15/09/2026
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከ/ም/ቤት ፕሬዚዳንት ኢማም ሐጅ ዐብዱልሃዲ አህመድ ቡርሃን፣ ም/ፕሬዚዳንቱ ሸኽ በህጃ ዐ/ጀሊል፣ የዑምራ እና ሐጅ ተጠሪ ሸኽ ሳዲቅ ወጌቦ፣ የጉራጌ ዞን እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ሰብሳቢ ሸኽ አባስ ያሲን የቁርአን ሂፍዝ ተመራቂዎቻችን ካስመረቁ በኋላ የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሮጀክት ያለበት ሁኔታ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
ፕሬዚዳንቱ ኢማም ሐጅ ዐብዱልሃዲ በክልል እስልምና ጉዳዮች ከ/ም/ቤት ስም 300 ሺህ ብር ለአልሂዳያ ዩኒቨርሲቲ ፕሮጀክት የነየቱ ሲሆን በግላቸው 50 ሺህ ብር እዚያው ገቢ አድርገዋል። በሌላ በኩል የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ የማስፋፊያ ቦታ ጥያቄ ከክልሉ እና ከዞኑ መንግስት ጋር በመነጋገር እንዲፈታ እንደሚያደርጉ በመድረኩ ገልፀዋል።
ጀዛኩሙሏህ ኸይር መሪዎቻችን!