልደዋል::
እርሱ ግን ሁሉንም ታግሷል:: የቅዱሱን ታሪክ ለመናገር ከመብዛቱ የተነሳ ይከብዳልና ልቡና ያለው ሰው ሊቃውንትን ሊጠይቅ እንደሚገባ እመክራለሁ::

+ቅዱስ ዼጥሮስ መልካሙን ገድል ተጋድሎ በ66 ዓ/ም የኔሮን ቄሳር ወታደሮች ሲሰቅሉት ለመናቸው::
"እባካችሁን? እኔ እንደ ጌታየ ሆኜ መሰቀል አይገባኝም" አላቸው:: እነሱም ዘቅዝቀው ሰቅለው ገድለውታል:: በበጐ እረኝነቱም የማታልፈውን ርስት ከነመክፈቻዋ ተቀብሏል:: በሰማዕትነት ሲያርፍም ዕድሜው ወደ 88 አካባብ ደርሶ
ነበር::

✝=> መጠሪያዎች:-✝

1.ሊቀ ሐዋርያት
2.ሊቀ ኖሎት (የእረኞች / ሐዋርያት አለቃ)
3.መሠረተ ቤተ ክርስቲያን
4.ኰኩሐ ሃይማኖት (የሃይማኖት ዐለት)
5.አርሳይሮስ (የዓለም ሁሉ ፓትርያርክ)

+"+✝ ✝+"+

=>የቤተ ክርስቲያን መብራቷ ቅዱስ ዻውሎስን እንደ ምን ባለ ዐማርኛ እንገልጠዋለን?
¤ስለ እርሱ መናገርና መጻፍ የሚችልስ እንደ ምን ያለ ሰው ነው?
¤የዓለምን ነገር ሲጽፍ በኖረ እጄስ እንደ ምን
እጽፈዋለሁ?
¤ይልቁኑስ የርሱን 14ቱን መልዕክታትና ግብረ ሐዋርያትን መመልከቱ ሳይሻል አይቀርም::

+ ከነገደ ብንያም #ሳውል የሚባል የጠርሴስ ሰው ሲሆን ምሑረ ኦሪት: ቀናተኛና ፈሪሳዊ ነበር:: ጌታ በደማስቆ ጐዳና ጠርቶ በ3 ቀናት ልዩነት ምርጥ ዕቃ አደረገው:: ይህ የሆነው በ42 ዓ/ም: ጌታ ባረገ በ8ኛው ዓመት ነበር:: ከዚያማ ብርሃን ሆኖ አበራ:: ጨው ሆኖ አጣፈጠ::

+ከኢየሩሳሌም እስከ ሮም: ከእንግሊዝ እስከ እልዋሪቆን (የዓለም መጨረሻ) ወንጌልን ሰበከ:: ስለ ወንጌል ተደበደበ: ታሠረ: በእሳት ተቃጠለ:: በድንጋይ ተወገረ: በጦር ተወጋ:: ባፍም በመጣፍም ብሎ አገለገለ:: በየቦታውም ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ሠራ:: ለ25 ዓመታት ቀንና ሌሊት ያለ መታከት ወንጌልን ሰበከ::

+እርሱን የመሰሉ: እርሱንም ያከሉ ብዙ አርድእትን አፍርቶ: በ67 ዓ/ም በኔሮን ቄሳር ትእዛዝ አንገቱ ተቆርጧል:: ከ14ቱ መልዕክታቱ ባሻገር ቅዱስ ሉቃስ ወንጌልን ሲጽፍ አግዞታል:: ልክ ቅዱስ ዼጥሮስ ማርቆስን እንዳገዘው ማለት ነው::

