Areka Centeral KHC Children's Ministry Official

Areka Centeral KHC Children's Ministry Official Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Areka Centeral KHC Children's Ministry Official, Religious organisation, South, Areka.

(1ኛ የዮሐንስ መልእክት ምዕራፍ 4)
----------
14፤ እኛም አይተናል አባትም ልጁን የዓለም መድኃኒት ሊሆን እንደ ላከው እንመሰክራለን።

15፤ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በሚታመን ሁሉ እግዚአብሔር በእርሱ ይኖራል እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል።

 ለመሪዎችና ለመላው አባላቶቿ ስለ ዘመኑ "የሐዋርያትና የነቢያት" አገልግሎት ጉዳይ የወጣ ደብዳቤ
23/05/2026


ለመሪዎችና ለመላው አባላቶቿ ስለ ዘመኑ "የሐዋርያትና የነቢያት" አገልግሎት ጉዳይ የወጣ ደብዳቤ

19/05/2026
16/05/2026



1. ከዓላማ አንጻር : የድሮዎቹ ትኩረታቸው በክርስቶስ ላይ:በቅድስና ላይ:በእግዝአብሔር መንግስት ላይ ብቻ ነው።የአሁኖቹ ትኩረታቸው በእግዝአብሔር መንግስት በሚመስል ካባ ውስጥ ገብቶ ራሳቸውን ማበልጸግ :ፎቅ መስራት :የተንደላጠጠ ኑሮ ለመኖር ወዘተ...
2. ከጥሪያቸው አንጻር: የድሮዎች ቀጥታ እግዝአብሔር ለአገልግሎቱ የጠራቸው ስማቸውና ተግባራቸው የሚገናኝባቸው :ለተቀበሉት አውነት ለመሰዋት የተዘጋጁ:ሞትን እየተጋፈጡ ኖሮ ያለፋ ናቸው።የአሁኖዎቹ ደግሞ ራሳቸውን የሰየሙ :በሰየሙት ስም ካልተጠሩ የሚናደዱ:ቤተክርስቲያን ለአገልግሎት ያለሰማራቻቸው:ቤተክርስቲያን ብሎ ያቋቋሙትን ተቋም የንግድ ቤት ያደረጉ ናቸው። በነዝህ በሁለቱ እንዃን ስናያቸው የአሁኖችን አሰራር መቶ በመቶ መጽሐፍ ቅዱስ ውድቅ ያደርጋል ። በመጨረሻም የራሴ ግል ምክር ለመለጠፍ እፈልጋለሁ ::
1) እግዝአብሔር ጸጋ ሰጥቶኛል የሚል ማንም ቢኖር እንደ እግዚአብሔር ቃል ያገልግል።
2) ትኩረታችሁን ገንዘብ:መክና :የተደላቀቄ ኑሮ እኖራለሁ ከሚትሉ ለክርስቶስ ስባል በባዶ እግር ለመሄድ ተዘጋጁ ወንገል መሰዋዕት የሚያስከፍል ስለሆነ
3. ነቢይነት:ሐዋሪያነት ገንዘብ መሰብሰቢያ ሳይሆን መሰዋዕት ለመሆን መዘጋጀት እንደሆነ እውቁ
4. ነቢይ ነኝ ሐዋሪያ ነኝ እያላችሁ የሰውን ቤት ለቤት የሚትዞሩ አርፋችሁ ወደ ጓዳ ግቡ ጸልዩ ቤተክርስቲያን ስታሰማራችሁ ጠናማ አገልግሎት አገልግሉ
5. ይህ አገልግሎት የሚያበላ መስሏችሁ በዝህ ሙያ ካልገባው የሚትሉ ለንግድ የሚሆን ትንሽዬን ሱቅ ክፈቱ
ማጠቃለያ:
ሐዋሪያነት:ነቢይነት ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚሰጥ የጸጋ ስጦታ ስሆን ቤተክርስቲያን ታሰማራለች። ከዝህ ውጪ ራስን በራስ ነቢይ:ሐዋሪያ እያሉ ማቆላጳጰስ ልክ አይደለም። ተግባርና ጸጋ አንድ ይሁን።
✍️Habtam haile

ዛሬ ከሰዓት
03/05/2026

ዛሬ ከሰዓት

የነገ እሁድ  9:00. ጀምሮ በአረካ ከተማ መኃል አጥቢያ ቃ/ህ/ቤ/ያን
30/04/2026

የነገ እሁድ 9:00. ጀምሮ በአረካ ከተማ መኃል አጥቢያ ቃ/ህ/ቤ/ያን

 ቤተክርስቲያኗ የተመሰረተችው በ1961 ዓ.ም ሲሆን፣ አጀማመሯም በጥቂት አማኞች አማካኝነት በየቤቱ በሚደረግ የጸሎትና የአምልኮ ሥነ-ሥርዓት ነበር። የአማኞች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ ቋሚ የ...
25/04/2026


