በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Mintch
  • በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ, Religious Center, Gamo zone, Arba Mintch.

ይህ በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ ነው። ሚዲያው በሀገረ ስብከቱ መመሪያ ሰጭነትና በወረዳው ቤተ ክህነት እውቅና ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ተከፈተ። አላማው የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ለዓለም ማስተጋባት በወረዳው የሚከናወኑ መንፈሳዊና ልማታዊ እንቅስቃሴዎችን ለምዕመናን ተደራሽ ማድረግ ነው። ሚዲያው ለመንፈሳዊ ዓላማ ቢቻ የተከፈተ ነው።

ቀን24/12/2018 ዓ.ም የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ የንግሥ በዓል በሰላም ተከብሮ ዋለ!በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት፣ በዳራማሎ ወረዳ ቤተክህነት ስር በሚገኘው በ...
30/08/2026

ቀን24/12/2018 ዓ.ም

የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ የንግሥ በዓል በሰላም ተከብሮ ዋለ!

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት፣ በዳራማሎ ወረዳ ቤተክህነት ስር በሚገኘው በዶምኣ ቀበሌ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ዓመታዊው የንግሥ በዓል በመንፈሳዊ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።

በዕለቱ በተካሄደው የጻድቁ አባታችን መታሰቢያ ሥነ-ሥርዓት ላይ የአከባቢው ካህናት፣ ዲያቆናትና በርካታ ቁጥር ያላቸው ምዕመናን ተገኝተዋል። የበዓሉ ታዳሚዎች በያሬዳዊ ወረብ፣ በማኅሌትና በእልልታ በዓሉን በታላቅ መንፈሳዊ ተመስጦ አሳልፈውታል።

የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ረድኤት፣ በረከትና ምልጃ ከሁላችን ጋር ይሁን!

አሜን።

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ

ቀን 24/12/2018 ዓ.ም➣የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ የንግሥ በዓል በሰላም ተከብሮ ዋለ!➣በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት፣ በዳራማሎ ወረዳ ቤተክህነት ስር በሚገኘው...
30/08/2026

ቀን 24/12/2018 ዓ.ም

➣የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ የንግሥ በዓል በሰላም ተከብሮ ዋለ!

➣በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት፣ በዳራማሎ ወረዳ ቤተክህነት ስር በሚገኘው በሌጼ ቀበሌ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ዓመታዊው የንግሥ በዓል በመንፈሳዊ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።

➣በዕለቱ በተካሄደው የጻድቁ አባታችን መታሰቢያ ሥነ-ሥርዓት ላይ የዳራማሎ ወረዳ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ ጨምሮ የአከባቢው ካህናት፣ ዲያቆናትና በርካታ ቁጥር ያላቸው ምዕመናን ተገኝተዋል። የበዓሉ ታዳሚዎች በያሬዳዊ ወረብ፣ በማኅሌትና በእልልታ በዓሉን በታላቅ መንፈሳዊ ተመስጦ አሳልፈውታል።

➣የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ረድኤት፣ በረከትና ምልጃ ከሁላችን ጋር ይሁን!

አሜን።🙏🙏

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ

ቀን 24/12/2018 ዓ.ምበጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ "የሌሊቱ ማህሌት ምስጋና ይህንን ይመስላል!"በጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት በዳራማሎ ወረዳ...
30/08/2026

ቀን 24/12/2018 ዓ.ም

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ

"የሌሊቱ ማህሌት ምስጋና ይህንን ይመስላል!"

በጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት በዳራማሎ ወረዳ ቤተክህነት ስር በሚገኘው በዶምኣ አብነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን፤ የቅዱስ አባታችን የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ የንግስ በዓልን ምክንያት በማድረግ በመከናወን ላይ የሚገኘው መንፈሳዊ የሌሊት ማህሌት አገልግሎት ይህንን ይመስላል።

ካህናቱ በያሬዳዊ ዜማና በሽብሸባ፣ ምዕመናኑም በታላቅ ተመስጦ ፈጣሪያቸውን በምስጋና እያገለገሉ ይገኛሉ።

የአባታችን የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ረድኤትና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን!

እንኳን ለአቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ በዓል ዋዜማ በሰላም አደረሳችሁ!በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በዳራማሎ ወረዳ ቤተክህነት ስር በሚገኘው በዶምኣ ቀበሌ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክር...
29/08/2026

እንኳን ለአቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ በዓል ዋዜማ በሰላም አደረሳችሁ!