=✝>የቅዱስ ዻውሎስ መጠሪያዎች:-✝

1.ሳውል (ከእግዚአብሔር የተሰጠ)
2. (አንደበቱ እንደ ሽቱ የሚጣፍጥ)
3. (የክርስቶስ አንደበቱ)
4.
5. (የቤተ ክርስቲያን መቅረዝ)
6.
7. #መራሒ (ወደ መንግስተ ሰማያት የሚመራ)
8. #አእኩዋቲ (በምስጋና የተሞላ)
9. (ምርጥ ዕቃ)
10. #መዶሻ (ለአጋንንትና መናፍቃን)
11. #መርስ (ወደብ)
12. #ዛኅን (ጸጥታ)
13. (የሕይወት ትምሕርትን ከአንደበቱ ያፈለቀ)
14. (የጥበብ ምንጭ / ባሕር)
15. (ድውያንን የፈወሰ) . . .

ጌታችን እግዚአብሔር የአባቶቻችንን ብርሃን ያብራልን:: ከበረከታቸውም ያድለን::

"+ ጌታ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው:: የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ! በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይሕንን አልገለጠልህምና ብጹዕ ነህ:: እኔም እልሃለሁ:: አንተ #ዼጥሮስ ነህ:: በዚህችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ:: የገሃነም ደጆችም አይችሏትም:: የመንግስተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ:: በምድር የምታሥረው ሁሉ በሰማያት የታሠረ ይሆናል:: በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል::" +"+ (ማቴ. 16:17)

"+ በመሥዋዕት እንደሚደረግ የእኔ ሕይወት
ይሠዋልና:: የምሔድበትም ጊዜ ደርሷል:: መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ:: ሩጫውን ጨርሻለሁ:: ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ:: ወደ ፊት ተዘጋጅቶልኛል:: ይሕንም ጻድቅ: ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል:: +" (2ጢሞ. 4:6)

>

© ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ

ሥርዓተ ማኅሌት ዘሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ +++++++++++ሐምሌ ፭+++++++++++ # ስቡህ ሥርዓተ ነግሥ:-ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉ...
11/07/2021

ሥርዓተ ማኅሌት ዘሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
+++++++++++ሐምሌ ፭+++++++++++
# ስቡህ
ሥርዓተ ነግሥ:-
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።

መልክዐ ሥላሴ
ሰላም ለቃልክሙ መታሬ እሳት ነዳዲ: ሥሉስ ቅዱስ ንዋያተ ዕፁብ ነጋዲ: አመ በንስሐ ተወልዱ እምጸጋክሙ ወላዲ: ተወፈየ መርኆ ሰማይ የማነ #ጴጥሮስ ከሐዲ: ወመምህረ ወንጌል ኮነ ጳውሎስ ሰዳዲ።

ዚቅ
ጸጋ ዘአብ ኂሩት ዘወልድ: ሱታፌ ዘመንፈስ ቅዱስ: ተውህቦሙ ለሐዋርያት።

ነግሥ
ሰላም ለመልክዕክሙ እመልክዐ አዳም ዘተቶስሐ: እግዚአብሔር መሐሪ ዘኮነክሙ መርሐ: ፲ወ፪ እለ ሰበክሙ ቃለ ንስሐ: ሥረዩ ኃጢአትየ ወጌጋይየ ብዙኀ: በእንተ ማርያም ድንግል በህሊናሃ ወድንግል በሥጋሃ።

ዚቅ
ሐዋርያተ ሰላም ክቡራነ ስም: ሥረዩ ኃጢአተ ዓለም: በእንተ ኢየሱስ ክርስቶስ ወበእንተ ድንግል እም።

መልክዐ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
ሰላም ለመቃብሪከ በመካነ ሐዋዝ ሃሌሉያ፡
ወለትንሣኤከ ድኅረ ዘይከውን በዕለተ ምርያ፡
ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሞተከ ታብዕል ኢትዮጵያ፡
ለጴጥሮስ በዓለ መርኆ ወለጳውሎስ ሐዋርያ፡
ከመ ተዝካሮሙ ታብዕል ሮምያ።