ቤተክርስቲያኗ የተመሰረተችው በ1961 ዓ.ም ሲሆን፣ አጀማመሯም በጥቂት አማኞች አማካኝነት በየቤቱ በሚደረግ የጸሎትና የአምልኮ ሥነ-ሥርዓት ነበር።
የአማኞች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ ቋሚ የመሰብሰቢያ ቦታ አስፈላጊ ሆነ። በዚህም መሠረት ኮሚቴ ተዋቅሮ ለከተማው መስተዳድር የቦታ ጥያቄ አቀረበ። መጀመሪያ ላይ መስተዳድሩ "ቦታ የለንም" በሚል ጥያቄውን ውድቅ ቢያደርገውም፣ አማኞቹ ግን በጸሎትና በጥረት በመቀጠላቸው በመጨረሻም አሁን ያለችበት ቦታ ተሰጣቸው።
ቤተክርስቲያኗ ያረፈችበት ቦታ ቀደም ሲል የቆሻሻ መጣያ ተብሎ የሚጠራ ሥፍራ ነበር። ዛሬ ግን ያ የተናቀ ስፍራ በእግዚአብሔር ረድኤት ተለውጦ ለከተማዋ ውበትና ለነዋሪዎቿ የመንፈሳዊ ዕረፍት ምንጭ የሆነ ታላቅ የአምልኮ ስፍራ ለመሆን በቅቷል።
ሰሞኑን ከአረካ ከተማ አስተዳደር በአረካ ከተማ ቁ-1 ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ላይ
ስለሚደርሰውና እየደረሰ ላለው በደል አስመልክቶ

👉 ወቅታዊ የአቋም መግለጫ ነጥቦች

ቤተክርስቲያኗ በሰሞኑ ሁኔታ ላይ ያላትን አቋም በሚከተሉት አምስት ነጥቦች ገልጻለች፡-
ሀ/ የጸሎት ጥሪ፦ በመላው ዓለምና በኢትዮጵያ የሚገኙ ምዕመናን ሁሉ ስለ ቤተክርስቲያኗ በጸሎት እንዲተጉ ጥሪ ቀርቧል።
ለ/ የስም ማጥፋት ዘመቻ ይቁም፦ በቤተክርስቲያኗና በመሪዎቿ ላይ የተጀመረው የማጥቃትና ስም የማጥፋት ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲቆም ትጠይቃለች።
ሐ/ የልማት ስራ እንቅፋት ይወገድ፦ ቤተክርስቲያኗ የገዛ ይዞታዋን እንዳታለማ የተከለከለችበትንና በልማት ስራዋ ላይ የተጻፈውን የማገጃ ደብዳቤ አጥብቃ ትቃወማለች፤ የተጀመረው ሁከትም እንዲቆም ትጠይቃለች።
መ/ የሕልውና ጥበቃ፦ የቤተክርስቲያንን ሕልውና አደጋ ላይ የሚጥሉና ስሟን የሚያጠለሹ ማናቸውም የዘመቻ ተግባራት እንዲቆሙ አጥብቃ ታሳስባለች።
ሠ/ የመንግስት ጣልቃ ገብነት፦ የከተማው አስተዳደር በቤተክርስቲያኗና በመሪዎቿ ላይ እያደረሰ ያለውን ኢ-ሕገመንግስታዊ እርምጃና ዛቻ ቤተክርስቲያኗ አጥብቃ ትቃወማለች።
እኛ እንደ ቤተ ክርስቲያን ሁሌም ሰላምን፣ ፍቅርን እና አንድነትን በማስፋፋት ለማህበረሰብ ጥቅም መሥራታችንን እንቀጥላለን። በዚህም ጉዳይ ፍትሃዊ እና ሕጋዊ መፍትሔ እንዲሰጥ በክብር እንጠይቃለን። በቀን 17-08-2018 ዓ.ም. መልዕክቱ ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር በማድረግ እንድትተባበሩ እናሳስባለን።

  ባለ 6 ነጥብ አቋም መግለጫ   እኛ ከሶዶ ከተማ አጠቃላይ ቃለሕይወት አጥቢያዎች የተሰበሰብን የከተማው ቃለሕይወት ጠቅላላ ጉባኤ አባል መሪዎችና አገልጋዮች የክርስትና እምነት  መመሪያና የ...
06/04/2026

