ሞሌ አባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን - Molle Abay Ber Kale Hiwot Church

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Mintch
  • ሞሌ አባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን - Molle Abay Ber Kale Hiwot Church

ሞሌ አባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን - Molle Abay Ber Kale Hiwot Church የአባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን PAGE ነው
📖 የሕይወት ቃል ለሁሉም!✨ የወንጌል ብርሃን የሚበራባት፣ ፍቅርና አንድነት የነገሰባት ቤተክርስቲያን።
🕊️ መንፈሳዊ እድገት | አገልግሎት | ወንድማማችነት

"እግዚአብሔርን በማወቅ ማደግ

15/04/2026

🥰

‎🌟 የትንሳኤ በዓል በሞሌ አባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን 🌟‎"ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶልናል!"‎‎ዛሬ በሞሌ አባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሳ...
12/04/2026

‎🌟 የትንሳኤ በዓል በሞሌ አባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን 🌟
‎"ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶልናል!"

‎ዛሬ በሞሌ አባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሳኤ በዓል በታላቅ ድምቀት አክብረናል። እግዚአብሔር በዚህች ምድር ላይ ራሱን ዝቅ አድርጎ ሲሰራ አይተናል፤ ክብሩንም ተመልክተናል! 🙌✨

‎በዕለቱ የነበረው የአምልኮ ጊዜ እጅግ ልዩ ነበር፦

‎በዝማሬ፦ ከቤተክርስቲያናችን አምልኮ መርዎች ና ከመዘምራን ህብረት (Choir) ጋር በመሆን እግዚአብሔርን ከፍ አድርገናል። 🎶🎤

‎በቃል፦ ከአገልጋይ ማርቆስ ጋር በመሆን "ፋሲካ ምንድነው?" በሚል ርዕስ ጥልቅ የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል ተካፍለናል። ፋሲካችን የታረደልን ክርስቶስ መሆኑን ተረድተናል! 📖 ሰምተናል! ተባርከናል!

‎እግዚአብሔር አምላክ ስሙ ለዘላለም የተባረከ ይሁን! አሜን። 🕊️🔥

‎ #ትንሳኤ #ፋሲካ #አምልኮ 🥰

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ ለሰው ልጆች ሁሉ የድል፣ የተስፋና የዘላለም ሕይወት ብስራት ነው!‎‎"እርሱ በሕይወት አለ፤ እንደተናገረ ተነስቷል!" (ማቴዎስ 28:6)‎‎ሞትን ድል አድር...
11/04/2026

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ ለሰው ልጆች ሁሉ የድል፣ የተስፋና የዘላለም ሕይወት ብስራት ነው!

‎"እርሱ በሕይወት አለ፤ እንደተናገረ ተነስቷል!" (ማቴዎስ 28:6)

‎ሞትን ድል አድርጎ ለተነሳው፣ የጨለማውን ኃይል ላሸነፈው ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ክብርና ምስጋና ይሁን። ይህ በዓል የሞት ጥላ ተገፎ የሕይወት ብርሃን የበራበት፣ ተስፋ መቁረጥ አብቅቶ አዲስ ሕይወት የተጀመረበት ታላቅ ቀን ነው።

‎የሞል አባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ለወዳጆቻችን፣ ለምዕመናንና ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ፦

‎✨ እንኳን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ✨

‎በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የበረከት እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን። የትንሳኤው ኃይል በቤታችሁ፣ በሥራችሁና በሕይወታችሁ ሁሉ ይገለጥ!

‎ክርስቶስ ተነስቷል! በእውነት ተነስቷል!

‎ #ትንሳኤ #ፋሲካ #ኢየሱስክርስቶስ #ሞላአባይበር #ቃለሕይወት

ዛሬ በሞል አባይ በር ቃል ህይወት ቤተክርስቲያን ከታላላቅ እስከ ታናናሽ፣ ከጎልማሳ እስከ ህፃናት ሁላችንም በጋራ ተንበርክከን የንስሐ ጸሎት ያደረግንበት ድንቅ ጊዜ ነበር። 🙏✨‎‎ጌታ ለህዝቡ...
05/04/2026

