Al-Hidaya Islamic University

Al-Hidaya Islamic University አልሂዳያ ኢስላማዊ ዩንቨርሲቲ በጉራጌ ዞን ጉመር እየተገነባ የሚገኝ ተቋም ሲሆን በምዕራፍ 1 ያስገነባው መስጅድና መድረሳው ተመርቆ ስራ ጀምሯል።
(1)

24/02/2026

Construction Progress update‼

የካቲት 17/2018

ህንፃ 1:

#2ኛ ፎቅ ስላብ እየተሞላ ይገኛል

#ያለቀላቸው ፍሎሮች ፓርቲሽን ለመስራት ብሎኬት እየገባ ይገኛል

ህንፃ 2:

#የምድር ወለል ግሬድ ቢም እየተሰራ ይገኛል

1447ኛው ሂጅራ ረመዷን ነገ እሮብ 1 ብሎ እንደሚጀምር ታውቋል ‼አላህ ጨርሰው ከሚፆሙት እና ፆመው ከሚጠቀሙት ያድርገንረመዷን ሙባረክ
17/02/2026

1447ኛው ሂጅራ ረመዷን ነገ እሮብ 1 ብሎ እንደሚጀምር ታውቋል ‼

አላህ ጨርሰው ከሚፆሙት እና ፆመው ከሚጠቀሙት ያድርገን

ረመዷን ሙባረክ

15/02/2026

የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ አሁናዊ የግንባታ ሁኔታ! !

Progress Update ( የህንፃ ግንባታ ሁኔታ) : 1የህንፃ ዓይነት: B + G + 4 + Tአገልግሎት: የተማሪዎች መኖሪያ (Dormitory)የህንፃ ስፋት: 625 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈአሁ...
07/02/2026

Progress Update ( የህንፃ ግንባታ ሁኔታ)

: 1

የህንፃ ዓይነት: B + G + 4 + T

አገልግሎት: የተማሪዎች መኖሪያ (Dormitory)

የህንፃ ስፋት: 625 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ

አሁን ያለበት ደረጃ:

የ1ኛ ፎቅ ኮለኖች በመሙላት ጉዞ ወደ 2ኛ ፎቅ ግንባታ ስራ ተጀምሯል

2 ግንባታ ደረጃ በሌላ ፖስት እንመለሳለን

የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ 3ኛ ህንፃ ግንባታ ተበሰረ‼በትናንትናው እለት ጥር 23/2018 በአድዋ ዜሮ ዜሮ በነበረ የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ ነው የ3...
01/02/2026

የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ 3ኛ ህንፃ ግንባታ ተበሰረ‼

በትናንትናው እለት ጥር 23/2018 በአድዋ ዜሮ ዜሮ በነበረ የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ ነው የ3ኛው ህንፃ ግንባታ እንደሚጀመር የተበሰረው።

የሁለት ህንፃዎች ግንባታ በአሁኑ ወቅት በፍጥነት እየተከናወነ ባለበት በዚህ ወቅት 3ኛ ህንፃ ለማስጀመር የአክስዮን ሽያጭ ተጀምሯል።

ህንፃው 108 ሚሊየን ብር ወጪ የሚጠይቅ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይ የተገኙ እና ሌሎች ወንድም እህቶች በአክስዮን መልክ ሊገነቡት ቃል ገብተዋል። ለህንፃው በተለያዩ ኸይር ስራዎች የሚታወቁ 5 እንቁ ወንድሞቻችን ወንድም መቃሙ ሀሰን፣ ወንድም አንዋር ኸድር፣ ወንድም መኪ አብደላህ፣ ኡስታዝ ሰዓድ ጅላሉ፣ እና ኢንጅነር ሷሊህ በአስገንቢ ኮሚቴነት ተመርጠዋል።

