Heavenly Crown media ministry

Heavenly Crown media ministry Media

አፍን ሁንዱማትን ሲያፋርፋችሱ
01/10/2023

አፍን ሁንዱማትን ሲያፋርፋችሱ

Watch, follow, and discover more trending content.

30/04/2023

🌀🌀 "ሀሉም በጊዜው ይሆናል"! 🌀🌀

✅ ያለ ሰዓቱ አይነጋም!"

✅ ጨርሶ አይጨልምም።

👉 ፀሐይ ስትጠልቅ፣ ጨረቃና ከዋክብት ይወጣሉ።

👉 ዘጠኝ በሮች ሲዘጉ አንዱ ይከፈታል።

👉 ዘጠኝ ወዳጆች ሲሄዱ አንዱ ይተርፋል።

👉 ፀሐይ ባትጠልቅ ጨረቃ አትታይም። ፈተና ካልመጣምየማናውቃቸው ሰዎች አሉ።

👉 ፈተናው የሚሰጠን የመጨረሻ ውጤት የቅርብ ያልነው ሩቅ፣ የሩቅ ያልነው የቅርብ መሆኑን ነው።

👉 ፀሐይ እንደምትወጣ እርግጠኞች ነን።
👉 ጨረቃና ከዋክብት ለመውጣታቸው ግን እርግጠኛ አይደለንም።

👉 ጨረቃ የማትወለድበት፣ ከዋክብት የሚሰወሩበት ጊዜ አለ።

👉 የምታስተማምነዋ ፀሐይ ስትጠልቅ ያልጠበቅናቸው ጨረቃና ከዋክብት ይወጣሉ።

👉 የማታ ብርሃኖች ዙሪያውን በደንብ ባያሳዩንም ለእግራችን መርገጫ ያሳዩናል።

👉 ሰማዩን በውበት ይገልጡልናል። የብርሃንን ዋጋ እንድናስብና እንድንሰስት ያደርጉናል።

👉 እንደ ፀሐይ እርግጠኛ የሆንባቸው ሊጠልቁ ይችላሉ።

👉 ያልጠበቅናቸው ደግሞ ብቅ ይላሉ። ጨርሶ አይጨልምምና።

👉 “ፀሐይ ስለ መጥለቋ ከተመረርህ ከዋክብትም ይሰወሩብሃል” ይባላል።

👉 ቢወጡም አታያቸውም ማለት ነው።

👉 ምሬት ዓይንን ያጨልማልና።

🌀✅ #አዎ ያለ ሰዓቱ አይነጋም።

👉 አሁን ለመተኛት ገብተን ወዲያው ቢነጋ መልካም አይደለም።

🌀✅ #ያለ ሰዓቱ ከነጋ፡-

1️⃣ "አእምሮአችን አይታደስም፡-

👉 አእምሮ የሚታደሰው የዋልንበትን አሳብ ፍጹም ትተን ስናርፍ ነው።

👉 በቂ ዕረፍት ስናገኝ ለቀጣዩ ቀን መማርና መሥራት እንችላለን።

👉 በሕይወት ውስጥ የሚገጥመን የፈተና ሰዓትም ራሳችንንና ዙሪያችንን እንድናይ ስለሚረዱን ያበስሉናል።

🌀✅ እኔ ማን ነኝ?