ዛሬ በሞል አባይ በር ቃል ህይወት ቤተክርስቲያን ከታላላቅ እስከ ታናናሽ፣ ከጎልማሳ እስከ ህፃናት ሁላችንም በጋራ ተንበርክከን የንስሐ ጸሎት ያደረግንበት ድንቅ ጊዜ ነበር። 🙏✨

‎ጌታ ለህዝቡ ይቅርታውን እንዲልክ፣ ወደ ቀድሞ ማንነታችንም እንዲመልሰን በምልጃ ፊት አሳልፈናል:: እግዚአብሔር አምላክ ልመናችንን ሰምቶ ምህረቱን በሀገራችን ላይ ያውርድ። 🇪🇹🙌

‎📖 'በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈልጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።' (2 ዜና 7:14)

‎ጌታ ስሙ ይባረክ! ተመስገን!"🥰🥰🙏

01/04/2026

‎ #ያስረሳችሗል ዘፍ 41:51
‎ዮሴፍ የበኩር ልጁን ስም እግዚአብሄር መከራዬን አስረሳኝ ሲል #ምናሴ አለዉ። የዮሴፍ አብዛኛዉ ሕይወት የመከራ ሕይወት ነዉ፥ የመተዉ፣ የመጠላት፣ የመሸጥ፣ በሀሰት የመወንጀል፡ የስደት መጠጊያ የማጣት ነበር። እግዚአብሄር ሲጎበኘዉ ግን ሁሉንም አስረሳኝ አለ
‎የማያልፉ የሚመስሉ ክፉ ቀናቶች፣ ሞት የሚያስመኙ ጨለማዎች፥ ተስፋ በማጣት እያሳለፋችሁ ሊሆን ይችላል እግዚአብሄር በካሳ ሲመጣ ግን ሁሉንም ያስረሳል። ዛሬ ላይ ይህ ቃል ላይገባችሁ ይችላል ግን እርግጠኛ ነኝ እናንተም እንደ ዮሴፍ እግዚአብሄር መከራዬን ሁሉ አስረሳኝ ትላላችሁ።
‎ያስረሳችሗል።

‎✨ ልዩ የእሁድ ጠዋት @ ሞል አባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ✨‎ዛሬ እሁድ መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም (March 29, 2026) በሞል አባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ...
29/03/2026

‎✨ ልዩ የእሁድ ጠዋት @ ሞል አባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ✨
‎ዛሬ እሁድ መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም (March 29, 2026) በሞል አባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ድንቅ ጊዜ ነበረን! እግዚአብሔር በመካከላችን ተገኝቶ በረከቱን አፍስሷል።

‎በቃል፡ ከአገልጋይ እስራኤል ጋር በመሆን የእግዚአብሔርን ቃል ተካፍለናል፤ ልባችንም ታድሷል።

‎በአምልኮ፡ ከዘማሪ ዳጊ እና ከቤተ ክርስቲያናችን የአምልኮ መሪዎች ጋር በመሆን ጌታን በከፍታ አምልከናል።በመዝሙር፡ በዝማሬና በስብከት እግዚአብሔርን እያመሰገንን ድንቅ ጊዜ አሳልፈናል።

‎እግዚአብሔር ይመስገን! ስሙ በዙፋኑ ላይ ለዘላለም ከፍ ይበል! 🙏🔥✨

‎በአባያ በር ቃል ህይወት ቤተክርስቲያን  ዛሬ ረቡዕ የተጀመረውን ድንቅ የ"ቅድመ ጋብቻ" ስልጠና በታላቅ ደስታ አሳልፈናል! ⛪️✨‎‎ከፓስተር ተስፉ ቶማ ጋር በነበረን ቆይታ ወጣቶች በከፍተኛ...
25/03/2026

‎በአባያ በር ቃል ህይወት ቤተክርስቲያን ዛሬ ረቡዕ የተጀመረውን ድንቅ የ"ቅድመ ጋብቻ" ስልጠና በታላቅ ደስታ አሳልፈናል! ⛪️✨

‎ከፓስተር ተስፉ ቶማ ጋር በነበረን ቆይታ ወጣቶች በከፍተኛ ተነሳሽነት ትምህርቱን ሲከታተሉና ማስታወሻ ሲይዙ ማየታችን ለሁላችንም ብርታት ሆኖልናል። 🙏📖 እግዚአብሔር ይመስገን፣ ለሁላችንም የታደልንበትና የምንማርበት ጊዜ ነበር።