ህንፃውን በ18 ወራት ገንብተው በማጠናቀቅ ለአልሂዳያ እንደሚያስረክቡ ኮሚቴዎቹ የገለፁ ሲሆን የአንድ አክስዮን ዋጋ 360ሺህ ብር ሆኖ ባለአክስዮኖች እንደአቅማቸው በየወሩ፣ በየ3 ወር፣ በየ 6 ወር ፣ወይም ሙሉውን በአንዴ ወይም በሁለቴ መክፈል የሚችሉበት አሰራር ተዘርግቶ በእለቱ የተወሰኑ አክስዮኖች ተሽጠዋል። አጠቃላይ 300 አክስዮኖች ለዚህ ህንፃ ግንባታ እንደሚሸጥ የተነገረ ሲሆን ተሽቀዳዳሚዎች ለአኼራቸው እንዲሽቀዳደሙ ጥሪ ቀርቧል።

የአክስዮኑ ገቢ ማድረጊያ የራሱ የተለየ አካውንት በአልሂዳያ የተዘጋጀ ሲሆን ማንኛውም ሰው ከአንድ አክስዮን ጀምሮ የቻለውን ያህል መግዛት እንደሚችል እና ሁሉም ኸይር ፈላጊ ይህንን አክስዮን በመሸጥ ይረባረብ ዘንድ የቤት ስራ ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተ/ም/ፕሬዚዳንት የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ ሳይት ጎበኙ‼በትናንትናው እለት ጥር  14/2018 ዓ ል የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ...
23/01/2026

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተ/ም/ፕሬዚዳንት የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ ሳይት ጎበኙ‼

በትናንትናው እለት ጥር 14/2018 ዓ ል የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተ/ም/ፕሬዚዳንት ክቡር ሸይኽ ዐብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ ሳይት ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸው ወቅት የ2ቱ ህንፃዎች ግንባታ ሂደት ተዛዙረው የተመለከቱ ሲሆን የግንባታው ሂደት እና ፍጥነት እጅግ እንዳስደሰታቸው ገልፀው እጅግ የሚያኮራ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በመጨረሻም ገንዘባቸውን፣ ጊዜያቸውን እና ጉልበታቸውን መሰዋዕት እያደረጉ ላሉ ሁሉ አመስግነው ዱዓ አድርገዋል።

የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ የመሰረት ድንጋይ የዛሬ 3 አመት ታህሳስ 02/2015 ዓ ል በእሳቸው መቀመጡ የሚታወስ ነው።

22/01/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከ/ም/ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ኡስታዝ በህጃ ዐብዱል ጀሊል ከአልሂዳያ ግንባታ ሳይት ያስተላለፉት መልዕክት

16/01/2026

የኡስታዝ ሰለሓዲን መልዕክት ከአልሂዳያ ግንባታ ሳይት ...

15/01/2026

ኡስታዝ አዩብ ከአልሂዳያ ግንባታ ሳይት ያስተላለፈው መልዕክት ...

13/01/2026

የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ አምባሳደር የሆነው የውዱ ኡስታዛችን Abubeker Hussien መልዕክት ከአልሂዳያ ግንባታ ሳይት ...

11/01/2026

የኡስታዝ ዐብዱልመናን መልዕክት ከአልሂዳያ ግንባታ ሳይት ...

ዛሬ ታህሳስ 29/2018 ከተለያዩ ማ/ሰብ ክፍሎች የተውጣጡ የአልሂዳያ ቤተሰቦች፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከ/ም/ ቤት አመራሮች፣ የሁለቱም ጉራጌ ዞኖች እስልምና ጉዳዮች ...
07/01/2026

ዛሬ ታህሳስ 29/2018 ከተለያዩ ማ/ሰብ ክፍሎች የተውጣጡ የአልሂዳያ ቤተሰቦች፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከ/ም/ ቤት አመራሮች፣ የሁለቱም ጉራጌ ዞኖች እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት አመራሮች፣ ታላላቅ ኡስታዞች፣ የአልሂዳያ የቦርድ አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የአልሂዳያ አምባሳደሮች፣ የአልሂዳያ ግሩፕ አድሚኖች ወዘተ.... የአልሂዳያ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ ሳይት በመገኘት ጎብኝተዋል‼

Address

Dember-Gumer Mazoria, Addis Ababa To Hosana Road
Arek'it

Telephone

+251911267224

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Al-Hidaya Islamic University posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Al-Hidaya Islamic University:

Share