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በዳራማሎ ወረዳ ቤተክህነት ስር በሚገኘው በዶምኣ ቀበሌ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን የዋዜማው በዓል በመንፈሳዊ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የአከባቢው ካህናት፣ ዲያቆናትና ምዕመናን ተገኝተው በያሬዳዊ ወረብ፣ በማኅሌትና በእልልታ በዓሉን ታድመውታል።

የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ረድኤትና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን!

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ

እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ወርሃዊ መታሰቢያ በዓል አደረሰን አደረሳችሁ!!"የእግዚአብሔርም መልአክ ከአናንያና ከአዛርያ ከሚሳኤልም ጋር ወደሚነደው ወደ እሳቱ ምድጃ ወርዶ ከምድጃ ...
25/08/2026

እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ወርሃዊ መታሰቢያ በዓል አደረሰን አደረሳችሁ!!

"የእግዚአብሔርም መልአክ ከአናንያና ከአዛርያ ከሚሳኤልም ጋር ወደሚነደው ወደ እሳቱ ምድጃ ወርዶ ከምድጃ ያለውን እሳት መታው፤ የእሳቱንም ነበልባል እንደ ቀዝቃዛ ነፋስ አደረገው፤ እነዚያንም ሰዎች እሳቱ ምንም አልነካቸውም፤ የራሳቸውንም ጠጕር አልለበለባቸውም፤ አላስጨነቃቸውምም።"(ትንቢተ ዳንኤል ፫፥፵፱-፶)

በናቡከደነፆር ዘመን በነበልባሉ እቶን ውስጥ የነደደውን እሳት አየር አልባ ወላፈኑን ወደ ቀዝቃዛ ነፋስ የለወጠ፣ አምላክን ለሚያምኑና በቅንነት ለሚመላለሱ አጋዥ የሆነው ቅዱስ መልአክ ተራዳኢነቱ አይለየን።

ለእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የደስታንና የሰላምን ብስራት ያበሰረ መልአክ፣ በሕይወታችን ውስጥም የመከራውን ዘመን አልፎ የደስታና የሰላም ዘመን እንዲተካ በጸሎቱ ይደግፈን።

በዚህ ቅዱስ ቀን፣ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በምልጃው ከክፉ ሁሉ ይጠብቀን፤ በቤታችን አድሮ ፍቅርን፣ ሰላምንና በረከትን ያብዛልን።

የቅዱስ ገብርኤል ጥበቃና ምልጃ አይለየን!
በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ ቀን16/12/2018 ዓ.ም ☑️“ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባ...
22/08/2026

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ

ቀን16/12/2018 ዓ.ም

☑️“ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ” (ሉቃስ 1፥28)

ለመላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች፣ ለሀገረ ስብከታችንና ለወረዳችን ምእመናንና ምእመናት በሙሉ፦

☑️በጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት፣ በዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር በሚገኘው በዎማላ ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን የእመቤታችን የዓመታዊ በዓል (የነሐሴ 16 መታሰቢያ) በሰላም አደረሳችሁ!

☑️የዘንድሮው የነሐሴ 16 የቅድስት ኪዳነ ምህረት ዓመታዊ በዓል በዎማላ ቅድስት ኪዳነ ምህረት ደብር እጅግ ደማቅና መንፈሳዊ ይዘቱን በጠበቀ ታላቅ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።

☑️በዚህ ታላቅ በዓል ላይ የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር በኩረ ትጉሃን ቀሲስ ጌትነት ደሳለኝ በቦታው በአካል በመገኘት በዓሉን በጸሎትና በማስተማር መርተዋል። በተጨማሪም የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንተ ካህናትና ዲያቆናት በተገኙበት የዕለቱ ማኅሌትና ቅዳሴ በታላቅ ያሬዳዊ ሥርዓት ተከናውኗል። ሊቃውንቱ የዕለቱን ምስጋናና የእግዚአብሔርን ቃል በምሥጢርና በምሳሌ ያቀረቡ ሲሆን፣ በበዓሉ ልዩ መዝሙራት ምእመናኑን በታላቅ መንፈሳዊ ደስታ አስፈንጥዘዋል።

