ፍጡነ ረድኤት የአርባ ምንጭ ደ/ፀ/ቅ/ጊዮርጊስና ደ/ሎ/ቅ/ኪዳነ ምሕረት አቢያተ ክርስቲያናት ሚዲያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Mintch
  • ፍጡነ ረድኤት የአርባ ምንጭ ደ/ፀ/ቅ/ጊዮርጊስና ደ/ሎ/ቅ/ኪዳነ ምሕረት አቢያተ ክርስቲያናት ሚዲያ

ፍጡነ ረድኤት የአርባ ምንጭ ደ/ፀ/ቅ/ጊዮርጊስና ደ/ሎ/ቅ/ኪዳነ ምሕረት አቢያተ ክርስቲያናት ሚዲያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ፍጡነ ረድኤት የአርባ ምንጭ ደ/ፀ/ቅ/ጊዮርጊስና ደ/ሎ/ቅ/ኪዳነ ምሕረት አቢያተ ክርስቲያናት ሚዲያ, Religious Center, Arba minch, Arba Mintch.

የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ እጩ ምሩቃን ደቀ መዛሙርት ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቡራኬ ተቀበሉ። ግንቦት ፳ ፳፻፲፰ ዓ.ም   በብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከ...
28/05/2026

የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ እጩ ምሩቃን ደቀ መዛሙርት ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቡራኬ ተቀበሉ።

ግንቦት ፳ ፳፻፲፰ ዓ.ም

በብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አባታዊ ምሪት፣ በወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ እጩ ምሩቃን ደቀመዛሙርት ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዘንድ ቀርበው ቡራኬ ተቀበሉ

​ኮሌጁ ለሁለተኛ ጊዜ የሚያስመርቃቸው እነዚህ ደቀ መዛሙርት፣ ባለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት በዲፕሎማ መርሐ ግብር የሥነ መለኮቱንና የአብነቱን ትምህርት አስተባብረው የተማሩ ናቸው። ተማሪዎቹ በቆይታቸው የንድፈ ሐሳብ ትምህርት ብቻ ሳይሆን፣ ወደፊት ለሚጠብቃቸው ሰፊ የቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚበጅ ተግባራዊ የክህነት ልምምድ እንዲኖራቸው በብፁዕነታቸው ከፍተኛ ጥረት መደረጉ ታውቋል።

​የኮሌጁ እጩ ምሩቃን እንደገለጡት፤ ከቃል ስብከት ባለፈ ምሳሌ የሚሆን የአገልግሎት ሕይወት እንዲኖራቸው ተደርጎ መሠራቱና የብፁዕነታቸው የቅርብ ክትትል መኖሩ፣ ወደፊት ለሚኖራቸው መንፈሳዊ ጉዞ ትልቅ ስንቅ እንደሚሆናቸው ገልጸዋል።

ይህ ከቅዱስነታቸው የተገኘው አባታዊ ቡራኬም፣ ተመርቀው ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለአገልግሎት በሚሰማሩበት ወቅት ቤተክርስቲያንን ይበልጥ በጠንካራ መንፈስና በትጋት ለማገልገል ትልቅ ኃይልና መነሳሳትን እንደሚፈጥርላቸው ተማሪዎቹ በደስታ ገልጸዋል።

​በዚሁ ታላቅ የቡራኬ መርሐ ግብር ላይ የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ እጩ ምሩቃንን ጨምሮ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ እና የሐዋሳ ታቦር ፍኖተ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ እጩ ደቀመዛሙርት በጋራ ተገኝተዋል።

​የዕለቱ የቡራኬ መርሐ ግብር ከተጠናቀቀ በኋላ፣ የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ እጩ ደቀመዛሙርት ሌላ መንፈሳዊ ጉብኝት አድርገዋል። በዚህም መሠረት ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በነበሩበት ወቅት ያደራጁትን የቦሌ ቡልቡላ አቡነ ተክለሃይማኖት የእናቶች ገዳምን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን፣ እዚያም በብፁዕነታቸው የጸሎት ሥነ ሥርዓት ተከናውኖላቸዋል።