ዚቅ
ንግበር ተዝካሮሙ ለእለ ኃረዮሙ ዓጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ።

መልክዐ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
ሰላም ለዝክረ ስምክሙ ዘአልባስጥሮስ አፈው: ወለሥዕርትክሙ ጸሊም ዘድላሌሁ ፍትው: ምቱረ ክሣድ #ጳውሎስ #ወጴጥሮስ ቅንው: ተራወጸ ውስተ ልብየ ምስል መዓዛሁ ቅድው: ደመ ስምክሙ ሐዋርያ ዘኅብሩ ከዋው።

ዚቅ
ሃሌ ሉያ: ከዋው እገሪሆሙ: ለእለ ይዜንዉ ዜና ሠናየ: ዘእግዚአብሔር ፈነዎ: ቃለ እግዚአብሔር ይነግር።

አመላለስ
ሃሌ ሉያ/፪/
ከዋው እገሪሆሙ/፪/

ወረብ
ከዋው እገሪሆሙ ለእለ ይዜንዉ ዜና ሠናየ ለእለ ይዜንዉ/፪/
ዘእግዚአብሔር ፈነዎ ይነግር ቃለ እግዚአብሔር/፪/

መልክዐ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
ሰላም ለአዕዛኒክሙ ለሰሚዓ ወንጌል ዘተሰብሐ: ወለመላትሒክሙ ቀይሐት እምነ ሮማን ዘቄሃ: መሥዋዕተ አምልኮት ኩኑ ወዘመሃይምናን ምክሐ: ደምከ #ጴጥሮስ ወልደ ዮና በጽዋዓ መስቀል ተቀድሐ: ወደመ #ጳውሎስ ሐዋርያ ሰማያተ ጸርሐ።

ዚቅ
ኢየሩሳሌም ኢየሩሳሌም እንተ ትቀትሎሙ ለነቢያቲሃ: ወትዌግሮሙ ለሐዋርያቲሃ: ሚ መጠን ዘተክዕወ ዲቤሃ: እምደመ #ጳውሎስ ሐዋርያ: እስከ ደመ #ጴጥሮስ ወልደ ዮና።

ዓዲ
እግዚአብሔር : እንተ ተሰመይኪ ገነተ: ደሞሙ ለሰማዕታትኪ ውኅዘ ከመ ማይ: ድምፀ ነጎድጓዶሙ በጽሐ እስከ ሰማይ።

ወረብ
ሚ መጠን ዘተክዕወ ዲቤሃ ለኢየሩሳሌም/፪/
እምደመ #ጳውሎስ ሐዋርያ እስከ ደመ #ጴጥሮስ ወልደ/፪/

መልክዐ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
ሰላም ለዘባናቲክሙ በምኲራባት እለ ተቀሥፋ: ወለእንግድዓክሙ ዘሰፍሐ መልዕልተ ጠበብት ወፈላስፋ: በእንተ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘተጸፍአ ቅድመ ቀያፋ: ሀበኒ #ጴጥሮስ መስቀለከ ይኲነኒ ተስፋ: #ወጳውሎስ ዉቅየተከ እንተ ደም ለከፋ።

ዚቅ
እስመ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ: ዘተሠውጠ ላዕለ ኲሎሙ ሐዋርያት: በመንፈስ ቅዱስ ነበቡ በነገረ ኲሉ በሐውርት: ይኲነኒ አክሊለ መዊዕ ወተስፋ: በረከቶሙ ለሳውል ወኬፋ።

ወረብ
እስመ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ዘተሰውጠ ላዕለ ሐዋርያት/፪/
በመንፈስ ቅዱስ ነበቡ በነገረ ኲሉ በሐውርት/፪/

መልክዐ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
ሰላም ዕብል ብርሃናተ ፪ኤተ: በዓውደ ንጉሥ ኔሮን እለ ፈጸሙ ሩጸተ: #ጳውሎስ #ወጴጥሮስ ዘያጸንዑ ፀበርተ: አሐዱ በመስቀል ተሰቅለ ቊልቊሊተ: ወካልዑ ተመትረ ክሣዱ ክብርተ።

