10/02/2026
፡ ለፍትህና ለቤተክርስቲያን መብት መከበር!
"ርስትህን አትልቀቅ"
በሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ የሚገኘውና ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ጀምሮ በሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ይዞታነት የሚታወቀው ታሪካዊው ቦታችን፤ ዛሬ ከፍተኛ በደልና ግፍ እየተፈጸመበት ይገኛል። ይህ ለበርካታ አስርት ዓመታት ለወንጌል አገልግሎትና ለቅዱሳን ስብስብ ሲያገለግል የቆየ ቅዱስ ስፍራ፣ ዛሬ በማዘጋጃ ቤት አማካኝነት ለግለሰቦች ተላልፎ በመሰጠት የጥፋት ግንባታ እየተካሄደበት ነው።
የሰበካው መሪዎች ጉዳዩ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በተደጋጋሚ አቤቱታ ቢያቀርቡም፣ እስካሁን ሰሚ በማጣት በደሉ እየቀጠለ ይገኛል።
በየካቲት 1 ቀን 2018 ዓ.ም የሰበካው ተወካዮች ግንባታውን በአካል ተገኝተው ለማስቆም ቢሞክሩም፣ አንዳንድ የመንግስት ባለስልጣናት በስተጀርባ ሆነው ህገ-ወጥ ድርጊቱን እያበረታቱ መሆኑን ደርሰንበታል።
ይህ ድርጊት በሀዋሳ የሚገኙ ምዕመናንን ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም የሚገኙ የአድቬንቲስት ማህበረሰብን ታሪክና እሴት የናቀ ፍጹም ህገ-ወጥ ድርጊት ነው።
ለዓለም አቀፍ ምዕመናን፦ ይህ መልዕክት የደረሳችሁ ሁሉ ለሌሎች አባላት በማዳረስ (Share በማድረግ) የበኩላችሁን እንድትወጡና በጽሁፍም ሆነ በማህበራዊ ሚዲያ ድምጽ በመሆን ከጎናችን እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
መንግስት ይህንን በግልጽ እየታየ ያለውን የመብት ጥሰት በአስቸኳይ እንዲያስቆምና የቤተክርስቲያኗን ይዞታ እንዲያስከብር በጥብቅ እንጠይቃለን!
"እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው!"