👉 የምኖረው ከእነማን ጋር ነው? የሚለውን ጥያቄ መመለስ የምንችለው በመከራ ሰዓት ነው።

👉 የፈተና ቀኖች የጠለለ አሳብን፣ የተጣራ ወዳጅን ያስቀሩልናል።

👉 ለቀጣዩ ዘመንም በቀላሉ የማይበገር አእምሮን ያጎናጽፉናል።

👉 ያለ ሰዓቱ ካልነጋ አንበስልም።

👉 እኛ የሚያስጨንቀን መከራው ነው፣ ጌታ ግን ትምህርቱ እንዳያልፈን ያስባል።

👉 ሕጻን ልጅ ስለ መድኃኒቱ ምሬት ያለቅሳል፣ ወላጆች ግን ስለመዳኑ ይጨክናሉ።

👉 ሩኅሩኁ ጌታ እስክንማር ይጨክናል።

2️⃣ "ከድካም አንላቀቅም፡-

👉 ያለ ሰዓቱ ከነጋ አሁን የተለየነው ግርግር መልሶ ይመጣል።

👉 አሁን የተውነውን ሥራ እንቀጥላለን።

👉 ከድካም ስለማንበረታ በቀጣዩ ቀን እንደክማለን፣ እንወድቃለን፣ በሥራችንም ውጤታማ አንሆንም።

👉 የቀጣዩን ቀን ትግል ለመቋቋም በሰዓቱ መንጋት አለበት።

👉 እግዚአብሔር ከግርግሩ ለይቶ፣ ሱስ ከሆኑብን የጊዜ ገዳዮች አውጥቶ የሚያሳርፈን በጨለማ ቀኖች ነው።

👉 በሰዓቱ ሲነጋ በርትተን ለቀጣዩ ዘመን ኃይል ይዘን እንቆማለን።

👉 በሰዓቱ ይንጋ፣ በትግሎቻችን ሁሉ ጌታ ትዕግሥት ይስጠን።

✅ የማይነጋ ሌሊት የለም።
✅ ማታ ጠዋት ይሆናል።
✅ ማታ የተለየን ጠዋት ይመጣል።

🌀👉 ጠዋት ሲመጣ ግን በሰዓቱ ነግቷልና አእምሮአችን ታድሶ፣ አቅማችን በርትቶ እንቀበለዋለን።

#ፈጣሪ ጸጋውን ያብዛልን!
#ሀገራችንና ህዝቦቿን ከክፉው ሁሉ ይጠብቅልን!"(አሜን)
ምርጥ መጣጥፎች
ሼርርርር

የካማሺ ቅዱሳን በካማሺ ቁ1 ሙ/ወ/ቤ/ክ ኮንፈረንሰ
30/04/2023

የካማሺ ቅዱሳን በካማሺ ቁ1 ሙ/ወ/ቤ/ክ ኮንፈረንሰ

Watch, follow, and discover more trending content.

30/04/2023

የካማሺ ቅዱሳን በካማሺ ሙሉ ወንጌል ቤቴክርስቲያን ኮንፈረንስ
30/04/2023

የካማሺ ቅዱሳን በካማሺ ሙሉ ወንጌል ቤቴክርስቲያን ኮንፈረንስ

18/04/2023

እስከዛሬ ተናግሬው የማላውቀውን ገጠመኜን ላውራችሁ
ሚስጥር ነበር

እንዲህ ከገጠመኝ ላካፍላችሁ
አንዴ ምን ሆንኩላችሁ መሰላችሁ ጠዋት ላይ ነው ከቤቴ ልወጣ ተዘጋጅቼ ጨርሼ ከዛም ስልኬን ብፈልገው አጣሁት ያልፈለኩበት የለም የት እንዳረኩት ጠፍቶኝ ግራ ገባኝ ለካ እያወራሁበት ነበር በራሴ ተገርሜ ቀልቤ ለካ ወሬው ላይ ሆኖ ነው ጉድ ያደረገኝ። ስልኬን ያጣሁትና ስፈልገው የቆየሁት ስልኬ ከእኔ ሩቅ ሆኖ ሳይሆን ጆሮዬ ላይ መሆኑን ዘንግቼው ነው።
አሁንም እግዚአብሔር ሩቅ የመሰለንና ሌላ ቦታ(ሰው) ጋር ፍለጋ የምንዞረው በውስጣችን መሆኑን ዘንግተነው ነው እንጂ እርሱ የቅርብ ነው።
" እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ የሩቅ አምላክ አይደለሁም። "
(ትንቢተ ኤርምያስ 23:23)
እግዚአብሔር ከእኛ አልራቀም እኛ ነን ከእርሱ የራቅነው በዚህ ክፍል እንደሚያወራው የቅርብ እንጂ የሩቅ አይደለሁም ይለናል
ታድያ እርሱ የቅርብ ነኝ ካለ ማን ነው የራቀው?

እንኳን እግዚአብሔር በቅርብ ያለ ጓደኛ እንኳን ይሰማል። በተለይ ደግሞ ለኛ ለአዲሱ ኪዳን አማኞች እግዚአብሔር የቅርባችን ብቻ ሳይሆን መኖሪያው ነው ያደረገን።
" ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።
"
(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:19-20)
----------
5፤ እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።

6፤ በእኔ የማይኖር ቢሆን እንደ ቅርንጫፍ ወደ ውጭ ይጣላል ይደርቅማል፤ እነርሱንም ሰብስበው ወደ እሳት ይጥሉአቸዋል፥ ያቃጥሉአቸውማል።