ዚቅ
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ: ብርሃናተ ዓለም ሐዋርያተ ሰላም ሱቱፋነ ሕማም: አሥራበ ምሕረት ከዓዉ እምአርያም።

ወረብ
ሐዋርያተ ሰላም "ብርሃናተ ዓለም"/፪/
አሥራበ ምሕረት ከዓዉ ከዓዉ እምአርያም/፪/

መልክዐ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
ተዘኪረከ ክርስቶስ ዘሐዋርያት ኲሎሙ: ህየንተ ክቡር ደምከ እለ ከዓዉ ደሞሙ: አክሊለ ስምዕ ሀበኒ ከመ እሳተፍ ገድሎሙ: ወደምስስ ለአጽራርየ እመጽሐፈ ህይወት ዝክሮሙ: ከመ ለይሁዳ ረሲዕ ተደምሰሰ ስሙ።

ዚቅ
#ስምዖን #ጴጥሮስ ወአኃዊሁ ሱቱፋነ ሕማምከ: እለ ከዓዉ ደሞሙ ህየንተ ደምከ: ከመ ይኩን ተውሳከ ለሴጠ አሕዛብ በስብከተ ወንጌልከ: በከመ ተቶስሐ መዓዛ ክህነትከ በክህነቶሙ: ቶስሕ ስእለተነ በስእለቶሙ: ጸግወነ ሎሙ ከመ ንድኃን ቦሙ።

ወረብ
#ስምዖን #ጴጥሮስ ወአኃዊሁ "ሱቱፋነ ሕማምከ"/፪//፪/
እለ ከዓዉ ደሞሙ ደሞሙ ህየንተ ደምከ/፪/

መልክዐ ኢየሱስ
ሰላም ለእራኅከ መክፈልተ ሕማማት ሱቱፍ: ወቅንዋቲሁ እኤምሕ በአፍ: በላዕለ ቅዱሳን ዕሩፍ: ይፀነስ ውስተ ከርሥየ ዘርአ ቃልከ መጽሐፍ: ጸዳለ እምጸዳል ከመ ትፀንስ ዖፍ።

ዚቅ
እግዚአ ውእቱ ለሰንበት ውእቱ: አቡሃ ለምሕረት ውእቱ: ኃያል ወብዙኅ ሣህል ውእቱ: ዘባሕቲቱ በቅዱሳኒሁ ዕሩፍ።

ምልጣን
ይቤሎ #ጴጥሮስ #ለጳውሎስ ጥባዕኬ እኁየ #ጳውሎስ ወኢትናፍቅ እምዝ ዳግመ ኢንመውት ዳግመ ወእምዝ ዳግመ ኢንመውት።

ወረብ
ይቤሎ ጴጥሮስ ለጳውሎስ ጥባዕኬ እኁየ ጳውሎስ እኁየ/፪/
ወኢትናፍቅ ዳግመ እምዝ ዳግመ ኢንመውት/፪/

እስመ ለዓለም
ሕዝብ ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡራን: አርድዕት ልዑላን አዕማደ ቤተክርስቲያን: ሰመየ ስሞሙ ደቂቀ ብርሃን #ጴጥሮስ #ወጳውሎስ: ወኲሎሙ ሐዋርያት: ፈድፋደ ቦሙ ሞገሰ በኀበ ኲሎሙ ሕዝብ።

አመላለስ
ሕዝበ ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡራን አዕማደ ቤተክርስቲያን/፪/
ሰመየ ስሞሙ ደቂቀ ብርሃን ጴጥሮስ ወጳውሎስ/፪/

Address

Awassa
ቅዱስሩፋኤልቤተክርስቲያን

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hawassa Saint Rufael Sunday School-የሀዋሳ ደብረ ታቦር ቅዱስ ሩፋኤል ሰንበት ትምህርት ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share