@ ሳሌም ሚዲያ ጉራጌ ሀገረ ስብከት/Gurage Diocese ነው
👇👇👇👇👇👇
ፍጡነ ረድኤት የአርባ ምንጭ ደ/ፀ/ቅ/ጊዮርጊስና ደ/ሎ/ቅ/ኪዳነ ምሕረት አቢያተ ክርስቲያናት ሚዲያ

"እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ" ሉቃ ፩፥፲፱ኃያሉ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሁሌም በንጉሡ በእግዚአብሔር ፊት ይቁምልን (ይጸልይልን)    ግንቦት ፲፱ ፳፻፲፰ ዓ.ም 👇👇👇👇👇👇...
27/05/2026

"እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ" ሉቃ ፩፥፲፱
ኃያሉ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሁሌም በንጉሡ በእግዚአብሔር ፊት ይቁምልን (ይጸልይልን)
ግንቦት ፲፱ ፳፻፲፰ ዓ.ም

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ፍጡነ ረድኤት የአርባ ምንጭ ደ/ፀ/ቅ/ጊዮርጊስና ደ/ሎ/ቅ/ኪዳነ ምሕረት አቢያተ ክርስቲያናት ሚዲያ

በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ በተገኙበት ቅዳሴ ቤት በዓል ተከበረ።ግንቦት ፲፮ ፳፻፲፰ ...
24/05/2026

በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት
ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ በተገኙበት ቅዳሴ ቤት በዓል ተከበረ።

ግንቦት ፲፮ ፳፻፲፰ ዓ.ም
@ EOTC

24/05/2026

በጋሞኛ ቋንቋ ተተርጉሞ በመመረቅ ላይ ያለው የውዳሴ ማርያም መጽሐፍ ተባርኮ ሲከፈት

በጋሞኛ ቋንቋ የተተረጎመው የውዳሴ ማርያም  መጽሐፍ ተመረቀ ግንቦት ፲፮ ፳፻፲፰ ዓ.ም   በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ማኅበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል አማኞች በቋንቋቸው መጸለይ...
24/05/2026

በጋሞኛ ቋንቋ የተተረጎመው የውዳሴ ማርያም መጽሐፍ ተመረቀ

ግንቦት ፲፮ ፳፻፲፰ ዓ.ም

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ማኅበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል አማኞች በቋንቋቸው መጸለይ እንዲችሉ ብቁ መምህራንን በመመደብ በጋሞኛ ቋንቋ ያስተረጎመው የውዳሴ ማርያም መጽሐፍ በታላቅ ድምቀት ተመረቀ

የምረቃ ሥነ ሥርዓቱም በአርባ ምንጭ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የማኅበረ ቅዱሳን አዳራሽ ውስጥ የተካሄደ ሲሆን በመርኃ ግብሩ ላይ የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ዋና ጸሐፊ ክቡር መጋቤ ሠናያት ያዕቆብ ደስታን ጨምሮ ታላላቅ አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም በርካታ ምእመናንና መዕመናት በመገኘት የተሰመቸውን ደስታ ገልጸዋል
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ፍጡነ ረድኤት የአርባ ምንጭ ደ/ፀ/ቅ/ጊዮርጊስና ደ/ሎ/ቅ/ኪዳነ ምሕረት አቢያተ ክርስቲያናት ሚዲያ

24/05/2026

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ማኅበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል አማኞች በቋንቋቸው መጸለይ እንዲችሉ በጋሞኛ ቋንቋ የተተረጎመው የውዳሴ ማርያም መጽሐፍ የምረቃ መርኃ ግብር በቀጥታ ስርጭት

ታላቅ መንፈሳዊ የምስራች! በጋሞኛ ቋንቋ ተተርጉሞ የተዘጋጀው የ“ውዳሴ ማርያም” የጸሎት መጽሐፍ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በአርባ ምንጭ ይካሄዳል።፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠ግን...
23/05/2026

ታላቅ መንፈሳዊ የምስራች!