7፤ በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል።
(የዮሐንስ ወንጌል ምዕ. 15)
እንግዲህ እርሱ በእኛ የሚኖር ከሆነ ደግሞ ከእስትንፋሳችንም ቅርብ ከሆነ መስማት ያቃተን እኛ እንጂ ሳይሰማን ቀርቶ አያውቅም።
ለነገሩ ሰው በክርስቶስ ኢየሱስ ማን እንደተደረገ ስላላወቀ እግዚአብሔር የሚሰማው አይመስለውም ስለዚህም የሚሰማለት ፃድቅ(ለእግዚአብሔር ቅርብ) የሆነን ሰው ፍለጋ ሳይታክተው ይዞራል ይልቅ ዙረታችንን አቁመን በውስጣችን ያደረውን(ያልራቀውን) ጌታ እንቅረበውና ጥያቄ ይዘን ሳይሆን ምስጋና ተሞልተን ለማመስገንና ምስክር ለመሆን እንቀሳቀስ።
ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለናል።
ቃሉ የሚለንን ልክ እንደዝያው ነን። ቃሉ ምን እንደምለን ደግሞ ከፍተን ማንበብ ይኖርብናል።
ድሮ ድሮ ትዝ ይለኛል እናቶቻችን ብራቸውን መፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያስቀምጡ ነበር እናም እዝያው ያገኙት ነበር ምክንያቱም ማንም አይከፍተውማ።
ማንም ለህመሙ ዋ መድሃኒት ይዤአለሁ ቢለው አይተወውም መፍትሄው መድኃኒቱን መዋጥ ነው።
መፅሐፍ ቅዱስ በተለያየ ቋንቋ እቤታችን ቢኖረን ካላነበብነው
(ቃሉን ካልዋጥነው) መፍትሔ የለም። ቃሉ ውስጥ ሁሉም አለ።
(መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 34)
----------
1፤ እግዚአብሔርን ሁልጊዜ እባርከዋለሁ፥ ምስጋናውንም ዘወትር በአፌ ነው።

2፤ ነፍሴ በእግዚአብሔር ትከብራለች፥ ገሮችም ሰምተው ደስ ይላቸዋል።

3፤ እግዚአብሔርን ከእኔ ጋር ታላቅ አድርጉት፥ በአንድነትም ስሙን ከፍ ከፍ እናድርግ።

4፤ እግዚአብሔርን ፈለግሁት መለሰልኝም፥ ከመከራዬም ሁሉ አዳነኝ።

5፤ ወደ እርሱ ቅረቡ ያበራላችሁማል፥ ፊታችሁም አያፍርም።

6፤ ይህ ችግረኛ ጮኸ፥ እግዚአብሔርም ሰማው፥ ከመከራውም ሁሉ አዳነው።
ከእግዚአብሔር ጋር ሩቅ አይደለንም በደሙ ኃይል ቀርበናል።

" አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል።"
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2:13)
በጌታ ወንድማችሁ ፓስተር ሶፎንያስ ሞላልኝ ነኝ።
ከወደዱት ሼር ያድርጉት

አለማየሁ የእግዚአብሔር ሰዉ እንኳን እግዚአብሔር ባላበትህን ለዚህ አበቃት።
21/08/2022

አለማየሁ የእግዚአብሔር ሰዉ እንኳን እግዚአብሔር ባላበትህን ለዚህ አበቃት።

እኔን የለወጠ ጥቅስ ዮሐ 15 ነዉ አንብቡት
18/08/2022

እኔን የለወጠ ጥቅስ ዮሐ 15 ነዉ አንብቡት

እስከዛሬ ተናግሬው የማላውቀውን ገጠመኜን ላውራችሁ
ሚስጥር ነበር

እንዲህ ከገጠመኝ ላካፍላችሁ
አንዴ ምን ሆንኩላችሁ መሰላችሁ ጠዋት ላይ ነው ከቤቴ ልወጣ ተዘጋጅቼ ጨርሼ ከዛም ስልኬን ብፈልገው አጣሁት ያልፈለኩበት የለም የት እንዳረኩት ጠፍቶኝ ግራ ገባኝ ለካ እያወራሁበት ነበር በራሴ ተገርሜ ቀልቤ ለካ ወሬው ላይ ሆኖ ነው ጉድ ያደረገኝ። ስልኬን ያጣሁትና ስፈልገው የቆየሁት ስልኬ ከእኔ ሩቅ ሆኖ ሳይሆን ጆሮዬ ላይ መሆኑን ዘንግቼው ነው።
አሁንም እግዚአብሔር ሩቅ የመሰለንና ሌላ ቦታ(ሰው) ጋር ፍለጋ የምንዞረው በውስጣችን መሆኑን ዘንግተነው ነው እንጂ እርሱ የቅርብ ነው።
" እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ የሩቅ አምላክ አይደለሁም። "
(ትንቢተ ኤርምያስ 23:23)
እግዚአብሔር ከእኛ አልራቀም እኛ ነን ከእርሱ የራቅነው በዚህ ክፍል እንደሚያወራው የቅርብ እንጂ የሩቅ አይደለሁም ይለናል
ታድያ እርሱ የቅርብ ነኝ ካለ ማን ነው የራቀው?