‎ይህ ልዩ ስልጠና አርብ ጠዋት ቀጥሎ፣ ቅዳሜና እሁድም ሙሉ ቀን የሚቀጥል ይሆናል። 📅

‎ሁላችሁም ተገኝታችሁ ከበረከቱ ተካፋይ እንድትሆኑ እንጋብዛለን! 🕊️💍

‎ #ቅድመጋብቻ #ስልጠና # አባያ በር ቃል ህይወት ቤተክርስቲያን #መንፈሳዊህይወት #ወጣቶች #ፍቅርናጋብቻ

24/03/2026

‎በሞሌ አባይ በር ቃል ህይወት ቤተ ክርስቲያን የፌስቡክ ገጽ ተከታታዮች በሙሉ፦

‎በእናታችን ሞሌ መቃ ቃል ህይወት ቤተ ክርስቲያን ልዩ የዝማሬ ኮንሰርት ተዘጋጅቷል። በዚህ መንፈሳዊ መድረክ ላይ ዘማሪት ይብራለም መለሰ በዝማሬ ታገለግለናለች።

‎ሁላችሁም የዚህ ልዩ በረከት ተካፋይ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል።

‎📅 ቀን፦ መጪው አርብ
‎🕘 ሰዓት፦ ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ
‎📍 ቦታ፦ ሞሌ መቃ (እናት) ቃል ህይወት ቤተ ክርስቲያን

‎ኑ! አብረን ጌታን በዝማሬ እናክብር።

‎"እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ስሙንም ጥሩ፤ በአሕዛብም መካከል ሥራውን አስታውቁ።"

‎ #🥰

እስከዚህም ድረስ እግዚአብሔር ረድቶናል” (1ኛ ሳሙኤል 7፡12)በሞሌ አባይ በር ቃል ህይወት ቤተክርስቲያን ላለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የመጀመሪያ አመት የምስረታ በዓል በታላቅ በረ...
23/03/2026

እስከዚህም ድረስ እግዚአብሔር ረድቶናል” (1ኛ ሳሙኤል 7፡12)

በሞሌ አባይ በር ቃል ህይወት ቤተክርስቲያን ላለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የመጀመሪያ አመት የምስረታ በዓል በታላቅ በረከት ተጠናቋል። እግዚአብሔር በአገልጋዮቹ፣ በቃሉና በዝማሬ ህዝቡን ሲጎበኝ ሰንብቷል። ክብር ሁሉ ለአምላካችን ይሁን! በሰላም ላስፈጸመን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይግባው።🥰🙏

የዛሬውን አስደናቂ ቀን በሞሌ አባይበር ቃለ-ህይወት ቤተክርስቲያን ከእናንተ ጋር ለመጋራት ጓጉቻለሁ! 🙌✨ ዛሬ የቤተክርስቲያናችንን የ1ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በታላቅ ድምቀት አክብረናል። 🎉...
22/03/2026

የዛሬውን አስደናቂ ቀን በሞሌ አባይበር ቃለ-ህይወት ቤተክርስቲያን ከእናንተ ጋር ለመጋራት ጓጉቻለሁ! 🙌✨ ዛሬ የቤተክርስቲያናችንን የ1ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በታላቅ ድምቀት አክብረናል። 🎉🙏

የእግዚአብሔር ቃል በነቢይ ይስሐቅ ይፍሩ እና በፓስተር አስፈራቸው ጳውሎስ አማካኝነት ልባችንን የሚነካ መልዕክት ደርሶናል። መንፈስን በሚያድስ ዝማሬ ደግሞ ከዘማሪ እንዳሸው ዱንዳ፣ ከቤተክርስቲያኗ የመዘምራን ህብረት እና ከአዝማች መሪዎች ጋር በመሆን ጌታን ከፍ አድርገናል።

የጌታ መገኘት በቃላት ከሚገለጸው በላይ በእውነት የሚያስደንቅ ነበር! 🕊️🔥 እግዚአብሔር ይመስገን!

⛪✝️🙏🥰

Address

Southern
Arba Mintch

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሞሌ አባይ በር ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን - Molle Abay Ber Kale Hiwot Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share