በጋሞኛ ቋንቋ ተተርጉሞ የተዘጋጀው የ“ውዳሴ ማርያም” የጸሎት መጽሐፍ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በአርባ ምንጭ ይካሄዳል።
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ግንቦት ፲፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም

«ከእግዚአብሔርም ሕግ መጽሐፍ አነበቡ፥ ትርጓሜውንም እየሰጡ አስታወቁት፥ ሕዝቡም ንባቡን አስተዋለ።» ነህምያ ፰:፰

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን አገልግሎትን በቋንቋቸው ተደራሽ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ እና በጋሞኛ ቋንቋ የተተረጎመው የ“ውዳሴ ማርያም” የጸሎት መጽሐፍ የምረቃ መርሃ-ግብር በአርባ ምንጭ ከተማ እንደሚካሄድ ተገለጸ።

ይህንን ታላቅ መንፈሳዊ መርሃ-ግብር ያዘጋጀው በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ማኅበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም ምዕመናን የእግዚአብሔርን ቃል እና የድንግል ማርያምን ምስጋና በቋንቋቸው በመማርና በመጸለይ መንፈሳዊ ሕይወታቸውን እንዲያሳድጉና ለነፍሳቸው ስንቅ እንዲሰበስቡ ታስቦ የተዘጋጀ ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ መሆኑ ታውቋል።

በዕለቱ በሚካሄደው ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ በጋሞኛ ቋንቋ የተተረጎመው የ“ውዳሴ ማርያም” የጸሎት መጽሐፍ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት፣ ዕለቱን የጠበቀ መንፈሳዊ ስብከተ ወንጌል፣ በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን የሚቀርቡ መንፈሳዊ መዝሙራት እና ሌሎች ልዩ ልዩ መንፈሳዊ መርሃ-ግብሮች ይካሄዳሉ።

በዚህ ታላቅ መርሃ-ግብር ላይ የሀገረ ስብከቱ ዋና ፀሐፊ መጋቤ ሰናያት ያዕቆብ ደስታ፣ የሀገረ ስብከቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣የአድባራትና የገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና መምህራነ ወንጌል፣ዘማሪያን፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች በክብር ይገኛሉ።

ይህ ታሪካዊ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት የሚካሄድበት የፊታችን እሁድ ግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በአርባ ምንጭ ደ/ኃ/ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በሚገኘው በማኅበረ ቅዱሳን ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ሲሆን አዘጋጁ ማኅበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል ነው

መረጃው፦ ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ፍጡነ ረድኤት የአርባ ምንጭ ደ/ፀ/ቅ/ጊዮርጊስና ደ/ሎ/ቅ/ኪዳነ ምሕረት አቢያተ ክርስቲያናት ሚዲያ

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ለሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለአገልግሎት የሚሆን ፕራዶ መኪና ገዝቶ በስጦታ አበረከተ፡፡ ግንቦት ፲፫ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም   ...
21/05/2026

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ለሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለአገልግሎት የሚሆን ፕራዶ መኪና ገዝቶ በስጦታ አበረከተ፡፡
ግንቦት ፲፫ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የመኪናውን ቁልፍ ለብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል የካፋ ሸካ ቤንች ማጂ ምዕራብ ኦሞ እና የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሊቀ ጳጳስ የበላይ ኃላፊ አበርክተዋል፡፡
ቅዱስነታቸው በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት “ሥራ የሚሠራ ሰው ዋጋ ይገባዋል፡፡ ለአገልግሎት የሚሆን መኪና አስፈላጊ ነው፡፡ ብፁዕነትዎ እርስዎ ብዙ ጊዜ ሲጠይቁ ቆይተው አሁን ማግኘትዎ በጣም ደስ ብሎናል፤ ለአገልግሎት የሚሆን መኪና ስላገኙ ሁላችንም ደስ ብሎናል፤ እግዚአብሔር የተባረከ ያድርግልዎት” ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመርሐ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት “ቀደም ሲል ለቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ በተያዘው በጀት ዓመት ቅዱስ ሲኖዶስ በቅዱስ አባታችን መመሪያ ሰጪነትና የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በወሰነው ውሳኔ መሠረት ፕራዶ መኪና እንዲገዛ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል በጠየቁት መሠረት ጥሩ መኪና ተገዝቶላቸዋል፡፡ ብለውል፡፡
በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤልም እንደተናገሩት “እግዚአብሔር በወሰነው ጊዜና ሰዓት ጥሩ መኪና ተገዝቶልናል፤ ለዚህም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ አስተዋጽኦ መሠረት ሲሆን፤ ይህን ያደረገ አምላክ የተመሰገነ ይሁን፣ እግዚአብሔር ይስጥልን ስለተደረገልኝ በጣም አመሰግናለው” ብለዋል፡፡
የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ት/ቤት ከተመሠረተበት ከ1935 ዓም ጀምሮ መንፈሳዊውንና ዘመናዊውን ትምህርት ጎን ለጎን በማስተማር አያሌ ሊቃውንትን፣ ጳጳሳትንና ሊቃነ ጳጳሳትን በማፍራት የታወቀ አንጋፋ ትምህርት ቤት መሆኑ ይታወቃል፡፡በአሁኑ ወቅትም የትምህርት አድማሱን በማስፋት የትምህርት አገልግሎቱን አጠናክሮ እየቀጠለ መሆኑ ይታወቃል፡፡
👇👇👇👇👇👇👇👇
ፍጡነ ረድኤት የአርባ ምንጭ ደ/ፀ/ቅ/ጊዮርጊስና ደ/ሎ/ቅ/ኪዳነ ምሕረት አቢያተ ክርስቲያናት ሚዲያ