በዚህ በተቀደሰ ዕለት፦

☑️የ16ቱን ቀን ሙሉ የፍልሰታ ሱባኤ የገባችሁ፣በሌሊት ማኅሌት የቆማችሁ፣በቅዳሴ ያስቀደሳችሁና የበረከቱ ተሳታፊ የሆናችሁ የመካነ ቅዱሳኑ ምእመናን በሙሉ፤

☑️እናታችን ቅድስት ኪዳነ ምህረት ልመናችሁንና መስዋዕታችሁን ተቀብላ፣ ከቅዱስ ልጇ ዘንድ የምሕረትና የሰላም ዋጋን ታስጥላችሁ። ከቁጥር ሳታጎድለን፣ ሁላችንንም በፍቅርና በጤና ለሚቀጥለው ዓመት በሰላም ታድርሰን።

☑️የእመቤታችን የቅድስት ኪዳነ ምህረት አማላጅነትና በረከት አይለየን!

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያቀን16/12/2018 ዓ.ም➦የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማሪያም አመታዊ ክብር ባዓል በጋሞና አካባቢው ሀገር ስብከት በ...
22/08/2026

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ

ቀን16/12/2018 ዓ.ም

➦የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማሪያም አመታዊ ክብር ባዓል በጋሞና አካባቢው ሀገር ስብከት በዳራማሎ ወረዳ ቤተክህነት የዎማላ ቅድስት ክዳኔ ምህረት ቤተክርስቲያን የሌሊቱ አገልግሎት በፎቶግራፍ በክፍል 👇

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ ቀን 13/12/2018 ዓ.ም➣ባዓለ ደብር ታቦር በዋጫ ምስራቀ ፀሐይ ቅድስት ድንግል ማሪያም ቤተክርስቲያን የተወሰደ የ...
19/08/2026

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ

ቀን 13/12/2018 ዓ.ም

➣ባዓለ ደብር ታቦር በዋጫ ምስራቀ ፀሐይ ቅድስት ድንግል ማሪያም ቤተክርስቲያን የተወሰደ የዕለቱ የሌሊት ማህሌቱ አገልግሎት ፎቶግራፍ በከፍል👇

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ በሳውላ ማረሚያ ተቋም ተገኝተው ታራሚዎችን አጽናኑ።በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን “ዛቲ ይእቲ...
10/08/2026

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ
ብፁዕ አቡነ ኤልያስ በሳውላ ማረሚያ ተቋም ተገኝተው ታራሚዎችን አጽናኑ።

በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን “ዛቲ ይእቲ ምዕራፍዬ ለዓለም” በሚል ርዕስ መንፈሳዊ ትምህርት ሰጡ።

ማረሚያ ቤት የሕይወት መጨረሻ ሳይሆን ራስን የማደስና የመለወጥ ዕድል መሆኑን አስተምረዋል።

ታራሚዎችም ቂምን በመተው በንስሐና በይቅርታ ወደ ፈጣሪ እንዲቀርቡ መክረዋል።

በመጨረሻም በመባረክና በማጽናናት የአባታዊ ፍቅራቸውን ገልጸዋል።

መረጃ ምንጭ፦ግናይ ሚዲያ የአርባ ምንጭ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል እና ደብረ መንክራት ቅዱስ ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት ሚዲያ

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ ➡️በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት፣ በዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ስር በሚገኘው ጥንታዊው የኤሊ ደብረ ብሥራት ቅ...
02/08/2026

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ

➡️በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት፣ በዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ስር በሚገኘው ጥንታዊው የኤሊ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ለሦስት ተከታታይ ቀናት (ከሐምሌ ፳፬ እስከ ፳፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም) ሲካሄድ የቆየው ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ሦስተኛውና የመጨረሻው ቀን መርሐ ግብር በታላቅ ድምቀት የጥዋቱ ተጠናቋል።

➡️በዕለቱ የሀገረ ስብከቱ የሒሳብና በጀት ክፍል ኃላፊ መጋቤ ሃብታት ቀሲስ ደጉ አልቤ እና የወረዳው ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ በኩረ ትጉሃን ቀሲስ ጌትነት ደሳለኝ ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው አባቶችና እንግዶች በቦታው ተገኝተዋል። መጋቤ ሃብታት ቀሲስ ደጉ አልቤ ጉባኤውን በቡራኬ የከፈቱ ሲሆን፣ ጥልቅ የቃለ እግዚአብሔር ትምህርትም ለአማንያኑ አስተላልፈዋል።

Address

Gamo Zone
Arba Mintch

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዳራማሎ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share