22/04/2023
የእግዚአብሄርን ቃል ስንመለከት በቃሌ ኑሩ ይላል፤ በሌላ ስፍራ ደግሞ በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ለምኑ ይሆንላችኋል ይላል፡፡ (ዮሀ8፤31-32፣ ዮሀ15፤7)
በመሰረቱ የእግዚአብሄር ቃል በህይወቱ ውስጥ ያለ ሰው የሚወደውና የሚመኘው የእግዚአብሄርን ፈቃድ ማድረግ እና እግዚአብሄርን ማክበር ብቻ ነው፡፡ (1ነገ3፤4-14)
ምክንያቱም የእግዚአብሄር ቃል ፡-
ለራሱ እንዳይኖር ገድሎታል፡፡ (2ቆሮ5፤14-15፣ ዕብ4፤12)
ለእግዚአብሄር ፈቃድ እንዲኖር አድርጎታል፡፡ (ኤር1፤9-10)
የእግዚአብሄርን ፈቃድ እንዲያውቅና እንዲፈፅም ብርሃንና ሀይል ሆኖታል፡፡ (መዝ119፤100-105፣ መዝ67፤1-2)
የእግዚአብሄር ቃል ይህን ያህል አስፈላጊና ወሳኝ መሆኑን ከተረዳን፤ ያልተደባለቀውንና ንፁህ የሆነውን የእግዚአብሄርን ቃል ብቻ ለይተን ለመያዝ በጥንቃቄ መትጋት አለብን፡፡ ምክንያቱም ስለ ማንኛውም ጉዳይ ከእግዚአብሄር ጋር የምንገናኘው በቃሉ እውነት ላይ በመቆም ብቻ ነውና፡፡ (ዕብ10፤21-22)