+ ዕርገተ እግዚእ + የጌታ ዕርገት                   እንኳን አደረሳችሁ!!በዚህች ዕለት የክብር ባለቤት ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእኛ በነሣው ሥጋ ከአባቱና ከመንፈ...
21/05/2026

+ ዕርገተ እግዚእ + የጌታ ዕርገት
እንኳን አደረሳችሁ!!

በዚህች ዕለት የክብር ባለቤት ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእኛ በነሣው ሥጋ ከአባቱና ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ ወደአለው የአንድነት አኗኗሩ ከሰማያት በላይ ያረገበት በዓል ይከበራል።

እርሱም በረቀቀ ጥበቡ በመከራው በሞቱና በመነሣቱ ሥራውን ከፈጸመ በኋላ አርባው ቀን ሲፈጸም በነፋሳት ክንፍ ላይ ሆኖ ዐረገ።

ያን ጊዜ በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ ወጣ በነፋሳትም ክንፎች ላይ ሁኖ ወጣ ያለው የዳዊት ትንቢት ተፈጸመ። በዚህም ዕርገቱ ለሚያምኑበት በልዕልና ወደሚኖሩበት የሚዐርጉ መሆናቸው ተረዳ ተረጋገጠ ራስ በአለበት ሕዋሳት ሊኖሩ ይገባልና ።

አዳም አስቀድሞ በምድራዊ ርስቶች በሲኦልም እንደኖረ መኖርንም እንደ ቀደመ እንዲሁ ዳግማዊ አዳም ጌታ በመንግሥተ ሰማያት ርስት መኖርን ቀደመ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ዕርገቱን ከትንሣኤው አከታትሎ ወዲያውኑ አላደረገም መናፍቃን ዕርገቱ ምትሐት ናት ብለው እንዳያስቡ።

ጌታችንም በረቀቀ ጥበቡ የደቀ መዛሙርቱን ተሸብሮ የነበረ ልቡናቸውን እያጽናና መነሣቱንም እያስረዳቸው ከትንሣኤው በኋላ አርባ ቀን ኖረ። በጌታችንም ዕርገት የዳንኤል ትንቢት ተፈጸመ እንዲህ የሚል ሌሊት በራእይ አየሁ እነሆ ታላቅ እንደ ሰው ልጅ የሆነ መጣ ዘመናትን ወደሚያስረጃቸው ደረሰ ከፊቱም አቀረቡት።

የዘላለም አገዛዝ ጌትነት መንግሥት የዘላለም ሥልጣን ተሰጠው ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነዋሪ ነው።

የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት  በዓለ ንግሥ በአርባ ምንጭ እድገት በር ደብረ አእላፍ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ተከበረ
20/05/2026

የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ንግሥ በአርባ ምንጭ እድገት በር ደብረ አእላፍ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ተከበረ

ነቅዐ ጽድቅ  የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ
20/05/2026

ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ

Address

Arba Minch
Arba Mintch

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ፍጡነ ረድኤት የአርባ ምንጭ ደ/ፀ/ቅ/ጊዮርጊስና ደ/ሎ/ቅ/ኪዳነ ምሕረት አቢያተ ክርስቲያናት ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share