እንኳን እግዚአብሔር በቅርብ ያለ ጓደኛ እንኳን ይሰማል። በተለይ ደግሞ ለኛ ለአዲሱ ኪዳን አማኞች እግዚአብሔር የቅርባችን ብቻ ሳይሆን መኖሪያው ነው ያደረገን።
" ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።
"
(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:19-20)
----------
5፤ እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።

6፤ በእኔ የማይኖር ቢሆን እንደ ቅርንጫፍ ወደ ውጭ ይጣላል ይደርቅማል፤ እነርሱንም ሰብስበው ወደ እሳት ይጥሉአቸዋል፥ ያቃጥሉአቸውማል።

7፤ በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል።
(የዮሐንስ ወንጌል ምዕ. 15)
እንግዲህ እርሱ በእኛ የሚኖር ከሆነ ደግሞ ከእስትንፋሳችንም ቅርብ ከሆነ መስማት ያቃተን እኛ እንጂ ሳይሰማን ቀርቶ አያውቅም።
ለነገሩ ሰው በክርስቶስ ኢየሱስ ማን እንደተደረገ ስላላወቀ እግዚአብሔር የሚሰማው አይመስለውም ስለዚህም የሚሰማለት ፃድቅ(ለእግዚአብሔር ቅርብ) የሆነን ሰው ፍለጋ ሳይታክተው ይዞራል ይልቅ ዙረታችንን አቁመን በውስጣችን ያደረውን(ያልራቀውን) ጌታ እንቅረበውና ጥያቄ ይዘን ሳይሆን ምስጋና ተሞልተን ለማመስገንና ምስክር ለመሆን እንቀሳቀስ።
ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለናል።
ቃሉ የሚለንን ልክ እንደዝያው ነን። ቃሉ ምን እንደምለን ደግሞ ከፍተን ማንበብ ይኖርብናል።
ድሮ ድሮ ትዝ ይለኛል እናቶቻችን ብራቸውን መፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያስቀምጡ ነበር እናም እዝያው ያገኙት ነበር ምክንያቱም ማንም አይከፍተውማ።
ማንም ለህመሙ ዋ መድሃኒት ይዤአለሁ ቢለው አይተወውም መፍትሄው መድኃኒቱን መዋጥ ነው።
መፅሐፍ ቅዱስ በተለያየ ቋንቋ እቤታችን ቢኖረን ካላነበብነው
(ቃሉን ካልዋጥነው) መፍትሔ የለም። ቃሉ ውስጥ ሁሉም አለ።
(መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 34)
----------
1፤ እግዚአብሔርን ሁልጊዜ እባርከዋለሁ፥ ምስጋናውንም ዘወትር በአፌ ነው።

2፤ ነፍሴ በእግዚአብሔር ትከብራለች፥ ገሮችም ሰምተው ደስ ይላቸዋል።

3፤ እግዚአብሔርን ከእኔ ጋር ታላቅ አድርጉት፥ በአንድነትም ስሙን ከፍ ከፍ እናድርግ።

4፤ እግዚአብሔርን ፈለግሁት መለሰልኝም፥ ከመከራዬም ሁሉ አዳነኝ።

5፤ ወደ እርሱ ቅረቡ ያበራላችሁማል፥ ፊታችሁም አያፍርም።

6፤ ይህ ችግረኛ ጮኸ፥ እግዚአብሔርም ሰማው፥ ከመከራውም ሁሉ አዳነው።
ከእግዚአብሔር ጋር ሩቅ አይደለንም በደሙ ኃይል ቀርበናል።

" አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል።"
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2:13)
በጌታ ወንድማችሁ ፓስተር ሶፎንያስ ሞላልኝ ነኝ።
ከወደዱት ሼር ያድርጉት

18/08/2022

Peace be unto you

MOHC media
30/03/2022

MOHC media

05/03/2022

GOD IS GREAT

Address

Benishangul Gumuz
Asosa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Heavenly Crown media ministry posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Heavenly Crown media ministry:

Share