ባለ 6 ነጥብ አቋም መግለጫ

እኛ ከሶዶ ከተማ አጠቃላይ ቃለሕይወት አጥቢያዎች የተሰበሰብን የከተማው ቃለሕይወት ጠቅላላ ጉባኤ አባል መሪዎችና አገልጋዮች የክርስትና እምነት መመሪያና የአምላክ እስተንፋስ የሆነውን መጽሐፍ ቅዱስን በመቅደድ የቆቀር መጠቅለያ በማድረግ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ የሆነው አቶ መሐመድ ሽኩር በፈጸመው ተግባር የሚቀጥለውን ባለ 6 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥቷል።
👉1.የክርስትና እምነት የሕይወት መመሪያ የሆነውን መጽሐፍ በመቅደድ ክርስትና እምነት ተከታዮችን ለማስቆጣት ያደረገውን ተግባር በፅኑ እንቃወማለን፣
👉2. የክርስትና እምነት ተከታይ ወጣቶችን ለማስቆጣት ስሉ እጅ ከፍንጅ የተያዘውን የወንጀል ክስተት አንዳንድ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ድራማ ነው እያሉ የሚገልጹትን እንቃወማለን፣
👉3.ድርጊት ፈጻሚው የእስልምና ሃይማኖት ተከታዩ አቶ መሐመድ ሽኩር ድርጊቱን በቀን 23/07/2018 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 አከባቢ ተፈጽሞ እስከ እሁድ ቀን 27/07/2018 ዓ.ም ድረስ ከእስልምና ሃይማኖት ተቋም በኩል ድርጊቱን ያለማውገዙን በከፍተኛ ሁኔታ እናወግዛለን፤እንቃወማለን፣
👉4. የክርስትና እምነት መመሪያና እስተንፋስ እግዚአብሔር የሆነውን መጽሐፍ ለቆቀር መጠቅለያነት ስያውል የነበረውና እጅ ከፍንጅ የተያዘውን ድርጊት ፈጻሚውን በአፋጣኝ ፍትህ መንግስት ተጠያቂ እንድያደርገውና የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ ማህበረሰብ ህጋዊ ጥያቄውን እንድመልስ ካልሆነ ሁሉም ዓይነት ሠላማዊ ድምጻችን የምናሰማበት መንገድ እንድፈቀድ መንግስትን እንጠይቃለን፣
👉5.የቤተእምነታችን ተከታይ የሆናችሁ በሁሉም ዕድሜ ክልል የሚትገኙ የመጽሐፍ ቅዱስ አማንያን የሆናችሁ እስካሁን ድረስ በተፈጸመዊ ሰይጣናዊ ድርጊት ምክንያት ስህተትን በስህተት ከማረም ይልቅ መጽሐፍ ቅዱስ ራሱ የሚዋጋ መጽሐፍ መሆኑን በመገናዘብ በሠላማዊ መንገድ የጀመራችሁትን ትግል ብቻ እንድትቀጥሉ እንጠይቃለን፣
👉6.የአባባ ዋንዳሮና ሌሎች የወንጌል አባቶችን የሠላም ወንጌል ትምህርት ከጌታ አባቶቻችን የተቀበሉትን ወንጌል ተቀብላ የሠላም ተምሳሌት በመሆን የሚትታወቀው የደ/ኢት/ያ የክልሉ ርዕሰ መዲና የሆነቺው የሶዶ ከተማ ሁሉም ሃይማኖቶች ተቻችለው ፣ተከባብረው በሰላምና በፍቅር የሚኖሩባት የአብሮነት ከተማ ፀጥታዋ እንድታወክ በሃይማኖቶች መካከል ጥላቻ እንድነሳ የተደረገውን ተግባር እንቃወማለን።

እግዚአብሔር ወላይታና ኢትዮጵያን ይባርክ!!
/ክያናት_ኅብረት
መጋቢት 27/2018

02/04/2026

ይህች እናት በመሀመድ ሸኩር /መጽሐፍ ቅዱስ እየቀደደ ቆቀር በሚጠቀልለው አሸባሪ በራፍ ሁሉ ጊዜ ትመላለሳለች። እማማ የምታለቅስበት ምክንያት 😭😭 እየለች ታለቅሳለች። 😭😭😭 ዋታነ ስማ 😭😭😭

😭😭😭😭😭...በጌታ የሆናችሁ-ሁላችሁም   አድርጉ  ⁉️ይህ ከታች በፎቶ የሚትመለከቱት ሌላ ወረቀት ሳይሆን በወላይታ ሶዶ ከተማ አሮጌ አራዳ ከጊዮርጊስ ቤተ/ያን በታች በኩል አቶ   በተባለ  ...
02/04/2026

😭😭😭😭😭...በጌታ የሆናችሁ-ሁላችሁም አድርጉ
⁉️
ይህ ከታች በፎቶ የሚትመለከቱት ሌላ ወረቀት ሳይሆን በወላይታ ሶዶ ከተማ አሮጌ አራዳ ከጊዮርጊስ ቤተ/ያን በታች በኩል አቶ በተባለ ሸይ ቤት ተቀድዶ ቆቀር ጠቅልሎ የሚሸጠው መጽሐፍ ቅዱስ ነው።😭 ክርስቲያኖች ይህ ርኩስ ተግባር በአካባቢያችን ሲአሰት ዝምታችን እስከ መቼ ነው⁉️ በሌላ አከባቢ እንደተከሰተው በወንጌል አገር ቤተ/ንቷ በእሳት እስከሚትቃጠል ነው የሚንጠብቀው⁉️ #ይጠየቁ❗️ 😭
የመጽሐፍ ቅዱሱ ጌታ ሆይ ወደ አንተ እንጮሃለን !😭
ይደረግ!

25/03/2026

Address

South
Areka
CENTERALKALEHIYWET

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Areka Centeral KHC Children's Ministry Official posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share